Ethiopian Coffee and Tea Authority
5.74K subscribers
5.5K photos
30 videos
66 files
358 links
Ethiopian Coffee and Tea Authority
Download Telegram
በዞኑ በሻይ ልማት ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል
ታህሳስ 26/2018
በኢሉ አባቦር ዞን ሻይን በኩታ ገጠም በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸው ተመላከተ።
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ኢንሼቲቭ ተቀርጾላቸው በአዲስ መልክ እየለሙ ካሉ የእርሻ አይነቶች ውስጥ ሙዝ፣ አቮካዶ፣ ሩዝና ሻይ ተጠቃሽ ናቸው።
የሻይ ልማት ኢንሼቲቭ በኢሉባቦር ዞን በአብዛኞቹ ወረዳዎች እየተተገበረ የሚገኝ ሲሆን ባለፉት ሶስት ዓመታት በተለይም በመቱ፣ አሌና ሐሉ ወረዳዎች በስፋት በኩታ ገጠም እየለማ ይገኛል።
በተያዘው የበጋ ወቅትም ባለፈው ክረምት የተተከሉና በችግኝ ጣቢያዎች ላይ ያሉ የሻይ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የኢሉባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ከዚሁ ጎን ለጎን ደግሞ በ2018/2019 የሚተከሉ ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ትኩረት መሰጠቱን የጽሕፈት ቤቱ ምክትል ኃላፊ አቶ አወል መሐመድ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በዚህም ሁሉን የልማት አቅም በማሳተፍ 250 ሚሊዮን የሻይ ቅጠል ችግኞችን ለማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።
የችግኝ ዝግጅት ስራው ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ በወረዳዎች በወል አቅም በሕብረተሰብ ንቅናቄ ታግዞ የሚሰራ መሆኑም ተገልጿል።
በመቱ ወረዳ በሻይ ልማት ተደራጅተው የተሰማሩ አርሶአደሮች፤ በአሁኑ ወቅት የተተከለ የሻይ ተክል በመንከባከብ ስራ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የሻይ ልማት ስራውን የማስፋት እቅድ ያላቸው መሆኑን ተከትሎ ደግሞ በችግኝ ዝግጅት ስራውም እየተሳተፉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የሻይ ልማት ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት የሚውልና ከችግኝ ዝግጅቱ ጀምሮ ሰፊ የሰው ኃይል የሚፈልግ በመሆኑ በዞኑ ትልቅ የስራ እድል ይፈጥራል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት መስክ መሆኑም ተገልጿል ።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ፡
እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የደስታ እንዲሆንላችሁ በራሴ እና በባለስልጣን መ/ቤቱ ስም ከልብ እመኛለሁ፡፡
መልካም በዓል
አዱኛ ደበላ (ዶ/ር)
የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የስልጤ ዞን ግብርና መምሪያ የቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ገለፀ፡፡

ወራቤ፤ ታህሳስ 26/2018 ስልጤ ኤፍ ኤም፤ የቡናና ቅመማ ቅመም ልማት ጽ/ቤት በቡና ወቅታዊ ተግባራት ዙሪያ ለወረዳና ከተማ አስተዳደር ለተውጣጡ የዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች የክህሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በተከላ ቡና ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል ፣በቡና በሽታና በግብይት መመሪያ ዙሪያ በጽ/ቤቱ ከፍተኛ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡

በስልጠና ማጠቃለያ ላይ የዞኑ ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የቡና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቶፊቅ ኑሪ ስልጠናው የዘርፉ ባለሙያዎች በእውቀትና በክህሎት ታግዘው አርሶ አደሩን እንዲደግፉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ለቡና ምርታማነት መቀነስ ዋናው ምክንያት የቡና ማሳ አያያዝና እንክብካቤ ያለው አንዱ ጉድለት መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በእርጅና ምክንያት ምርታማነታቸው የቀነሱ የቡና ዛፎችን ሳይንሱን ተከትለው ለማደስ እና ለመጎንደል የሚያስችል በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ስልጠና ለአመራሮችና ለዘርፉ ባለሙያዎች መሰጠቱን አቶ ቶፊቅ ተናግረዋል፡፡

የቡና ምርታማነት በሁለት መንገድ ማሳደግ ይቻላል ያሉት አቶ ቶፊቅ አንደኛው ያረጁ ቡናዎች በማደስ (በመጎንደል) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ያረጁ ቡናዎችን በንቀል በአዲስ መተካት እንደሆነ አስረድተዋል ።

ጉንደላ እና እድሳት የሚደረግላቸው ቡናዎች በተለይ በበሽታ የተጠቁ፣ ምርት መስጠት የማይችሉና እንዲሁም ከተተከሉ ረጅም ዕድሜ የሆናቸው እንደሆነም ኃላፊው አያይዘው ተናግረዋል።

አቶ ቶፊቅ አክለውም የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በዞኑ በዘንድሮ ዓመት ከ272 ሄክታር መሬት በላይ ቡናን ለመጎንደል ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ አካላት ከቅየሳ ጀምሮ እስከ የቡና የተከላ አይነት፣ ጎንደላ፣ ምቀሳ እና ግረዛ ድረስ በንድፈ ሀሳብና በተግባር የተደገፈ ግልፅና አስተማሪ የሆነ ግንዛቤ የተገኘበት እንደሆነ አንስተዋል፡፡

በመጨረሻም ያረጀ ቡና ጉንደላና ምቀሳ እንዲሁም በቡና ጉድጓድ ቁፋሮ ቅየሳ አወጣጥና በቡና ችግኝ አተካከል
በወራቤ ከተማ 01 ቀበሌ ወርኮ መንደር በአርሶ አደር የቡና ማሳ ላይ በተግባር የተደገፈ ስልጠና በመስጠት ተጠናቋል፡፡