በጉጂ ዞን የቡና ልማትን ለማሳደግ የተያዘውን ዕቅድ ማሳካት የሚያስችሉ የቡና ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
በጉጂ ዞን የቡና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የቡናና ሻይ ልማት ባለሙያ ብርሀኑ ፈይሳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ዓመት የዞኑን የቡና ልማት ማሳደግ የሚያስችሉ ከ61 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።
ባለፉት ሰባት ወራትም ከ70 ሚሊየን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን በማዘጋጀት ከእቅድ በላይ መፈፀም መቻሉን አብራርተዋል።
የተዘጋጁት ችግኞች በመጪው ክረምት የሚተከሉ ሲሆን የተሻሻሉና የቡና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በጉጂ ዞን የቡና ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ችግኞች መዘጋጀታቸውን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በጽህፈት ቤቱ የቡናና ሻይ ልማት ባለሙያ ብርሀኑ ፈይሳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ በዘንድሮው ዓመት የዞኑን የቡና ልማት ማሳደግ የሚያስችሉ ከ61 ሚሊየን በላይ ችግኞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ ወደ ስራ ተገብቷል።
ባለፉት ሰባት ወራትም ከ70 ሚሊየን በላይ የተሻሻሉ የቡና ችግኞችን በማዘጋጀት ከእቅድ በላይ መፈፀም መቻሉን አብራርተዋል።
የተዘጋጁት ችግኞች በመጪው ክረምት የሚተከሉ ሲሆን የተሻሻሉና የቡና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ መሆናቸውን አመልክተዋል።
በሲዳማ ክልል የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች ለተከላ ተዘጋጅተዋል
በሲዳማ ክልል የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከተለያዩ የግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡
ለመጪው ክረምት የሚተከሉ ከ34 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች መዘጋጀታቸውንም አስታውቀዋል፡፡
ችግኞቹ የተዘጋጁት በክልሉ መንግስት፣ በማህበራት፣ በግል ባለሃብቶች እና 15ሺህ በሚጠጉ አርሶ አደሮች አማካኝነት መሆኑንም ገልጸዋል፡:
በሲዳማ ክልል የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ከተለያዩ የግብርና ምርምር ማዕከላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡
ለመጪው ክረምት የሚተከሉ ከ34 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ የተሻሻለ ዝርያ ያላቸው የቡና ችግኞች መዘጋጀታቸውንም አስታውቀዋል፡፡
ችግኞቹ የተዘጋጁት በክልሉ መንግስት፣ በማህበራት፣ በግል ባለሃብቶች እና 15ሺህ በሚጠጉ አርሶ አደሮች አማካኝነት መሆኑንም ገልጸዋል፡:
በኦሮሚያ ክልል የተሻሻሉና የአካባቢን ስነ-ምህዳር ታሳቢ ያደረጉ የቡና ችግኞች ይተከላሉ
በኦሮሚያ ክልል የተሻሻሉና የአካባቢን ስነ-ምህዳር ታሳቢ ያደረጉ የቡና ችግኞች እንደሚተከሉ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትልና የቡናና ፍራፍሬ ዘርፍ አስተባባሪ መሐመድሳኒ አሚን ገለጹ።
አቶ መሐመድሳኒ አሚን በክልሉ ባለፉት ዓመታት የቡና ምርት እና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች ሲናወኑ መቆየታቸውንና በተያዘው የበልግ የዝናብ ወቅት የተዘጋጁ የቡና ችግኞችን ከ300ሺህ በሄክታር በሚበልጥ አዲስ መሬት ላይ ይለማሉ ብለዋል።
የቡና ዝርያዎቹ ከግብርና ምርምር ተቋማት የተለቀቁ እንዲሁም የአካባቢን ስነ-ምህዳር ከግምት ያስገቡ እና የተሻለ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውንም ለኢዜአ ገልጸዋል።
ስራውን ስኬታማ ለማድረግ በየደረጃው ከሚገኙ የግብርና ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል።
በክልሉ ባሌ ዞን የቡና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ሙአዊያ ፉአድ ናቸው።
ከግብርና ምርምር ማዕከላት የወጡ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በስፋት መትከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
እነዚህን ዝርያዎች በመጠቀም ባለፉት ሰባት ወራት በወረዳዎቹ በተደረገው እንቅስቃሴ ከ41 ሚሊየን በላይ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ያላቸው ችግኞች ማዘጋጀት መቻሉን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት በዞኑ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የቡና ችግኝ ተከላ መጀመሩን ገልጸው በዚህም 5ሺህ 700 ሔክታር አዲስ መሬት እንደሚለማ አስታውቀዋል።
በልማቱም ከ20 ሺህ በላይ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ጠቁመው የቡና ችግኝ ተከላውም ከአዲስ መሬት በተጨማሪ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ተክሎችን በመንቀል ጭምር በምትኩ ተከላው እንደሚካሄድ አመልክተዋል።
በኦሮሚያ ክልል የተሻሻሉና የአካባቢን ስነ-ምህዳር ታሳቢ ያደረጉ የቡና ችግኞች እንደሚተከሉ የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትልና የቡናና ፍራፍሬ ዘርፍ አስተባባሪ መሐመድሳኒ አሚን ገለጹ።
አቶ መሐመድሳኒ አሚን በክልሉ ባለፉት ዓመታት የቡና ምርት እና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ስራዎች ሲናወኑ መቆየታቸውንና በተያዘው የበልግ የዝናብ ወቅት የተዘጋጁ የቡና ችግኞችን ከ300ሺህ በሄክታር በሚበልጥ አዲስ መሬት ላይ ይለማሉ ብለዋል።
የቡና ዝርያዎቹ ከግብርና ምርምር ተቋማት የተለቀቁ እንዲሁም የአካባቢን ስነ-ምህዳር ከግምት ያስገቡ እና የተሻለ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውንም ለኢዜአ ገልጸዋል።
ስራውን ስኬታማ ለማድረግ በየደረጃው ከሚገኙ የግብርና ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም አንስተዋል።
በክልሉ ባሌ ዞን የቡና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ሙአዊያ ፉአድ ናቸው።
ከግብርና ምርምር ማዕከላት የወጡ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን በስፋት መትከል የሚያስችሉ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
እነዚህን ዝርያዎች በመጠቀም ባለፉት ሰባት ወራት በወረዳዎቹ በተደረገው እንቅስቃሴ ከ41 ሚሊየን በላይ የተሻሻሉ የቡና ዝርያ ያላቸው ችግኞች ማዘጋጀት መቻሉን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት በዞኑ እየጣለ ያለውን የበልግ ዝናብ በመጠቀም የቡና ችግኝ ተከላ መጀመሩን ገልጸው በዚህም 5ሺህ 700 ሔክታር አዲስ መሬት እንደሚለማ አስታውቀዋል።
በልማቱም ከ20 ሺህ በላይ አርሶና ከፊል አርብቶ አደሮች እየተሳተፉ መሆኑን ጠቁመው የቡና ችግኝ ተከላውም ከአዲስ መሬት በተጨማሪ ያረጁና ከምርት ውጭ የሆኑ የቡና ተክሎችን በመንቀል ጭምር በምትኩ ተከላው እንደሚካሄድ አመልክተዋል።
ቡና ስልጠና ማዕከሉ ውጤታማነትና ያስገኛቸው ጠቀሜታዎች ላይ ጥናት ቀረበ
መጋቢት 01/2018 ዓ.ም
ኢቡሻባ፤
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በቡና ስልጠና ማዕከሉ ውጤታማነትና ያስገኛቸው ጠቀሜታዎች ላይ አበራ ፈይሳ የማማከር አገልግሎት በተባለ የግል ድርጅት ያስጠናውን ጥናት ለሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት እዲቀርብ አድርጓል፡፡
ጥናቱ በማዕከሉ በማሰልጠኛ ሞጁሎች ይዘት፣ የስልጠና አሰጣጥ፣ አቃፊነት፣ የስልጠና ክለጊዜያት በቂነትን ተመልክቷል፡፡
ከሞጁሎች ይዘት አንጻር 90 በመቶ አሰልጣኞች በጣም ጥሩ እንደሆነ፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ የጠበቁ እንደሆኑና ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ፍላጎት የሚያሟሉ ናቸው እንደሆኑ ጥናቱ አሳይቷል፡፡
ከስልጠና አሰጣጥ ጥራት አንጻር በተዳሰሰው ክፍል ደግሞ 76 በመቶ የሚሆኑ አሰልጣኞችና 70 በመቶ የሚሆኑ ሰልጣኞች መልካምና ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና ሂደት እንዳለ ተናግረዋል፡፡ ከስልጠና ክፍለጊዜ አንጻር ግን የንድፈ ሃሳቡንም የተግባር ስልጠናዎችንም በበቂ ሁኔታ ለመስጠት በቂ ጊዜ እንዳልተሰጠ ጥናቱ አስቀምጧል፡፡
ጥናቱ የማዕከሉን ውጤታማነትና ተጽእኖ በተመለከተ ስልጠና በሚሰጥባቸው የቡና ዘርፎች ያለው የቡና ሴክተር የአፈጻጸም ትክክለኝነት፣ ዓላም አቀፍ የቡና ገዢዎች ጋር ያለው ተግባቦት፣ የሰለጠነው የሰው ሃይል በራስ መተማመንና ውሳኔ ሰጪነት እንጨመረ አሳይቷል፡፡
እነዚህንም በመካን 22 በመቶ የሚሆኑት ሰልጣኞች የራሳቸውን የንግድ ስራ እንደከፈቱ እና 10 በመቶ የሚሆኑ ሴት ሰልጣኞች ኢንተርፕረኑር ወደ መሆን ደረጃ እንደደረሱ የተወሳ ሲሆን 13 በመቶ ነባር የቡና ንግድ ስራዎች ማስፋፋት እንደታየባቸው የጥናቱ ውጤት ያሳያል፡፡
በአጠቃላይ እሴት ጭመራ ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የገቢ መሻሻል፣ በገበያ ተወዳዳሪነትን በማስፈን ረገድ የማዕከሉ አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነና እንደሚሆን ተመላክቷል፡፡
መሻሻል እና መታከል ያለባቸውንም ጎኖችንም ጥናቱ ተመልክቷል፡፡ በዚህም መሠረት የስልጠና ፍላጎትና የማዕከሉ አቅም አለመመጣጠን፣ የስልጠና ማቴሪያሎች በበቂ ሁኔታ አለመኖር፣ የአሰልጣኞች የተግባቦት ክህሎት ውሱንነት፣ ውስን የሆኑት ስልጠናዎች ላይ ብቻ የሰልጣኝ ብዛት መኖር፣ የማዕከሉ የቦታ ስፋት ጥበት፣ የጥራት ሰርቲፊኬት ሰጪነት ማንዴት አለመለየት የመሳሰሉትን ጥናቱ ለይቷል፡፡
በቀጣይ መደረግ ያለባቸውንም ሲያወሳ የአየር ንብረት ለውጥ እና ኢንተርፕሬነር የመሳሰሉ ስልጠናዎች ቢካተቱ፣ ስልጠና አሰጣጡ ዲጂታላይዝ ቢሆን፣ ማዕከሉ ወደቡና አብቃይ አካባቢዎች ቢስፋፋ፣ ከሚመለከታቸው የክልልና ዓለም አቀፍ የግልና የመንግስት ድርጅቶች ጋር በቅንጅት መስራት የሚሉትን ጥናቱ እንደመፍትሄ ሃሳብ አቅርቧል፡፡
ጥናቱ ሲቀርብ በቦታው የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አዱኛ ደበላ ባለሰልጣኑ ጥናቱን ያስጠናው የማዕከሉን ጥራት ለማሻሻል ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ጠንካራዎቹን በማጠናከር ደካማ ጎኖችን በመቅረፍ የተሻለ ማሰልጠኛ ተቋም ለማድረግ በማለም እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ማዕከሉን ወደቡና አብቃይ ክልሎች ከማስፋት አንጻር ስራው እንደተጀመረና በጅማ ዞን አንድ ማዕከል እንደተከፈ ተናግረዋል፡፡
በማቴሪያል ከማሟላት አንጻር የሀገር ውስጥም የውጪም አጋርና ባለድርሻ አካላትን በማነጋገር በርካታ የቁሳቁስ እገዛዎችን ማግኘት እንደተቻለና በዚህም በቅንጅት የመስራቱን ተግባር ባለስልጣኑ አስቀድሞም የሄደበት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አሸናፊ ጌታሁን እንደዘገበው
መጋቢት 01/2018 ዓ.ም
ኢቡሻባ፤
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በቡና ስልጠና ማዕከሉ ውጤታማነትና ያስገኛቸው ጠቀሜታዎች ላይ አበራ ፈይሳ የማማከር አገልግሎት በተባለ የግል ድርጅት ያስጠናውን ጥናት ለሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት እዲቀርብ አድርጓል፡፡
ጥናቱ በማዕከሉ በማሰልጠኛ ሞጁሎች ይዘት፣ የስልጠና አሰጣጥ፣ አቃፊነት፣ የስልጠና ክለጊዜያት በቂነትን ተመልክቷል፡፡
ከሞጁሎች ይዘት አንጻር 90 በመቶ አሰልጣኞች በጣም ጥሩ እንደሆነ፣ ዓለማቀፍ ስታንዳርድ የጠበቁ እንደሆኑና ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ፍላጎት የሚያሟሉ ናቸው እንደሆኑ ጥናቱ አሳይቷል፡፡
ከስልጠና አሰጣጥ ጥራት አንጻር በተዳሰሰው ክፍል ደግሞ 76 በመቶ የሚሆኑ አሰልጣኞችና 70 በመቶ የሚሆኑ ሰልጣኞች መልካምና ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና ሂደት እንዳለ ተናግረዋል፡፡ ከስልጠና ክፍለጊዜ አንጻር ግን የንድፈ ሃሳቡንም የተግባር ስልጠናዎችንም በበቂ ሁኔታ ለመስጠት በቂ ጊዜ እንዳልተሰጠ ጥናቱ አስቀምጧል፡፡
ጥናቱ የማዕከሉን ውጤታማነትና ተጽእኖ በተመለከተ ስልጠና በሚሰጥባቸው የቡና ዘርፎች ያለው የቡና ሴክተር የአፈጻጸም ትክክለኝነት፣ ዓላም አቀፍ የቡና ገዢዎች ጋር ያለው ተግባቦት፣ የሰለጠነው የሰው ሃይል በራስ መተማመንና ውሳኔ ሰጪነት እንጨመረ አሳይቷል፡፡
እነዚህንም በመካን 22 በመቶ የሚሆኑት ሰልጣኞች የራሳቸውን የንግድ ስራ እንደከፈቱ እና 10 በመቶ የሚሆኑ ሴት ሰልጣኞች ኢንተርፕረኑር ወደ መሆን ደረጃ እንደደረሱ የተወሳ ሲሆን 13 በመቶ ነባር የቡና ንግድ ስራዎች ማስፋፋት እንደታየባቸው የጥናቱ ውጤት ያሳያል፡፡
በአጠቃላይ እሴት ጭመራ ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይል፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የገቢ መሻሻል፣ በገበያ ተወዳዳሪነትን በማስፈን ረገድ የማዕከሉ አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነና እንደሚሆን ተመላክቷል፡፡
መሻሻል እና መታከል ያለባቸውንም ጎኖችንም ጥናቱ ተመልክቷል፡፡ በዚህም መሠረት የስልጠና ፍላጎትና የማዕከሉ አቅም አለመመጣጠን፣ የስልጠና ማቴሪያሎች በበቂ ሁኔታ አለመኖር፣ የአሰልጣኞች የተግባቦት ክህሎት ውሱንነት፣ ውስን የሆኑት ስልጠናዎች ላይ ብቻ የሰልጣኝ ብዛት መኖር፣ የማዕከሉ የቦታ ስፋት ጥበት፣ የጥራት ሰርቲፊኬት ሰጪነት ማንዴት አለመለየት የመሳሰሉትን ጥናቱ ለይቷል፡፡
በቀጣይ መደረግ ያለባቸውንም ሲያወሳ የአየር ንብረት ለውጥ እና ኢንተርፕሬነር የመሳሰሉ ስልጠናዎች ቢካተቱ፣ ስልጠና አሰጣጡ ዲጂታላይዝ ቢሆን፣ ማዕከሉ ወደቡና አብቃይ አካባቢዎች ቢስፋፋ፣ ከሚመለከታቸው የክልልና ዓለም አቀፍ የግልና የመንግስት ድርጅቶች ጋር በቅንጅት መስራት የሚሉትን ጥናቱ እንደመፍትሄ ሃሳብ አቅርቧል፡፡
ጥናቱ ሲቀርብ በቦታው የተገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር አዱኛ ደበላ ባለሰልጣኑ ጥናቱን ያስጠናው የማዕከሉን ጥራት ለማሻሻል ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት ጠንካራዎቹን በማጠናከር ደካማ ጎኖችን በመቅረፍ የተሻለ ማሰልጠኛ ተቋም ለማድረግ በማለም እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ማዕከሉን ወደቡና አብቃይ ክልሎች ከማስፋት አንጻር ስራው እንደተጀመረና በጅማ ዞን አንድ ማዕከል እንደተከፈ ተናግረዋል፡፡
በማቴሪያል ከማሟላት አንጻር የሀገር ውስጥም የውጪም አጋርና ባለድርሻ አካላትን በማነጋገር በርካታ የቁሳቁስ እገዛዎችን ማግኘት እንደተቻለና በዚህም በቅንጅት የመስራቱን ተግባር ባለስልጣኑ አስቀድሞም የሄደበት ጉዳይ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አሸናፊ ጌታሁን እንደዘገበው