Ethiopian Coffee and Tea Authority
5.96K subscribers
5.8K photos
30 videos
67 files
370 links
Ethiopian Coffee and Tea Authority
Download Telegram
ቡና ስልጠና ማዕከሉ ውጤታማነትና ያስገኛቸው ጠቀሜታዎች ላይ ጥናት ቀረበ

መጋቢት 01/2018 ዓ.ም
ኢቡሻባ፤

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በቡና ስልጠና ማዕከሉ ውጤታማነትና ያስገኛቸው ጠቀሜታዎች ላይ አበራ ፈይሳ የማማከር አገልግሎት በተባለ የግል ድርጅት ያስጠናውን ጥናት ለሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት እዲቀርብ አድርጓል፡፡

ጥናቱ በማዕከሉ በማሰልጠኛ ሞጁሎች ይዘት፣ የስልጠና አሰጣጥ፣ አቃፊነት፣ የስልጠና ክለጊዜያት በቂነትን ተመልክቷል፡፡

ከሞጁሎች ይዘት አንጻር 90 በመቶ አሰልጣኞች በጣም ጥሩ እንደሆነ፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ የጠበቁ እንደሆኑና ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ፍላጎት የሚያሟሉ ናቸው እንደሆኑ ጥናቱ አሳይቷል፡፡

ከስልጠና አሰጣጥ ጥራት አንጻር በተዳሰሰው ክፍል ደግሞ 76 በመቶ የሚሆኑ አሰልጣኞችና 70 በመቶ የሚሆኑ ሰልጣኞች መልካምና ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና ሂደት እንዳለ ተናግረዋል፡፡ ከስልጠና ክፍለጊዜ አንጻር ግን የንድፈ ሃሳቡንም የተግባር ስልጠናዎችንም በበቂ ሁኔታ ለመስጠት በቂ ጊዜ እንዳልተሰጠ ጥናቱ አስቀምጧል፡፡

ጥናቱ የማዕከሉን ውጤታማነትና ተጽእኖ በተመለከተ ስልጠና በሚሰጥባቸው የቡና ዘርፎች ያለው የቡና ሴክተር የአፈጻጸም ትክክለኝነት፣ ዓላም አቀፍ የቡና ገዢዎች ጋር ያለው ተግባቦት፣ የሰለጠነው የሰው ሃይል በራስ መተማመንና ውሳኔ ሰጪነት እንጨመረ አሳይቷል፡፡

እነዚህንም በመካን 22 በመቶ የሚሆኑት ሰልጣኞች የራሳቸውን የንግድ ስራ እንደከፈቱ እና 10 በመቶ የሚሆኑ ሴት ሰልጣኞች ኢንተርፕረኑር ወደ መሆን ደረጃ እንደደረሱ የተወሳ ሲሆን 13 በመቶ ነባር የቡና ንግድ ስራዎች ማስፋፋት እንደታየባቸው የጥናቱ ውጤት ያሳያል፡፡

በአጠቃላይ እሴት ጭመራ ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የገቢ መሻሻል፣ በገበያ ተወዳዳሪነትን በማስፈን ረገድ የማዕከሉ አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነና እንደሚሆን ተመላክቷል፡፡

መሻሻል እና መታከል ያለባቸውንም ጎኖችንም ጥናቱ ተመልክቷል፡፡ በዚህም መሠረት የስልጠና ፍላጎትና የማዕከሉ አቅም አለመመጣጠን፣ የስልጠና ማቴሪያሎች በበቂ ሁኔታ አለመኖር፣ የአሰልጣኞች የተግባቦት ክህሎት ውሱንነት፣ ውስን የሆኑት ስልጠናዎች ላይ ብቻ የሰልጣኝ ብዛት መኖር፣ የማዕከሉ የቦታ ስፋት ጥበት፣ የጥራት ሰርቲፊኬት ሰጪነት ማንዴት አለመለየት የመሳሰሉትን ጥናቱ ለይቷል፡፡

በቀጣይ መደረግ ያለባቸውንም ሲያወሳ የአየር ንብረት ለውጥ እና ኢንተርፕሬነር የመሳሰሉ ስልጠናዎች ቢካተቱ፣ ስልጠና አሰጣጡ ዲጂታላይዝ ቢሆን፣ ማዕከሉ ወደቡና አብቃይ አካባቢዎች ቢስፋፋ፣ ከሚመለከታቸው የክልልና ዓለም አቀፍ የግልና የመንግስት ድርጅቶች ጋር በቅንጅት መስራት የሚሉትን ጥናቱ እንደመፍትሄ ሃሳብ አቅርቧል፡፡

ጥናቱ ሲቀርብ በቦታው የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አዱኛ ደበላ ባለሰልጣኑ ጥናቱን ያስጠናው የማዕከሉን ጥራት ለማሻሻል ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ጠንካራዎቹን በማጠናከር ደካማ ጎኖችን በመቅረፍ የተሻለ ማሰልጠኛ ተቋም ለማድረግ በማለም እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ማዕከሉን ወደቡና አብቃይ ክልሎች ከማስፋት አንጻር ስራው እንደተጀመረና በጅማ ዞን አንድ ማዕከል እንደተከፈ ተናግረዋል፡፡

በማቴሪያል ከማሟላት አንጻር የሀገር ውስጥም የውጪም አጋርና ባለድርሻ አካላትን በማነጋገር በርካታ የቁሳቁስ እገዛዎችን ማግኘት እንደተቻለና በዚህም በቅንጅት የመስራቱን ተግባር ባለስልጣኑ አስቀድሞም የሄደበት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

አሸናፊ ጌታሁን እንደዘገበው
የቡና ኢንተርናሽናል ባንክ ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣንን ጎበኙ!!
መጋቢት 02/2018
የቡና ኢንተርናሽናል ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉጌታ አለማየሁ እና የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝታቸው ወቅት የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በመሥሪያ ቤቱ እየተከናወኑ ያሉ አበይት ተግባራትን ለባንኩ አመራሮች አስረድተዋል።
በተለይም በዘመናዊ መልክ የተገነባውን የባለሥልጣኑን አዲስ ሕንፃ፣ የቡና ማሰልጠኛ ማዕከልንና የኦንላይን የግብይት ቁጥጥር ሥርዓትን ለጉብኝቱ ቡድን በዝርዝር አስጎብኝተዋል። ይህ ጉብኝት በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን የሥራ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና በዘርፉ እየተከናወኑ ያሉ የቴክኖሎጂ ለውጦችን ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
Higher level officials of Bunna International Bank Visits Ethiopian Coffee and Tea Authority!!
Mr. Mulugeta Alemayehu, President of Bunna International Bank, accompanied by the bank’s senior executive team, conducted an official working visit to the Ethiopian Coffee and Tea Authority. During the visit, the Director General of the Authority, H.E Dr. Adugna Debella, provided a comprehensive briefing on the institution's key strategic initiatives and ongoing projects.
The delegation visited several milestone developments, including the Authority's state-of-the-art headquarters, the modern Coffee Training Center, and the newly implemented online market regulatory system. This visit highlights the growing synergy between the financial sector and the coffee industry, showcasing the technological advancements driving Ethiopia's coffee value chain forward. Reported By Sahlemariam G/medhin
የቡና ገበያ ሲናወጥ፡ ዘላቂ አጋርነት የውድድር ብልጫ አለው!!
በሳህለማርያም ገ/መድህን

ባለፈው አንድ ዓመት የዓለም አቀፉ የቡና ኢንዱስትሪ ላለፉት አሥርተ ዓመታት አይቶት የማያውቀውን ከፍተኛ የዋጋ መዋዠቅ አስተናግዷል። የዋጋ ጣራ መንካት፣ የአሜሪካ የንግድ ታሪፎች እና የአውሮፓ ህብረት አዲሱ የደን ጥበቃ ደንብ (EUDR) ብዙ የቡና ድርጅቶች ስለ አቅርቦት ዋስትና፣ ስለ ዋጋ ስልቶች እና ስለ ረጅም ጊዜ ዕቅዳቸው ደጋግመው እንዲያስቡ፣ እንዲያጤኑ አስገድዷቸዋል።

⚠️ 2025፡ የኢንዱስትሪው የፈተና ዓመት
ያለፈው ዓመት የገበያ ሁኔታ፣ የዋጋ መከላከያ ዘዴዎች (hedging tools) ለሌላቸው አነስተኛ ቆዪ ኢንዱስትሪዎች እጅግ ፈታኝና ውጣ ውረድ የበዛበት ነበር። ለዚህ አለመረጋጋት ደግሞ ዋና ምክንያቶች የሚከተሉት ነበሩ፦

የጦዘ እና ሪከርድ የሰበረ የቡና ዋጋ ንረት፣

በሚያዝያ 2025 በብራዚል ቡና ላይ የተጣለው የ50% የአሜሪካ ታሪፍ፣

የዓለም አቀፍ ንግድን ያወከ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት፣ እንዲሁም
ከዋና ዋና አምራች አገራት የሚመጣው አቅርቦት መቀነስ።

ምንም እንኳን ቡናው ከታሪፍ ነፃ ቢደረግም፣ የተፈጠረው ድንጋጤ ግን የንግድ ምንጭ አሰባሰብ ስልቶችን ሙሉ በሙሉ እንዲቀየሩ አድርጓል።

🤝 የጥብቅ ግንኙነት አስፈላጊነት/ Strategic and strong partnership
በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ወቅት በቆዪዎች፣ በአልሚዎች፣ ላኪዎች እና በአምራች ገበሬዎች መካከል ያለው የረጅም ጊዜ አጋርነት ከምንጊዜውም በላይ ወሳኝ ይሆናል። በመተማመን፣ በግልጽነት እና በመረጃ ልውውጥ ላይ የተገነባ ግንኙነት፤ ገበያው በሚዋዥቅበት ወቅት እንኳ ድርጅቶች በአስተማማኝ መሠረት ላይ እንዲቆሙ፣ አቅርቦት እንዲያገኙ፣ ጥራትን እንዲጠብቁ እና ስጋቶችን እንዲቀንሱ ይረዳቸዋል። የአቅርቦት ሰንሰለቱ ሲወጣጠርና ዋጋ ሲንር፣ እነዚህ የቆዩ ጥብቅ ግንኙነቶች የንግድ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲቀጥል ያደርጋሉ። በተለይ ጥራት፣ ጥራት፣ ጥራት።

📉 በ2026 የሚታዩ አዳዲስ ዕድሎች
ወደ 2026 ስንገባ ገበያው እንደ ዓለም አቀፉ የቡና ድርጅት (ICO) ጥር 2026 ሪፖርት፦
የቡና ገበያ ዋጋ (C market) ከነሐሴ 2025 ወዲህ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ ደርሷል፣
በብራዚል የታየው የተሻለ የአየር ሁኔታ የዓለም አቅርቦት ገበያውን ሰፊ የአቅርቦት መጠን እንዲኖረው አድርጎታል። ነገር ግን ደግሞ ይህን ለውጥ ለበጎ ነው ብሎ መቀበል የብልሆች ምርጫ ነው። በንግድ አለም ብዙ ጊዜ ማትረፍ እንዳለ ሁሉ አንዳንዴ ደግሞ ትንሽ ትርፍ አልያም ደግሞ በዋና መሸጥ፣ እልፍ ካለም በጥቂት ኪሳራ መሸጥ ይጠበቃል። ይህ ተፈጥሯዊ፤ ያለ፣ የነበረ ወደ ፊትም የሚኖር የንግድ ዑደት ነው።
ይህ ለውጥ ድርጅቶች ወጪያቸውን እንዲያመጣጥኑ፣ በመረጃ ላይ የተመሠረተ የብልህ አካሄድ እንዲኖራቸው እና የረጅም ጊዜ የቡና ምንጭ ስልቶችን እንዲያቅዱ አዲስ በር ከፍቷል። ቀደም ብለው በአቅርቦት ሰንሰለቱ ውስጥ ጠንካራ አጋርነት የፈጠሩ ኩባንያዎች፣ ገበያው ወደ መረጋጋት ሲመለስ ራሳቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማላመድና ጥራቱን የጠበቀ አቅርቦት ለማረጋገጥ ዝግጁ ያደርጋቸዋል ።

📈 ከኢንዱስትሪው ምን እንማር?
ተለዋዋጭ ገበያዎች የሚያስተምሩን ትልቁ ቁምነገር፦ ቡና ማለት ዋጋ ብቻ ሳይሆን ግንኙነት፣ ግልጽነትና የረጅም ጊዜ መተማመን መሆኑን ነው። በጠንካራ አጋርነት ላይ መዋዕለ ንዋያቸውን ያፈሰሱ ድርጅቶች፣ የቡና ገበያውን የወደፊት ጉዞ በስኬት ለመወጣት የተሻለ ቁመና ላይ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል።

መንግስት የዜጎቹ በተለይም ደግሞ የቡናው ተዋናይ ዘለቄታዊ ኑሮ ያስጨንቀዋል፣ ያሳስበዋል። ለዚህም ነው እስከዛሬ አርሶ አደሩ የተሻለ ኑሮ እንዲኖር፣ ዘርፉም ወደላቀ ደረጃ እንዲደርስ ሌት ተቀን የሚደክመው። ይህ ጥረት ዛሬም፣ ነገም ከነገወዲያም ተጠናክሮ ይቀጥላል። የምርት ዘመኑ መግቢያ ላይ የአለምን የገበያ አዝማሚያ በመመልከት ክቡር የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ እና የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳ/ር ዶ/ር አዱኛ መላ ባለድርሻ አካላትን ሰብስበው የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈው ነበር። በዚህም የገባቸው አብዝተው ተጠቀሙ። አሁንም ብልጥ ከሰራው ስህተት ፈጥኖ ይማራልና የዋጋው ሁኔታ ከዚህም በላይ የከፋ ሁኔታ ላይ ሳይደርስ ቡናን ወደማዕከላዊ ገበያ አቅርቦ ከኪሳራም ሆነ ከተጠያቂነት መዳን ይቻላል። አንድ በዚሁ ዘርፍ የተሰማሩ ወዳጄ ያካፈሉኝን መልዕክት ጠቁሜ ፅሁፌን ላብቃ።
"ባለፈው አመት በዘመኔ አይቼው የማላውቅ ትርፍ አተረፍኩ። ዘንድሮም ያ ይደገማል የሚል ተስፋ ቢኖረኝም የቡና ገበያ የጨዋታ ህግ ተለዋዋጭ መሆኑን ስለማውቅ የበለጠ ከኪሳራ ለመዳን ስል እጄ ላይ የሚገኘውን ምርት አውጥቼ መሸጥ ችያለሁ። በዚህ ፈታኝ ወቅት መንግስት እያቀበለን ላለው መረጃ እና የውይይት መድረኮች የላቀ ክብር እና አድናቆት አለኝ''
የስትራቴጂ ሰነድ ርክክብ ተካሄደ

መጋቢት 04/2018
ኢቡሻባ

በጂ አይ ዜድ ፈንድ አድራጊትና በኬር ኢትዮጵያ አዘጋጅነት ለፍጻሜ የበቃውን የሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ለመከላከል የሚያስችል ስትራቴጂ ሰነድ 500 ኮፒ ሁለቱ አካላት በጋራ በመሆን ለኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስጣን አስረክበዋል፡፡

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አዱኛ ደበላ እንዳሉት ከአውሮፓ ኅብረት ደንብ ጋር በተያያዘ ብዙ ጉዳዮችን የተከናወኑ እንደሆነ ገልጸው ከሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ጋር በተያያዘ የተኬደው ርቀት ውሱን ሆኖ የቆየ ቢሆንም ከዚህ ስትራቴጂ ሰነድ ጋር በተያያዘ በተደረገው ጥረት ግን ብዙ ስራዎች እንደተከናወኑና ይህ ወሳኝ ሰነድም ግንዛቤን ከማስጨበጥ ባሻገር ብዝበዛውን ለመከላከል በሚደረግ ጥረት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ለዚህም በስራው የተሳተፉትን ጂ አይ ዜድን፣ ኬር ኢትዮጵያን፣ የተቋሙ ስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞችን አመስግነዋል፤ በቀጣይም ይህን ሰነድ ለተፈጻሚነቱ የሚመለከተው አካል መረባረብ እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡

ከዚሁ ርዕሰ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ባለስልጣን መስሪያቤቱ ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት፣ ከዓለማቀፍ የስራ ድርጅት እና ኢፌዴሪ ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከአውሮፓው ደንብ ጋር ተያይዞ ከዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ሕጎች አንጻር ስለ ሕጻናት ጉልበት ብዝበዛ ለቡናው ሴክተር አልሚዎች፣ የኢንዱስትሪ ባለቤቶች እና ላኪዎች በአዲስ አበባ፣ ሐዋሳ እና ጅማ ስለጠናዎችን አንደሰጠ ይታወሳል፡፡
አሸናፊ ጌታሁን ዘግቦታል