ኢትዮጵያ እሴት የተጨመረበት ቡና ለዓለም ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ገቢዋን ለማሳደግ እየሠራች ነው
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018: ኢትዮጵያ ቡናን በጥሬው ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለዓለም ገበያ በማቅረብ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ገለጸ።
ኢትዮጵያ የቡና መገኛና ከአፍሪካ ቀዳሚዋ አምራች ሀገር ስትሆን ቡናን እሴት ጨምሮ ወደ ውጭ በመላክ የተጀመረው ጥረት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው፡፡
ባለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ 470 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች፡፡
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት የ15 ዓመት የቡና ስትራቴጂ ፍኖተ ካርታ ተቀርጾ ወደ ሥራ ተገብቷል።
በዚህም በዘርፉ የነበሩ መዋቅራዊ ችግሮችን በመለየት በምርትና ምርታማነት እንዲሁም በገበያ አድማስ ማስፋት ላይ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡
ምርታማነታቸው ዝቅተኛ የነበሩ ያረጁ የቡና ተክሎችን በመጎንደል የማሳ ላይ ምርታማነትን የማሳደግ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡
በሀገር አቀፉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ታግዞ አዳዲስ የቡና ተክሎች በስፋት መተከላቸውን ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን የምርት መጠን ብቻ ሳይሆን ጥራት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ቡናው በከፍተኛ ጥራት እንዲመረት ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን የግብይት ሰንሰለቱን ማሳጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም ለውጥ እየመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡
ቀደም ሲል የነበረውን የተንዛዛ የገበያ ሥርዓት በፖሊሲ ማሳጠር በመቻሉ ይባክን የነበረውን የምርት መጠን መቀነስና በጥራት ላይ ይፈጠሩ የነበሩ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ማስቀረት መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ካላት የቡና አቅም አንጻር የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ እሴት ጨምሮ ለገበያ የማቅረብ ሥራ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ቀደም ሲል እሴት የተጨመረበት ቡና በምን ዓይነት የጥራት ደረጃና ሁኔታ ወደ ውጭ መላክ እንዳለበት የሚወስኑ ግልጽ መመሪያዎች ባለመኖራቸው ዘርፉ ሳይነቃቃ መቆየቱን አስረድተዋል።
ይህንን ክፍተት በመሙላት ምቹ ሁኔታዎችን የሚፈጥር አዲስ መመሪያ ጸድቆ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመው አዲሱ መመሪያ በሀገር ውስጥ የተቆላና የተፈጨ ቡናን በውጭ ምንዛሬ የመሸጥ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በርካታ የቡና ቆይ ኩባንያዎች ምርቶቻቸውን በኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በትላልቅ ሆቴሎችና በቱሪስት መዳረሻዎች በውጭ ምንዛሬ መሸጥ መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ ጥር 1/2018: ኢትዮጵያ ቡናን በጥሬው ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለዓለም ገበያ በማቅረብ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እየሠራች መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ገለጸ።
ኢትዮጵያ የቡና መገኛና ከአፍሪካ ቀዳሚዋ አምራች ሀገር ስትሆን ቡናን እሴት ጨምሮ ወደ ውጭ በመላክ የተጀመረው ጥረት ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው፡፡
ባለፈው በጀት ዓመት ኢትዮጵያ 470 ሺህ ቶን ቡና ወደ ውጭ በመላክ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች፡፡
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት የ15 ዓመት የቡና ስትራቴጂ ፍኖተ ካርታ ተቀርጾ ወደ ሥራ ተገብቷል።
በዚህም በዘርፉ የነበሩ መዋቅራዊ ችግሮችን በመለየት በምርትና ምርታማነት እንዲሁም በገበያ አድማስ ማስፋት ላይ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡
ምርታማነታቸው ዝቅተኛ የነበሩ ያረጁ የቡና ተክሎችን በመጎንደል የማሳ ላይ ምርታማነትን የማሳደግ ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡
በሀገር አቀፉ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ታግዞ አዳዲስ የቡና ተክሎች በስፋት መተከላቸውን ጠቁመዋል።
በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ ለመሆን የምርት መጠን ብቻ ሳይሆን ጥራት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው ቡናው በከፍተኛ ጥራት እንዲመረት ጥብቅ ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ምርታማነትን ከማሳደግ ጎን ለጎን የግብይት ሰንሰለቱን ማሳጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ሆኖ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዚህም ለውጥ እየመጣ ይገኛል ብለዋል፡፡
ቀደም ሲል የነበረውን የተንዛዛ የገበያ ሥርዓት በፖሊሲ ማሳጠር በመቻሉ ይባክን የነበረውን የምርት መጠን መቀነስና በጥራት ላይ ይፈጠሩ የነበሩ አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ማስቀረት መቻሉንም ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያ ካላት የቡና አቅም አንጻር የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ እሴት ጨምሮ ለገበያ የማቅረብ ሥራ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ቀደም ሲል እሴት የተጨመረበት ቡና በምን ዓይነት የጥራት ደረጃና ሁኔታ ወደ ውጭ መላክ እንዳለበት የሚወስኑ ግልጽ መመሪያዎች ባለመኖራቸው ዘርፉ ሳይነቃቃ መቆየቱን አስረድተዋል።
ይህንን ክፍተት በመሙላት ምቹ ሁኔታዎችን የሚፈጥር አዲስ መመሪያ ጸድቆ ወደ ሥራ መገባቱን ጠቁመው አዲሱ መመሪያ በሀገር ውስጥ የተቆላና የተፈጨ ቡናን በውጭ ምንዛሬ የመሸጥ ዕድል መፍጠሩን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በርካታ የቡና ቆይ ኩባንያዎች ምርቶቻቸውን በኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በትላልቅ ሆቴሎችና በቱሪስት መዳረሻዎች በውጭ ምንዛሬ መሸጥ መጀመራቸውን ጠቁመዋል፡፡
በቡና ገበያው ተወዳዳሪ ለመሆን ...
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም አቀፍ የቡና ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቆየት በምርት ጥራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው አሉ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ዑመር፡፡
በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የቻይና-ኢትዮጵያ የቡና ኢኮኖሚ እና ንግድ ትብብር ኮንፈረንስ በቻይና ሁናን ግዛት ጁጆ ከተማ በታሕሣሥ ወር ውስጥ መካሄዱ ይታወሳል።
በቻይና ውስጥ የኢትዮጵያ የቡና ምርት ተፈላጊነት እየጨመረ መምጣት የሁለቱን ሀገራት ትስስር በማጠናከር ረገድ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
የቻይና ገበያ ለኢትዮጵያ ቡና ያለው ፍላጎት እያደገ መምጣቱ ለኢትዮጵያ ትልቅ ዕድል በመሆኑ የምርት ጥራትና ብዛትን ማስጠበቅ እንደሚገባ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ቡናን ቻይናን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ፣ ገበያ ለመፈለግና ወጪ ንግዱን ለማሳደግ ታልሞ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሻፊ ኡመር፤ ለዚህም ሁለት ስትራቴጂዎች ተነድፈው እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የመጀመሪያው ስትራቴጂ ወደ አዳዲስ ገበያ መግባት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በነባሩ ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ መቆየት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
የቡና ጥራት ላይ ትኩረት ማድረግ የኢትዮጵያ ቡና ተፈላጊ እንዲሆን ያስችለዋል በማለት ገልጸው፤ ይህም አዳዲስ ገበያዎች ውስጥ ለመግባት እና ነባር ገበያ ውስጥ ደግሞ ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቆየት ያግዛል ብለዋል፡፡
እስካሁን የቡና ጥራትን ለማስጠበቅ በተከናወኑ ተግባራት የቡና ምርት መዳረሻ ሀገራትን ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በ2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ 64 ለሚሆኑ ሀገራት የቡና ምርቷን ትልክ እንደነበር ጠቅሰው፤ አሁን ላይ የቡና ምርታችን መዳረሻ ሀገራትን ቁጥር ወደ 84 ከፍ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
በሁለት ዓመታት ውስጥ የተፈጠሩት 20 አዳዲስ የቡና ገበያ መዳረሻዎች ከተለመደው አካሂድ በመውጣት ቡናን በአዲስ መልክ ለመላክ የተደረገው ጥረት ውጤት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም አቀፍ የቡና ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቆየት በምርት ጥራት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው አሉ የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሻፊ ዑመር፡፡
በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የቻይና-ኢትዮጵያ የቡና ኢኮኖሚ እና ንግድ ትብብር ኮንፈረንስ በቻይና ሁናን ግዛት ጁጆ ከተማ በታሕሣሥ ወር ውስጥ መካሄዱ ይታወሳል።
በቻይና ውስጥ የኢትዮጵያ የቡና ምርት ተፈላጊነት እየጨመረ መምጣት የሁለቱን ሀገራት ትስስር በማጠናከር ረገድ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
የቻይና ገበያ ለኢትዮጵያ ቡና ያለው ፍላጎት እያደገ መምጣቱ ለኢትዮጵያ ትልቅ ዕድል በመሆኑ የምርት ጥራትና ብዛትን ማስጠበቅ እንደሚገባ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ቡናን ቻይናን ጨምሮ በተለያዩ ሀገራት ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ፣ ገበያ ለመፈለግና ወጪ ንግዱን ለማሳደግ ታልሞ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ ሻፊ ኡመር፤ ለዚህም ሁለት ስትራቴጂዎች ተነድፈው እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
የመጀመሪያው ስትራቴጂ ወደ አዳዲስ ገበያ መግባት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በነባሩ ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ መቆየት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
የቡና ጥራት ላይ ትኩረት ማድረግ የኢትዮጵያ ቡና ተፈላጊ እንዲሆን ያስችለዋል በማለት ገልጸው፤ ይህም አዳዲስ ገበያዎች ውስጥ ለመግባት እና ነባር ገበያ ውስጥ ደግሞ ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቆየት ያግዛል ብለዋል፡፡
እስካሁን የቡና ጥራትን ለማስጠበቅ በተከናወኑ ተግባራት የቡና ምርት መዳረሻ ሀገራትን ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰዋል።
በ2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ 64 ለሚሆኑ ሀገራት የቡና ምርቷን ትልክ እንደነበር ጠቅሰው፤ አሁን ላይ የቡና ምርታችን መዳረሻ ሀገራትን ቁጥር ወደ 84 ከፍ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት፡፡
በሁለት ዓመታት ውስጥ የተፈጠሩት 20 አዳዲስ የቡና ገበያ መዳረሻዎች ከተለመደው አካሂድ በመውጣት ቡናን በአዲስ መልክ ለመላክ የተደረገው ጥረት ውጤት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡
በሲዳማ ክልል ከአንድ ሄክታር በአማካይ ከ10 ኩንታል በላይ የቡና ምርት እየተሰበሰበ ነው
++++++++++++++++++++
በሲዳማ ክልል በ2018 የምርት ዘመን ከአንድ ሄክታር መሬት በአማካይ ከ10 ኩንታል በላይ የቡና ምርት እየተሰበሰበ መሆኑን የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ በምርት ዘመኑ ለመሰብሰብ ከታቀደው 239 ሺህ ቶን የቡና ምርት ውስጥ እስካሁን 80 ሺህ ቶኑ ተሰብስቧል።
በክልሉ 176 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና የተሸፈነ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 146 ሺህ ሄክታር የሚሆነው ምርት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።
በደጋ እና ወይናደጋ አካባቢዎች የምርት አሰባሰብ ሂደቱ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መስፍን፤ አማካይ ምርታማነቱም በአንድ ሄክታር ከ10 ኩንታል በላይ መድረሱን ገልጸዋል።
የቡና ጥራትንና ምርታማነትን ለማሳደግ አርሶ አደሮችን በክላስተር የማደራጀት ሥራ እየተሠራ ሲሆን፤ በዘንድሮው ዓመትም በ239 ክላስተሮች የማደራጀት ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።
ያረጁ የቡና ዛፎችን በመጎንደል፣ አዳዲስ ዝርያዎችን በመተካትና የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም ምርታማነትን የመጨመር ሥራ እየተሠራ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በተጨማሪም ሁለት ሄክታርና ከዚያ በላይ የቡና ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ምርታቸውን በቀጥታ ለውጭ ገበያ እንዲልኩ በተፈቀደው መሠረት፤ በዘንድሮው ዓመት 495 አርሶ አደሮች አዲስ የኤክስፖርት ፈቃድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።
+++++++++++++++++
@ጋዜጣ_ፕላስ
++++++++++++++++++++
በሲዳማ ክልል በ2018 የምርት ዘመን ከአንድ ሄክታር መሬት በአማካይ ከ10 ኩንታል በላይ የቡና ምርት እየተሰበሰበ መሆኑን የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬ እና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ በምርት ዘመኑ ለመሰብሰብ ከታቀደው 239 ሺህ ቶን የቡና ምርት ውስጥ እስካሁን 80 ሺህ ቶኑ ተሰብስቧል።
በክልሉ 176 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና የተሸፈነ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 146 ሺህ ሄክታር የሚሆነው ምርት እየሰጠ ይገኛል ብለዋል።
በደጋ እና ወይናደጋ አካባቢዎች የምርት አሰባሰብ ሂደቱ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት አቶ መስፍን፤ አማካይ ምርታማነቱም በአንድ ሄክታር ከ10 ኩንታል በላይ መድረሱን ገልጸዋል።
የቡና ጥራትንና ምርታማነትን ለማሳደግ አርሶ አደሮችን በክላስተር የማደራጀት ሥራ እየተሠራ ሲሆን፤ በዘንድሮው ዓመትም በ239 ክላስተሮች የማደራጀት ተግባር እየተከናወነ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።
ያረጁ የቡና ዛፎችን በመጎንደል፣ አዳዲስ ዝርያዎችን በመተካትና የተፈጥሮ ማዳበሪያን በመጠቀም ምርታማነትን የመጨመር ሥራ እየተሠራ መሆኑንም ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
በተጨማሪም ሁለት ሄክታርና ከዚያ በላይ የቡና ማሳ ያላቸው አርሶ አደሮች ምርታቸውን በቀጥታ ለውጭ ገበያ እንዲልኩ በተፈቀደው መሠረት፤ በዘንድሮው ዓመት 495 አርሶ አደሮች አዲስ የኤክስፖርት ፈቃድ መውሰዳቸውን አስታውቀዋል።
+++++++++++++++++
@ጋዜጣ_ፕላስ
የስልጤ ሮዝመሪ ተፈላጊነቱ ጨምሯል!
.......
የታይላንድ ቡናና ሻይ ማህበር ፕሬዚዳንት እና የኤስያ ቡና ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ትርዋት ዎግቮራታት በስልጤ ዞን የሮዝመሪ ምርትን ጎብኝተዋል፡፡
ጉብኝቱ የሮዝመሪ ምርት የገበያ ትስስር ለመፍጠር ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ተፈላጋነቱ እየጨመረ የመጣው የሮዝምሪ ምርት ወደ ውጭ ሀገራት እየተላከ ፥ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እያስገኘ ነው።
#agriculturepostethiopia #agriculture Central Ethiopia Region - Prosperity Party - ብልፅግና Silte Zone Government Communication Affairs Department
.......
የታይላንድ ቡናና ሻይ ማህበር ፕሬዚዳንት እና የኤስያ ቡና ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ትርዋት ዎግቮራታት በስልጤ ዞን የሮዝመሪ ምርትን ጎብኝተዋል፡፡
ጉብኝቱ የሮዝመሪ ምርት የገበያ ትስስር ለመፍጠር ዓላማ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
ተፈላጋነቱ እየጨመረ የመጣው የሮዝምሪ ምርት ወደ ውጭ ሀገራት እየተላከ ፥ የውጭ ምንዛሬ ገቢ እያስገኘ ነው።
#agriculturepostethiopia #agriculture Central Ethiopia Region - Prosperity Party - ብልፅግና Silte Zone Government Communication Affairs Department
ክቡር አቶ አዲሱ አረጋ በዛሬው ዕለት ከStarbucks ኩባንያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሮቤርቶ ቬጋ አሎንሶ ጋር የቡና ልማት እና ግብይትን በተመለከተ በኢትዮጵያ እና በStarbucks ኩባንያ መካከል ያለውን ስትራቴጂያዊ አጋርነት የበለጠ አጠናክሮ ማስቀጠል የሚያስችል ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸው ወቅት አስተማማኝ የስፔሻሊቲ ቡና አቅርቦት በማረጋገጥ የኢትዮጵያ ቡና በStarbucks የቡና Recipe ውስጥ መጠኑን ትርጉም ባለው ደረጃ ማሳደግ የሚያስችል መግባባት እንደተፈጠረ እንዲሁም የአነስተኛ አርሶ አደሮች ምርት እና ምርታማነት ለማሳደግ ኩባንያው ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጡን ክቡር ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ አጋርተዋል።
Starbucks በዓለም ትልቁ የስፔሻለቲ ቡናገዢ ኩባንያ ነው።
Starbucks በዓለም ትልቁ የስፔሻለቲ ቡናገዢ ኩባንያ ነው።
በ741ሺህ 165 ሔክታር ላይ የነበረ የቅመማቅመም ሰብል ተሰበሰበ
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018፡- በ741 ሺህ 165 ሔክታር ላይ የነበረ የቅመማቅመም ሰብል ተሰብስቦ 1 ሚሊየን 385 ሺህ 150 ቶን ምርት መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ገለጸ።
በበጀት ዓመቱ በቅመማቅመም ሰብል የተሸፈነው 775ሺህ 439 ሔክታር መሆኑን በባለሥልጣኑ የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ፍቃዱ ደፈረስ ገልጸዋል።
ከዚህ ውስጥ እስካሁን ምርት የሚሰጠው በ741 ሺህ 165 ሔክታር ላይ የነበረው የቅመማቅመም ሰብል መሆኑን ገልጸው፤ ምርት ስብሰባውም እንደተጠናቀቀ አመላክተዋል።
የቅመማቅመሙ ዐይነትም፤ በርበሬ፣ ዝንጅብል፣ ኮረሪማ፣ እርድ፣ ጥቁር አዝሙድ፣ ነጭ አዝሙድ፣ አብሽ፣ ድንብላል፣ ቁንዶ በርበሬ፣ ሚጥሚጣ፣ ሮዝመሪ፣ጥምዝ እና ሌሎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
አሁን ላይ የቅመማቅመም ሰብል የምርታማነት ሁኔታ በሔክታር 18 ነጥብ 4 ኩንታል መሆኑንም ለኢዜአ አስረድተዋል።
የቅመማቅመም ዘር ከአርሶ አደር ለአርሶ አደር አቅርቦትን በተመለከተ 1 ሺህ 513 ነጥብ 75 ኩንታል በርበሬ፣ 32 ኩንታል ሚጥሚጣ፣ 2 ሺህ 444 ነጥብ 4 ኩንታል ጥቁር አዝሙድ፣ 406 ኩንታል ነጭ አዝሙድ፣ 1ሺህ 300 ኩንታል አብሽ፣ 868 ሺህ 153 ኩንታል ዝንጅብል፣ 90 ሺህ 597 ኩንታል እርድ ለተጠቃሚዎች መቅረቡን ገልጸዋል።
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግም የኤክስቴንሽን አገልግሎትን፣ የኩታ ገጠም ልማትን፣ የሙሉ ፓኬጅ አተገባበርን ማጠናከርና አዳዲስ ቴክኖሎጂን መጠቀም ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ጥር 5/2018፡- በ741 ሺህ 165 ሔክታር ላይ የነበረ የቅመማቅመም ሰብል ተሰብስቦ 1 ሚሊየን 385 ሺህ 150 ቶን ምርት መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ገለጸ።
በበጀት ዓመቱ በቅመማቅመም ሰብል የተሸፈነው 775ሺህ 439 ሔክታር መሆኑን በባለሥልጣኑ የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ፍቃዱ ደፈረስ ገልጸዋል።
ከዚህ ውስጥ እስካሁን ምርት የሚሰጠው በ741 ሺህ 165 ሔክታር ላይ የነበረው የቅመማቅመም ሰብል መሆኑን ገልጸው፤ ምርት ስብሰባውም እንደተጠናቀቀ አመላክተዋል።
የቅመማቅመሙ ዐይነትም፤ በርበሬ፣ ዝንጅብል፣ ኮረሪማ፣ እርድ፣ ጥቁር አዝሙድ፣ ነጭ አዝሙድ፣ አብሽ፣ ድንብላል፣ ቁንዶ በርበሬ፣ ሚጥሚጣ፣ ሮዝመሪ፣ጥምዝ እና ሌሎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
አሁን ላይ የቅመማቅመም ሰብል የምርታማነት ሁኔታ በሔክታር 18 ነጥብ 4 ኩንታል መሆኑንም ለኢዜአ አስረድተዋል።
የቅመማቅመም ዘር ከአርሶ አደር ለአርሶ አደር አቅርቦትን በተመለከተ 1 ሺህ 513 ነጥብ 75 ኩንታል በርበሬ፣ 32 ኩንታል ሚጥሚጣ፣ 2 ሺህ 444 ነጥብ 4 ኩንታል ጥቁር አዝሙድ፣ 406 ኩንታል ነጭ አዝሙድ፣ 1ሺህ 300 ኩንታል አብሽ፣ 868 ሺህ 153 ኩንታል ዝንጅብል፣ 90 ሺህ 597 ኩንታል እርድ ለተጠቃሚዎች መቅረቡን ገልጸዋል።
ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግም የኤክስቴንሽን አገልግሎትን፣ የኩታ ገጠም ልማትን፣ የሙሉ ፓኬጅ አተገባበርን ማጠናከርና አዳዲስ ቴክኖሎጂን መጠቀም ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል።