በሀላባ ዞን ዌራ ወረዳ በታችኛው አርሾ ቀበሌ በለበቆ የመንግስት ችግኝ ጣቢያ ውስጥ ለያዝነው ዓመት ተከላ እንዲውል እየተዘጋጀ የሚገኝ የቡና ችግኝ አሁናዊ ገጽታ!
ታህሳስ 26/04/18 ዓ.ም
ታህሳስ 26/04/18 ዓ.ም
የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ መረጃ በትክክል መሰብሰብና መያዝ ወሳኝ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ገለፀ
ሆሳዕና 24/04/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ቅመማ ቅመም ባላስልጣን ጋር በመተባበር በኢዩ-ካፌ በጀት ድጋፍ በEUDR ህጎችና የአርሶአደሮች ቡና ማሳ መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ ለዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በሆሳዕና ከተማ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሶምሶን ወ/ግዮርግስ በበኩላቸው ስልጠናው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ቅመማ ቅመም ባላስልጣን ጋር በመተባበር በኢዩ-ካፌ በጀት ድጋፍ በEUDR ህጎችና የአርሶአደሮች ቡና ማሳ መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ እየተሰጠ ነው ብለዋል ።
ከደን ጭፍጨፋ ነጻ የሆነ እና የምርቱ መነሻና ወቅቱ የተረጋገጠ እንድሁም የተሻለ ግብይት እንድካሄድ የሚያስችል ስልጠና እንደሆነም ተናግረዋል ።
የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ መረጃ በትክክል መሰብሰብና መያዝ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል ።
የሁሉም አርሶአደሮች ከተከለ እስከ ምርት አሰባሰብ ድረስ ያለውን የቡና መረጃ ለመሰባሰብ የጋራ ግንዛቤ እንድኖር ነው ብለዋል ።
በቡና ልማት በቴክኖሎጂ የተደገፈ መረጃ በመያዝ የግብይት ሂደቱን በማሳለጥ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ የስልጣናው ፋይዳ የጎላ እንደሆነም አንስተዋል ።
የሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ሀብታሙ ታደሰ በስልጠና ወቅት እንደገለፁት ስልጠናው በቡና ምርት ግብይት ፣በመረጃ አሰባሰብና በጥራትና በአመራረት ዘይቤ ትኩረት ያደርጋል ።
የቡና ምርት አያያዝን በቴክኖሎጂ ከማስደገፍ አንጻር የሚስተዋሉ ውስንናቶችን ለማስቀረት በሚል በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ዶክተር ሀብታሙ ተናግረዋል ።
በየአከባቢው የሚገኙ የቡና አምራቾችና የማሳ ሽፋን ተለይቶ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ልዩ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸውም አንስተዋል ።
ሰልጣኞች እየተሰጠ ያለውን ትምህርትና ስልጠና በአግባቡ በመከታተል በየአካባቢያቸው የአርሶአደሮችን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ የድርሻቸውን እንድወጡም አስገንዝበዋል ።
የሀድያ ዞን ቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተማም ስርጎታ እንደተናገሩት በዞኑ ከዚህ ቀደም የቡና ሽፋን 20 ሺህ ሄክተር ከነበረበት በተያየዘው በጀት ዓመት ወደ 42 ሺህ ሄክተር ማሳደግ ተችሏል ።
የጉራጌ ዞን ቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት የኃላፊ ተወካይ አቶ ታሪኩ ወርቁ በዞኑ የቡና ሽፋን 55 ሺህ ሄክተር እንደሆነ ገልጸው ይህ ስልጣና ህገወጥ ተግባራትን በመከላከል አምራቹ በቀጥታ ከገዥ ጋር እንድገነኝ እድል ይፈጥራልም ብለዋል ።
ከዚህ ቀደም የቡና ምርትን በተለምዶ በማምረት በአከባቢው ገበያ በማቅረብ የተጠቀሚነት ጉድለት እንደነበር ያነሱት ሀላፊዎቹ ከሽፋን ባለፈ ጥሩ ምርት የሚሰጥና በሽታን መቋቋም የሚችል የቡና ዝርያዎችን ተደራሽ በማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል ።
የአርሶአደሮችን ተጠቀምነት ለማረጋገጥ በገበያ ትስስር ዙርያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል ።
ምንጭ ሀድያ ቴሌቪዥን
ሆሳዕና 24/04/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ቅመማ ቅመም ባላስልጣን ጋር በመተባበር በኢዩ-ካፌ በጀት ድጋፍ በEUDR ህጎችና የአርሶአደሮች ቡና ማሳ መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ ለዘርፉ አመራሮችና ባለሙያዎች በሆሳዕና ከተማ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሶምሶን ወ/ግዮርግስ በበኩላቸው ስልጠናው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡናና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ቅመማ ቅመም ባላስልጣን ጋር በመተባበር በኢዩ-ካፌ በጀት ድጋፍ በEUDR ህጎችና የአርሶአደሮች ቡና ማሳ መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ እየተሰጠ ነው ብለዋል ።
ከደን ጭፍጨፋ ነጻ የሆነ እና የምርቱ መነሻና ወቅቱ የተረጋገጠ እንድሁም የተሻለ ግብይት እንድካሄድ የሚያስችል ስልጠና እንደሆነም ተናግረዋል ።
የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ የማሳ መረጃ በትክክል መሰብሰብና መያዝ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል ።
የሁሉም አርሶአደሮች ከተከለ እስከ ምርት አሰባሰብ ድረስ ያለውን የቡና መረጃ ለመሰባሰብ የጋራ ግንዛቤ እንድኖር ነው ብለዋል ።
በቡና ልማት በቴክኖሎጂ የተደገፈ መረጃ በመያዝ የግብይት ሂደቱን በማሳለጥ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ የስልጣናው ፋይዳ የጎላ እንደሆነም አንስተዋል ።
የሀዲያ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶክተር ሀብታሙ ታደሰ በስልጠና ወቅት እንደገለፁት ስልጠናው በቡና ምርት ግብይት ፣በመረጃ አሰባሰብና በጥራትና በአመራረት ዘይቤ ትኩረት ያደርጋል ።
የቡና ምርት አያያዝን በቴክኖሎጂ ከማስደገፍ አንጻር የሚስተዋሉ ውስንናቶችን ለማስቀረት በሚል በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ዶክተር ሀብታሙ ተናግረዋል ።
በየአከባቢው የሚገኙ የቡና አምራቾችና የማሳ ሽፋን ተለይቶ ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ልዩ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸውም አንስተዋል ።
ሰልጣኞች እየተሰጠ ያለውን ትምህርትና ስልጠና በአግባቡ በመከታተል በየአካባቢያቸው የአርሶአደሮችን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ የድርሻቸውን እንድወጡም አስገንዝበዋል ።
የሀድያ ዞን ቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተማም ስርጎታ እንደተናገሩት በዞኑ ከዚህ ቀደም የቡና ሽፋን 20 ሺህ ሄክተር ከነበረበት በተያየዘው በጀት ዓመት ወደ 42 ሺህ ሄክተር ማሳደግ ተችሏል ።
የጉራጌ ዞን ቡናና ቅመማ ቅመም ጽ/ቤት የኃላፊ ተወካይ አቶ ታሪኩ ወርቁ በዞኑ የቡና ሽፋን 55 ሺህ ሄክተር እንደሆነ ገልጸው ይህ ስልጣና ህገወጥ ተግባራትን በመከላከል አምራቹ በቀጥታ ከገዥ ጋር እንድገነኝ እድል ይፈጥራልም ብለዋል ።
ከዚህ ቀደም የቡና ምርትን በተለምዶ በማምረት በአከባቢው ገበያ በማቅረብ የተጠቀሚነት ጉድለት እንደነበር ያነሱት ሀላፊዎቹ ከሽፋን ባለፈ ጥሩ ምርት የሚሰጥና በሽታን መቋቋም የሚችል የቡና ዝርያዎችን ተደራሽ በማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል ።
የአርሶአደሮችን ተጠቀምነት ለማረጋገጥ በገበያ ትስስር ዙርያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል ።
ምንጭ ሀድያ ቴሌቪዥን
Prime Minister Abiy Ahmed Ali "The tea development initiative, which is part of the Green Legacy program, is being implemented successfully. The promising start observed in planting, if followed through with full agro-processing and supported by private sector participation to add value, will benefit our country through exports in addition to meeting domestic consumption needs. "