Ethiopian Coffee and Tea Authority
5.72K subscribers
5.48K photos
30 videos
66 files
358 links
Ethiopian Coffee and Tea Authority
Download Telegram

‎በደቡብ ቤንች ወረዳ የኮረሪማ ቅመም ልማት በከፊል (በምስል)


ምስል፡ የቤንች ሸኮ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን
ጥር 22/2018

ወደ አውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት የሚላክ ቡና ደን ሳይመነጠር የተመረተ እንደሆነ አረጋግጦ የመላክ ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጀመራል ተባለ።

ህብረቱ ወደ አባል ሀገራቱ የሚላክ የግብርና ምርት ከደን ምንጣሮ ነፃ መሆን እንዳለበት የሚያስገድደውን ህግ ከአንድ ዓመት በኋላ ስራ ላይ ማዋል እንደሚጀምር ማሳወቁ ይታወሳል።

የአውሮፓ ህብረት በተለይ በታዳጊ ሀገራት የተመረቱ ዘጠኝ የግብርና ምርቶች ወደ አባል ሀገራቱ መግባት የሚችሉት፤ ከደን ምንጣሮ ነፃ በሆነ መሬት ላይ ተዘርተው የበቀሉ ከሆነ እና ለዚህም ማረጋገጫ ሲያቀርቡ ብቻ እንደሚሆን በመጥቀስ ይህንኑ የተመለከተ የሚል ህግ አውጥቷል።

በዚህ ክልከላ ውስጥ ከተካተቱ የግብርና ምርቶች ኢትዮጵያን የሚመለከተቱት ቡና እና አኩሪ አተር መሆናቸውን ሠምተናል።

ህጉ ከባለፈው ወር አንስቶ ስራ ላይ ይውላል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ተግባራዊ የሚሆንበት ጊዜ በአንድ ዓመት ተራዝሟል።

ኢትዮጵያም በተሰጠው አንድ ዓመት ጊዜ ወደ ህብረቱ የምትልከው ቡና ደን ሳይመነጠር የተመረተ እንደሆነ እያረጋገጠች ምስክር ወረቀት ለማዘጋጀት እየሰራች እንደምትገኝ ተጠቅሷል።

አሁን ላይ እያንዳንዱ የቡና እርሻ መሬት ወደ መረጃ ቋት እየገባ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ቡና ፤ ሻይ እና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ፤ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የልማት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ተጋይ ኑሩ ነግረውናል።

በኢትዮጵያ ከሚመረተው ቡና ከ90 በመቶ በላዩ ከአርሶ አደሮች የሚገኝ እንደሆነ አቶ ታጋይ ተናግረዋል።

አርሶ አደሮቹ ቡናውን የሚያመረቱበት መሬት ስፋት እጅግ አነስተኛ እና የተበጣጠሰ በመሆኑ የመረጃ ማሰባሰቡን ስራ ከባድ ያደርገዋል ብለዋል።

የተራዘመውን የአንድ ዓመት ጊዜ በመጠቀም ግን የሁሉንም አርሶ አደሮች መሬት ወደ መረጃ ቋት በማስገባት ቡናቸው ደን ሳይመነጠር የተመረተ እንደሆነ የሚያረጋግጠውን የምስክር ወረቀት መስጠት እንደሚጀመር ነግረውናል።

የአውሮፓ ህብረት ያወጣው ህግ የቡና አመራረት ከህጻናት ጉልበት ብዝበዛ ነፃ ሊሆን ይገባዋል የሚል ድንጋጌንም ያካተተ እንደሆነ ተነግሯል።

ይህንንም የማረጋገጥ ማስረጃ ለማቅረብ የኢትዮጵያ ቡና ፤ ሻይ እና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ከሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር እየሰራሁ ነው ብሏል።

ሸገር ኤፍ ኤም
በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቡና ማሰልጠኛ ማዕከል occupational Standard ሰነድ በተዘጋጀበት ወቅት
ጥር 23/2018 ዓ.ም
አዳማ
የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ የቱሪዝም አቅም በመጠቀም ሀገሪቷን የዘርፉ የስበት ማዕከል ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

ሀዋሳ፤ ጥር 23/2018

የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ የቱሪዝም አቅም በመጠቀም ሀገሪቷን የዘርፉ የስበት ማዕከል ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተመላከተ።

የቱሪዝም ሚኒስቴር የኢትዮጵያን ቡና ለቱሪዝም መዳረሻነት ለማዋል የሚያስችሉ ስራዎችን ለማጠናከር ያዘጋጀው ሀገር አቀፍ የቡና ቱሪዝም ሴሚናርና የመስክ ምልከታ በሲዳማ ክልል ተካሄዷል።

በሚኒስቴሩ የቱሪዝም መስህብ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሳ ከድር እንደገለጹት የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ የቱሪዝም አቅም በመጠቀም ሀገሪቷን የዘርፉ የስበት ማዕከል ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል።

የተጀመሩ ትልልቅ የቱሪዝም ስራዎችን ለማጠናከር የፖሊሲ አቅጣጫ፣ የተቀናጀ ትብብርና ስልት ተነድፎ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አውስተው እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶችን ለማስቀጠል ያሉ ሀብቶችን የመለየትና የመጠቀም ስራ ይሰራል ብለዋል።

እንዲሁም አዳዲስ ያልተዳሰሱ ዘርፎችና ዕምቅ አቅሞች የመለየት ስራ እየተሰራ መሆኑን አንስተው ከዚህ ውስጥ አንዱ ቡናን በተለየ አቀራረብ ለቱሪዝም መዳረሻነት ለማዋል የሚያስችል ስራ መጀመሩን ተናግረዋል።

የቡና መገኛ በመሆናችን ከባህልና ታሪክ ጋር ያለንን ማህበረሰባዊ ትስስር እንዲሁም የምርት ሂደቱ ከእርሻ እስከ ቅምሻ ድረስ ያለውን ሂደት በተቀናጀ መንገድ ለቱሪዝም መዳረሻነት ለማዋል በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የሲዳማ ክልል ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የቱሪስት መስህብና መዳረሻ ልማት ዳይሬክተር አቶ ካሳ መንገሻ በበኩላቸው የክልሉ የቡና ልማት ለቱሪዝም መዳረሻነት አማራጭ አቅም መሆኑን ተናግረዋል።

ምንጭ ኢዜአ
The third African Coffee Week 2026 and Inter-African Coffee Organization (IACO) meetings have officially opened in Addis Ababa, Ethiopia.

2, February, 2026
ADDIS ABABA, Ethiopia –

The third African Coffee Week and Inter-African Coffee Organization (IACO) meetings have officially opened in the Skylight Hotel here in Addis Ababa today. This High-Level Policy Forum is being held under the theme: “Advancing Climate Resilience & the Transformation of the African Coffee Sector” which is Organized by the Inter-African Coffee Organization (IACO)—the African Union’s specialized agency for coffee—in collaboration with UNIDO.

This year's event is the third consecutive partnership between the African Fine Coffees Association (AFCA) and IACO, designed to bring together ministers, ambassadors, producers, policymakers, researchers, and global traders to strengthen the continent's coffee value chain.

During an opening session, Dr. Meles Mekonnen, State Minister of MoA stated that, the future of coffee is African, but that future will not build itself. It requires bold leadership, coordinated policies, public private partnerships and targeted investment. Let us leave this Forum not with declarations, but with commitments, not with promises, but with partnerships. Ethiopia stands ready to work with IACO-AU, Member States, AFCA, and all stakeholders to turn vision into action. Together, we can build a coffee sector that is climate-resilient, economically vibrant, socially inclusive, and globally competitive.

Ato Shafi Oumer, Deputy Director General of the Ethiopian Coffee and Tea Authority in his part said that, As Ethiopia is the birthplace of coffee, this commodity is far more than an economic crop, it is a cultural symbol and a pillar of the nation’s economy.
According to him, Investment in the African coffee industry is necessary to maximize the benefits of the sector. Value addition is also needed to create more opportunities for African coffee in the international market. This will help to create job opportunities for many unemployed Africans. African countries should work together for this. Forums involving such leaders will create the capacity of coffee-producing countries to address the challenges encounter the sector and seize the opportunities that exist.
Moreover, he added that, the need for massive transformation of African coffee sector, it needs a unified approach where all the stakeholders are united under one platform and work together to maximize the benefits of this untapped resource and invest in the African coffee industry to support local farmers' livelihoods. IACO’s collective commitment has also a crucial step to bring the growth and transformation of Africa's coffee sector.

The High-Level Policy Forum is anchored in the ACT Programme (Advancing Climate-Resilience and Transformation of the African Coffee Sector), a continental framework structured around five key pillars: Climate resilience, Value addition and industrial transformation, Compliance with international market standards, Research, innovation, and knowledge sharing, Social inclusion and sustainable livelihoods.
Panel discussions are also part of this great event. In Day One discussions focused on five outcome-oriented policy panels, each aimed at producing actionable recommendations and investment pathways.

Sahlemariam G/medhin Reported.
22ኛው የAFCA ኤግዚቢሽንና ኮንፈረንስ እንዲሁም 3ኛው የአፍሪካ ቡና ሳምንት በይፋ ተከፍቶ በመካሄድ ላይ ይገኛል

ጥር 28/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

የሁነቱ የክብር እንግዳ የግብርና ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር መለስ መኮንን፣ የዓለም አቀፍ የቡና ድርጅት ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ቬኑሲያ ንግዌሮ፣ የAFCA ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ጊልበርት ጋታሊ፣ የኢትዮጵያ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች ክቡር አቶ ሻፊ ዑመር እና ክቡር አቶ ታጋይ ኑሩ እንዲሁም የተለያዩ የቡና ሴክተር አካላት የስራ ኃላፊዎችና የአሀጉሪቱም ከሌላው ዓለምም የተገኙ የቡናው ሴክተር ማኅበረሰብ በተገኙበት 22ኛው የAFCA ኤግዚቢሽንና ኮንፈረንስ እንዲሁም 3ኛው የአፍሪካ ቡና ሳምንት በይፋ ተከፍቶ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመክፈቻ መርሀግብሩ ሚኒስትር ዴኤታው ክቡር ዶ/ር መለስ መኮንን ንግግር ያሰሙ ሲሆን በንግግራቸው ሁነቱ ለቡና ቅምሻ፣ ለልዩ ልዩ ውድድሮች፣ ለእውቀት ሽግግር እና ስልታዊ ትስስር ለመገንባት 2000 የቡናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት ከመላው ዓለም እንደሚሳተፉበት ተናግረዋል። ኮንፈረንሱ ቀጥታ የገበያ ትስስር፣ የቡና ዱካ እና ቀጣይነት ላይ በማተኮር የአፍሪካ ቡና ልህቀትን እንደሚያስተዋውቅ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ የግብርናው ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው ያሉት ሚኒስትር ዲኤታው የእድገት ፖሊሲው ምርታማነትን ለማሳደግ፣ ጥራትን ለመጨመር እሴት ጭመራን ማስፋት፣ አግሮ ፕሮሰሲንግንና ኤክስፖርትን ማጠናከርን ቅድሚያ እንደሚሰጥ አውስተዋል። ዓለማቀፍ የቡና ስፔሻሊቲ፣ የቡና ዘላቂነትና የቡና ዱካ ፍላጎት መጨመር ትልቅ እድልን ለአፍሪካ በተለይም ለፕሪሚየም የአረቢካ ቡና አምራቾች ይዞ እንሚመጣ ገልጸዋል።

ንግግራቸውን ሲቀጥሉም በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ የተጀመረው ግሪን ሌጋሲ ምን ያህል የቡና ልማቱን እንዳፋፋመው ከገለጹ በኋላ ሌጋሲው የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በቀጣይ የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን ምርታማነት ፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተቋቋሚነትንና ዓለማቀፍ ተወዳዳሪነትን የሚያሳድግ ስትራቴጂያዊ ኢንቨስትመንት እንደሆነ አብራርተዋል። ለዚህም እውናዊነት የአፍሪካ የቡናው ሴክተር ትብብር እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።

ይህን ካሉም በኋላ ጥር 28 እና 29 የሚካሄደውን 22ኛውን የአፍሪካ የቡና ኤግዚቢሽንና ኮንፈረንስ እንዲሁም 3ኛው የአፍሪካ ቡና ሳምንት ቀን በይፋ መጀመሩን አብስረዋል፤ ለዝግጅቱም ሚና የተጫወቱ አካላትን አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ሻፊ ዑመር በበኩላቸው እንግዶቻቸውን እንኳን ደህና መጣችሁ ካሉ በኋላ ኢትዮጵያ ኤግዚቢሽኑንና ኮንፈረንሱን አዘጋጅ ሀገር በመሆኗ ክብር እንደሚሰማቸው ገልጸው ሁነቶቹ ኤግዚቢሽኖች፣ ከፍተኛ ደረጃ ያላቸው ኮንፈረንሶችና የቢዝነስ ለቢዝነስ ተሳትፎ የአፍሪካን ቡናን በእጅጉ ለማሳደግ ያለንን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለዋል። ሁነቱም ከአፍሪካና ሌሎች አህጉራት በአምራቾች፣ በገዢዎች፣ በፖሊሲ አዘጋጆች፣ በተመራማሪዎችና በኢንቨስተሮች መካከል ትብብርን በማጠናከር ለውይይት፣ ለአጋርነት፣ ለፈጠራ እንዲሁም ለንግድ ልዩ ዕድል እንደሆነ ተናግረዋል።

የአፍሪካ ፋይን ኮፊ አሶሴሽን ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ሚስተር ጊልበርት ጋታሊም ንግግር አሰምተዋል። በንግግራቸው የዘንድሮው 22ኛው ኤግዚቢሽንና ኮንፈረንስ በአይነቱ ትልቁና ምርጡ ዝግጅት ነው ብለዋል። ድርጅቱም በቡና ኢንዱስትሪው ውስጥ ያሉ ፕሮፌሽናሎችን መምራትና ማነቃቃት ኃላፊነቱ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ በዛሬውና በቀጣዩ ቀን በሁነቱ የሚከናወኑ ተግባራት ማሳያ ይሆናሉ ሲሉ ተናግረዋል።

ከኤግዚቢሽኑና ኮንፈረንሱ ሁነት ጋር በተያያዘ ስለተከናወኑት ተግባራት ሲያወሱም ቴስት ኦፍ ሀርቨስት ክንውን አንዱ ነው ካሉ በኋላ የዘንድሮው ውድድር ወደጫረታ የሚያመራ መሆኑን ልዩ ያደርገዋል ብለዋል። ሌላው የዘንድሮው ሁነት ለየት የሚያደርገውን ሲናገሩ በሁነቱ ከ30 ሀገራት 25 ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉበት ከእስከዛሬው ሰፋ ያለ የባሬስታ ሻምፕዮንሺፕ ውድድር እንደሚካሄድበት አውስተዋል። በመቀጠልም በዘንድሮ ኤግዚቢሽንና ኮንፈረንስ EUDR LEARNING COMMUNITY for AFRICA የሚል ፕሮጀክት የማስጀመር መርሀግብር እንደሚከናወን ተናግረዋል። ሌላው ለየት ያለ ክንውን ሲያሳውቁም ከዓለማቀፉ የቡና ፕላትፎርም ጋር አጋርነት እንደተፈጠረና ድርጅቱ አባል እንደሆነ ገልጸው አጋርነቱ የአፍሪካን እምቅ አቅም ወደተግባር መቀየርን ያለመ ነው ብለዋል። ከአጋርነት ጋር በተያያዘ የተፈጸመው ሌላውን ተግባር ይፋ ሲያደርጉም ከቡና ጥራት ኢንስቲትዩሽን ጋር እንደሆ ተናግረዋል። የዚህ አጋርነትንም ሲገልጹ የአፍሪካን የቡና ጥራት ለማሳደግ ነው ብለዋል።

በወቅቱ የዓለም የቡና ድርጅት ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተርም ንግግር ያሰሙ ሲሆን ሁኑቱ ልምድ መለዋወጫና የቡናው ሴክተር ያሉበት ችግሮች መፍትሄ ማበጃ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል። ችግሮችም እንዳሉ ሁሉ መልካም እድሎችም እንዳሉ ከወሱም በኋላ ለዚህ ተፈጻሚነት መተባበር እንደሚያሻ አጽንኦት ሰጥተዋል። በስመጨረሻም ከደን ምንጣሮና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ ቡና የመፍትሄ እንጂ የችግር አካል አደለም ካሉ በኋላ ወጣቱ ትውልድ በሴክተሩ ውስጥ በስፋት እንዲሳተፍ መክረዋል።

ከቤት ውስጥ መርሀ ግብሩም በኋላ እንግዶቹና ሌሎች ታዳሚዎች በየቡዞቹ በመዘዋወር የቡና አካላቱን ኤግዚቢሽን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

አሸናፊ ጌታሁን እንደዘገበው