በዞኑ በሻይ ልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል
ታህሳስ 26/2018
በኢሉ አባቦር ዞን ሻይን በኩታ ገጠም በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተመላከተ።
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ኢንሼቲቭ ተቀርጾላቸው በአዲስ መልክ እየለሙ ካሉ የእርሻ አይነቶች ውስጥ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ሩዝና ሻይ ተጠቃሽ ናቸው።
የሻይ ልማት ኢንሼቲቭ በኢሉባቦር ዞን በአብዛኞቹ ወረዳዎች እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን ባለፉት ሶስት ዓመታት በተለይም በመቱ፣ አሌና ሐሉ ወረዳዎች በስፋት በኩታ ገጠም እየለማ ይገኛል።
በተያዘው የበጋ ወቅትም ባለፈው ክረምት የተተከሉና በችግኝ ጣቢያዎች ላይ ያሉ የሻይ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን ደግሞ በ2018/2019 የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ትኩረት መሰጠቱን የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም ሁሉን የልማት አቅም በማሳተፍ 250 ሚሊዮን የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የችግኝ ዝግጅት ስራው ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ በወረዳዎች በወል አቅም በሕብረተሰብ ንቅናቄ ታግዞ የሚሰራ መሆኑም ተገልጿል።
በመቱ ወረዳ በሻይ ልማት ተደራጅተው የተሰማሩ አርሶአደሮች፤ በአሁኑ ወቅት የተተከለ የሻይ ተክል በመንከባከብ ስራ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የሻይ ልማት ስራውን የማስፋት እቅድ ያላቸው መሆኑን ተከትሎ ደግሞ በችግኝ ዝግጅት ስራውም እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሻይ ልማት ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት የሚውልና ከችግኝ ዝግጅቱ ጀምሮ ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ በዞኑ ትልቅ የስራ እድል ይፈጥራል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት መስክ መሆኑም ተገልጿል ።
ታህሳስ 26/2018
በኢሉ አባቦር ዞን ሻይን በኩታ ገጠም በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተመላከተ።
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ኢንሼቲቭ ተቀርጾላቸው በአዲስ መልክ እየለሙ ካሉ የእርሻ አይነቶች ውስጥ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ሩዝና ሻይ ተጠቃሽ ናቸው።
የሻይ ልማት ኢንሼቲቭ በኢሉባቦር ዞን በአብዛኞቹ ወረዳዎች እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን ባለፉት ሶስት ዓመታት በተለይም በመቱ፣ አሌና ሐሉ ወረዳዎች በስፋት በኩታ ገጠም እየለማ ይገኛል።
በተያዘው የበጋ ወቅትም ባለፈው ክረምት የተተከሉና በችግኝ ጣቢያዎች ላይ ያሉ የሻይ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን ደግሞ በ2018/2019 የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ትኩረት መሰጠቱን የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም ሁሉን የልማት አቅም በማሳተፍ 250 ሚሊዮን የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የችግኝ ዝግጅት ስራው ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ በወረዳዎች በወል አቅም በሕብረተሰብ ንቅናቄ ታግዞ የሚሰራ መሆኑም ተገልጿል።
በመቱ ወረዳ በሻይ ልማት ተደራጅተው የተሰማሩ አርሶአደሮች፤ በአሁኑ ወቅት የተተከለ የሻይ ተክል በመንከባከብ ስራ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የሻይ ልማት ስራውን የማስፋት እቅድ ያላቸው መሆኑን ተከትሎ ደግሞ በችግኝ ዝግጅት ስራውም እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሻይ ልማት ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት የሚውልና ከችግኝ ዝግጅቱ ጀምሮ ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ በዞኑ ትልቅ የስራ እድል ይፈጥራል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት መስክ መሆኑም ተገልጿል ።
የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ገለፀ፡፡
ወራቤ፤ ታህሳስ 26/2018 ስልጤ ኤፍ ኤም፤ የቡናና ቅመማ ቅመም ልማት ጽ/ቤት በቡና ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በተከላ ቡና ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል ፣በቡና በሽታና በግብይት መመሪያ ዙሪያ በጽ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡
በስልጠና ማጠቃለያ ላይ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የቡና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ኑሪ ስልጠናው የዘርፉ ባለሙያዎች በእውቀትና በክህሎት ታግዘው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለቡና ምርታማነት መቀነስ ዋናው ምክንያት የቡና ማሳ አያያዝና እንክብካቤ ያለው አንዱ ጉድለት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በእርጅና ምክንያት ምርታማነታቸው የቀነሱ የቡና ዛፎችን ሳይንሱን ተከትለው ለማደስ እና ለመጎንደል የሚያስችል በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና ለአመራሮችና ለዘርፉ ባለሙያዎች መሰጠቱን አቶ ቶፊቅ ተናግረዋል፡፡
የቡና ምርታማነት በሁለት መንገድ ማሳደግ ይቻላል ያሉት አቶ ቶፊቅ አንደኛው ያረጁ ቡናዎች በማደስ (በመጎንደል) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ያረጁ ቡናዎችን በንቀል በአዲስ መተካት እንደሆነ አስረድተዋል ።
ጉንደላ እና እድሳት የሚደረግላቸው ቡናዎች በተለይ በበሽታ የተጠቁ፣ ምርት መስጠት የማይችሉና እንዲሁም ከተተከሉ ረጅም ዕድሜ የሆናቸው እንደሆነም ኃላፊው አያይዘው ተናግረዋል።
አቶ ቶፊቅ አክለውም የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በዞኑ በዘንድሮ ዓመት ከ272 ሄክታር መሬት በላይ ቡናን ለመጎንደል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በስልጠናው የተሳተፉ አካላት ከቅየሳ ጀምሮ እስከ የቡና የተከላ አይነት፣ ጎንደላ፣ ምቀሳ እና ግረዛ ድረስ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ግልፅና አስተማሪ የሆነ ግንዛቤ የተገኘበት እንደሆነ አንስተዋል፡፡
በመጨረሻም ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በቡና ጉድጓድ ቁፋሮ ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል
በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ ወርኮ መንደር በአርሶ አደር የቡና ማሳ ላይ በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ተጠናቋል፡፡
ወራቤ፤ ታህሳስ 26/2018 ስልጤ ኤፍ ኤም፤ የቡናና ቅመማ ቅመም ልማት ጽ/ቤት በቡና ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በተከላ ቡና ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል ፣በቡና በሽታና በግብይት መመሪያ ዙሪያ በጽ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡
በስልጠና ማጠቃለያ ላይ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የቡና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ኑሪ ስልጠናው የዘርፉ ባለሙያዎች በእውቀትና በክህሎት ታግዘው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለቡና ምርታማነት መቀነስ ዋናው ምክንያት የቡና ማሳ አያያዝና እንክብካቤ ያለው አንዱ ጉድለት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
በእርጅና ምክንያት ምርታማነታቸው የቀነሱ የቡና ዛፎችን ሳይንሱን ተከትለው ለማደስ እና ለመጎንደል የሚያስችል በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና ለአመራሮችና ለዘርፉ ባለሙያዎች መሰጠቱን አቶ ቶፊቅ ተናግረዋል፡፡
የቡና ምርታማነት በሁለት መንገድ ማሳደግ ይቻላል ያሉት አቶ ቶፊቅ አንደኛው ያረጁ ቡናዎች በማደስ (በመጎንደል) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ያረጁ ቡናዎችን በንቀል በአዲስ መተካት እንደሆነ አስረድተዋል ።
ጉንደላ እና እድሳት የሚደረግላቸው ቡናዎች በተለይ በበሽታ የተጠቁ፣ ምርት መስጠት የማይችሉና እንዲሁም ከተተከሉ ረጅም ዕድሜ የሆናቸው እንደሆነም ኃላፊው አያይዘው ተናግረዋል።
አቶ ቶፊቅ አክለውም የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በዞኑ በዘንድሮ ዓመት ከ272 ሄክታር መሬት በላይ ቡናን ለመጎንደል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
በስልጠናው የተሳተፉ አካላት ከቅየሳ ጀምሮ እስከ የቡና የተከላ አይነት፣ ጎንደላ፣ ምቀሳ እና ግረዛ ድረስ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ግልፅና አስተማሪ የሆነ ግንዛቤ የተገኘበት እንደሆነ አንስተዋል፡፡
በመጨረሻም ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በቡና ጉድጓድ ቁፋሮ ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል
በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ ወርኮ መንደር በአርሶ አደር የቡና ማሳ ላይ በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ተጠናቋል፡፡
የሻይ ልማትን ለማላቅ እየታተረች ያለችው ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ለሻይ ልማት ተስማሚና ምቹ ሥነ-ምኅዳር መኖሩን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ አካል የሆነው የሻይ ልማት ኢኒሼቲቭ ተከላ በጥሩ ሁኔታ እየተከወነ መሆኑን ሰሞኑን በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል።
በመትከል የታየው መልካም ጅማሮ በአግሮ-ፕሮሰሲንግ ከተደገመ ሙሉ እንደሚሆንም አስገንዝበዋል።
በዚህም መሠረት የግሉ ዘርፍ ዕሴት በማከል ቢሳተፍ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ በተጨማሪ በኤክስፖርት ሀገራችንን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።
እስካሁን በኢትዮጵያ ስላለው የሻይ ልማት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የቡና፣ሻይና ቅመማቅመም ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ደፈረስ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም፥ እስካሁን ባለው መረጃና ልየታ መሠረት በኢትዮጵያ ለሻይ ቅጠል ልማት ተስማሚና ምቹ የሆነ ከ6 ሚሊየን ሔክታር የሚልቅ መሬት መኖሩን አመላክተዋል።
ካለው የመልማት ዐቅም አንጻር እየለማ ያለው አነስተኛ መሆኑን አንስተው፤ በዘርፉ በቀጣይ የተሻለ ለመሥራት መንግሥት ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል።
ለዚህም ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ አካል የሆነው የሻይ ቅጠል ልማት ኢኒሼቲቭ ተከላ በጥሩ ሁኔታ እየተከወነ መሆኑን መግለጻቸው ማሳያ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ የሻይ ቅጠል ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሪ ፍላጎቷን እንደምትደጉምም አንስተዋል።
ለአብነትም በ2017 የበጀት ዓመት 882 ነጥብ 45 ቶን የሻይ ቅጠል ምርት ወደ እንግሊዝ፣ ሕንድ እና ጀርመን በመላክ 1 ነጥብ 61 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱን አረጋግጠዋል።
በተያዘው የበጀት ዓመትም 898 ቶን በመላክ 1 ነጥብ 72 ሚሊየን ዶላር ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመው፤እስካሁን በእርሻ ልማቶች እና በአርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ተክል ከለማው 4 ሺህ 936 ሔክታር 4 ሺህ 854 ቶን ምርት መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።
ከዚህ አንጻር ዘርፉ እንደ ሌሎች የወጪ ምርቶች የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው አስገንዝበው፤ በይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ሀገር የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የሻይ ቅጠል ተክል አንድ ጊዜ ከተተከለ ለ80 እና 90 ዓመታት ምርት በመስጠት የሚቆይና በየ15 ቀኑ ምርቱን በመልቀም ገቢ ማግኘት የሚያስችል ስለመሆኑም አስገንዝበዋል።
እንደ አቶ ፍቃዱ ገለጻ፤ በኢትዮጵያ በሰፋፊ እርሻዎች ውስጥ አምስት የሻይ ቅጠል ምርት ማዘጋጃ ፋብሪካዎች አሉ።
በሻይ ማዋሀድ (ዕሴት በመጨመር) ላይ ተሰማርተው ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ ልዩ ምርቶችን እያቀረቡ ያሉ ኩባንያዎችም፤ ኢትዮ አግሪ ሴፍት (ውሽውሽና ጉመሮ ሻይ ልማት)፣ ኢስት አፍሪካ አግሪ ቢዝነስ፣ ሄሪቴጅ ሻይ ኢትዮጵያ እና መታድ የግብርና ልማት መሆናቸውን አብራርተዋል።
የሻይ ቅጠል ተክል (Assam tea type) ወደ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባው በፈረንጆቹ 1927 የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጳጳስ በነበሩት ጆርጅ ሆላንድ አማካኝነት እንደሆነም አውስተዋል።
ጆርጅ ሆላንድ ከውጭ ያመጡትን የሻይ ቅጠል ተክል ዘር በቦንጋ ከተማ ቶንጎላ አካባቢ ለሚኖሩ አርሶ አደሮች እንዲያለሙት ማሠራጨታቸውንም ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በፈረንጆቹ 1928 የእንግሊዝ ቆንስል የነበሩት አብዱል መጅድ ከሕንድና ኬንያ የሻይ ቅጠል ተክል ፍሬዎችን በማስመጣት በኢሉአባቦር ዞን አሌ ወረዳ ጉመሮ አካባቢ ማሠራጨታቸውን አመላክተዋል።
እንዲሁም በኢትዮጵያ ከ1950 እስከ 1960 ዓ.ም አማራጭ የግብርና ልማት ማስፋፋት ሥራዎች አካል በመሆን የሻይ ቅጠል ልማት እና ኢንቨስትመንት ሥራ መጀመሩን አንስተዋል።
ልማቱ በተጠናከረ መልኩ የተጀመረው ሁለቱ ሰፋፊ የሻይ ቅጠል ተክል እርሻዎች በሚገኙባቸው በውሽውሽ እና ጉመሮ አካባቢዎች ከ1950 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑንም ይጠቅሳሉ።
ከ1972 ዓ.ም ጀምሮም በቡናና ሻይ ልማት ሚኒስቴር እየተመራ በተጠናከረ መልኩ ሲሠራበት መቆየቱን አውስተዋል።
ከወቅቱ መንግሥት ለውጥ በኋላ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በመፍረሱ የሻይ ልማት ድርጅቶቹ ወደ ግል ይዞታ (ኢትዮ-አግሪሴፍት አ.ማ) ተዛውረው እየተመሩ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ፣በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ጋምቤላ ክልሎች በአራት የሻይ ልማት ድርጅቶች (ውሽውሽ፣ ጉመሮ፣ኢስት አፍሪካ (የጨዋቃ ኡቶ) እና ቨርዳንታ) እንዲሁም በአነስተኛ አርሶ አደሮች በአውት ግሮዎርስ ትሥሥር እና በኩታ ገጠም እየለማ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
እስካሁን ባለው መረጃም የሻይ ልማት ዘርፍ ከ80 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን አስታውቀዋል።
#ኢዜአ
አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 28/2018 (ኢዜአ)፡-በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ለሻይ ልማት ተስማሚና ምቹ ሥነ-ምኅዳር መኖሩን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ አካል የሆነው የሻይ ልማት ኢኒሼቲቭ ተከላ በጥሩ ሁኔታ እየተከወነ መሆኑን ሰሞኑን በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል።
በመትከል የታየው መልካም ጅማሮ በአግሮ-ፕሮሰሲንግ ከተደገመ ሙሉ እንደሚሆንም አስገንዝበዋል።
በዚህም መሠረት የግሉ ዘርፍ ዕሴት በማከል ቢሳተፍ ከሀገር ውስጥ ፍጆታ በተጨማሪ በኤክስፖርት ሀገራችንን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።
እስካሁን በኢትዮጵያ ስላለው የሻይ ልማት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን የቡና፣ሻይና ቅመማቅመም ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ደፈረስ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።
በቆይታቸውም፥ እስካሁን ባለው መረጃና ልየታ መሠረት በኢትዮጵያ ለሻይ ቅጠል ልማት ተስማሚና ምቹ የሆነ ከ6 ሚሊየን ሔክታር የሚልቅ መሬት መኖሩን አመላክተዋል።
ካለው የመልማት ዐቅም አንጻር እየለማ ያለው አነስተኛ መሆኑን አንስተው፤ በዘርፉ በቀጣይ የተሻለ ለመሥራት መንግሥት ትኩረት መስጠቱን ጠቁመዋል።
ለዚህም ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአረንጓዴ ዐሻራ አካል የሆነው የሻይ ቅጠል ልማት ኢኒሼቲቭ ተከላ በጥሩ ሁኔታ እየተከወነ መሆኑን መግለጻቸው ማሳያ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያ የሻይ ቅጠል ወደ ተለያዩ ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሪ ፍላጎቷን እንደምትደጉምም አንስተዋል።
ለአብነትም በ2017 የበጀት ዓመት 882 ነጥብ 45 ቶን የሻይ ቅጠል ምርት ወደ እንግሊዝ፣ ሕንድ እና ጀርመን በመላክ 1 ነጥብ 61 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ገቢ መገኘቱን አረጋግጠዋል።
በተያዘው የበጀት ዓመትም 898 ቶን በመላክ 1 ነጥብ 72 ሚሊየን ዶላር ለማግኘት መታቀዱን ጠቁመው፤እስካሁን በእርሻ ልማቶች እና በአርሶ አደሮች በሻይ ቅጠል ተክል ከለማው 4 ሺህ 936 ሔክታር 4 ሺህ 854 ቶን ምርት መሰብሰቡን ጠቅሰዋል።
ከዚህ አንጻር ዘርፉ እንደ ሌሎች የወጪ ምርቶች የራሱ አስተዋጽኦ እንዳለው አስገንዝበው፤ በይበልጥ አጠናክሮ በማስቀጠል ሀገር የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ ማድረግ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የሻይ ቅጠል ተክል አንድ ጊዜ ከተተከለ ለ80 እና 90 ዓመታት ምርት በመስጠት የሚቆይና በየ15 ቀኑ ምርቱን በመልቀም ገቢ ማግኘት የሚያስችል ስለመሆኑም አስገንዝበዋል።
እንደ አቶ ፍቃዱ ገለጻ፤ በኢትዮጵያ በሰፋፊ እርሻዎች ውስጥ አምስት የሻይ ቅጠል ምርት ማዘጋጃ ፋብሪካዎች አሉ።
በሻይ ማዋሀድ (ዕሴት በመጨመር) ላይ ተሰማርተው ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ ልዩ ምርቶችን እያቀረቡ ያሉ ኩባንያዎችም፤ ኢትዮ አግሪ ሴፍት (ውሽውሽና ጉመሮ ሻይ ልማት)፣ ኢስት አፍሪካ አግሪ ቢዝነስ፣ ሄሪቴጅ ሻይ ኢትዮጵያ እና መታድ የግብርና ልማት መሆናቸውን አብራርተዋል።
የሻይ ቅጠል ተክል (Assam tea type) ወደ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የገባው በፈረንጆቹ 1927 የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጳጳስ በነበሩት ጆርጅ ሆላንድ አማካኝነት እንደሆነም አውስተዋል።
ጆርጅ ሆላንድ ከውጭ ያመጡትን የሻይ ቅጠል ተክል ዘር በቦንጋ ከተማ ቶንጎላ አካባቢ ለሚኖሩ አርሶ አደሮች እንዲያለሙት ማሠራጨታቸውንም ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በፈረንጆቹ 1928 የእንግሊዝ ቆንስል የነበሩት አብዱል መጅድ ከሕንድና ኬንያ የሻይ ቅጠል ተክል ፍሬዎችን በማስመጣት በኢሉአባቦር ዞን አሌ ወረዳ ጉመሮ አካባቢ ማሠራጨታቸውን አመላክተዋል።
እንዲሁም በኢትዮጵያ ከ1950 እስከ 1960 ዓ.ም አማራጭ የግብርና ልማት ማስፋፋት ሥራዎች አካል በመሆን የሻይ ቅጠል ልማት እና ኢንቨስትመንት ሥራ መጀመሩን አንስተዋል።
ልማቱ በተጠናከረ መልኩ የተጀመረው ሁለቱ ሰፋፊ የሻይ ቅጠል ተክል እርሻዎች በሚገኙባቸው በውሽውሽ እና ጉመሮ አካባቢዎች ከ1950 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑንም ይጠቅሳሉ።
ከ1972 ዓ.ም ጀምሮም በቡናና ሻይ ልማት ሚኒስቴር እየተመራ በተጠናከረ መልኩ ሲሠራበት መቆየቱን አውስተዋል።
ከወቅቱ መንግሥት ለውጥ በኋላ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በመፍረሱ የሻይ ልማት ድርጅቶቹ ወደ ግል ይዞታ (ኢትዮ-አግሪሴፍት አ.ማ) ተዛውረው እየተመሩ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ፣በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ጋምቤላ ክልሎች በአራት የሻይ ልማት ድርጅቶች (ውሽውሽ፣ ጉመሮ፣ኢስት አፍሪካ (የጨዋቃ ኡቶ) እና ቨርዳንታ) እንዲሁም በአነስተኛ አርሶ አደሮች በአውት ግሮዎርስ ትሥሥር እና በኩታ ገጠም እየለማ እንደሚገኝም አስረድተዋል።
እስካሁን ባለው መረጃም የሻይ ልማት ዘርፍ ከ80 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩን አስታውቀዋል።
#ኢዜአ