ከሲዳማ ክልል ከ6 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ቀረበ
ሐዋሳ ታኅሣስ 24/2018
በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት ከ6 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የሲዳማ ክልል ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ ተናገሩ።
ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበውን የቡና መጠን ለማሳደግም ቡናን በክላስተር የማልማት፣ ያረጁ ቡናዎችን የመጎንደልና በአዲስ የመተካት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።
ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለማስፋት ከምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር እየተሠራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግም ከቡና አምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም ከ232 በላይ ቡና አምራች ኢንዱስትሪዎች ቨርሚ ኮምፖስት አዘጋጅተው ለአርሶአደሩ እያሰራጩ ነው ብለዋል።
ዘንድሮ ከተዘጋጀው ከ5 ነጥብ 2 ሚሊየን ቶን በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ 3 ነጥብ 1 ሚሊየን ቶኑ ጥቅም ላይ መዋሉን እንዲሁም ቀሪው ለመጋቢት ተከላ መቀመጡን አስረድተዋል።
በክልሉ በቡና ልማት ከተሸፈነው 176 ሺህ ሔክታር መሬት 148 ሺህ ሔክታሩ ምርት እየሰጠ መሆኑም ተጠቁሟል።
በክልሉ የበንሳ ወረዳ ቡናና ፍራፍሬ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ታምራት ቱንሲሳ በበኩላቸው፤ በወረዳው ካለው ከፍተኛ የቡና ልማት የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው ብለዋል፡፡
ምርታማነቱን ለማሳደግም በወረዳው ባሉ ከ19 በላይ ቡናን የሚያዘጋጁ ኢንዱስትሪዎችና አርሶ አደሮች ማሳ ከ365 ሺህ ቶን በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት መቻሉን አንስተዋል።
ምንጭ፡ ኢዜአ
ሐዋሳ ታኅሣስ 24/2018
በበጀት ዓመቱ ያለፉት ወራት ከ6 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ መቅረቡን የሲዳማ ክልል ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ ተናገሩ።
ለማዕከላዊ ገበያ የሚቀርበውን የቡና መጠን ለማሳደግም ቡናን በክላስተር የማልማት፣ ያረጁ ቡናዎችን የመጎንደልና በአዲስ የመተካት ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስታውቀዋል።
ሥነ-ምኅዳርን መሠረት ያደረጉ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችን ለማስፋት ከምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር እየተሠራ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሳደግም ከቡና አምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር እየተሠራ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም ከ232 በላይ ቡና አምራች ኢንዱስትሪዎች ቨርሚ ኮምፖስት አዘጋጅተው ለአርሶአደሩ እያሰራጩ ነው ብለዋል።
ዘንድሮ ከተዘጋጀው ከ5 ነጥብ 2 ሚሊየን ቶን በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ 3 ነጥብ 1 ሚሊየን ቶኑ ጥቅም ላይ መዋሉን እንዲሁም ቀሪው ለመጋቢት ተከላ መቀመጡን አስረድተዋል።
በክልሉ በቡና ልማት ከተሸፈነው 176 ሺህ ሔክታር መሬት 148 ሺህ ሔክታሩ ምርት እየሰጠ መሆኑም ተጠቁሟል።
በክልሉ የበንሳ ወረዳ ቡናና ፍራፍሬ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ታምራት ቱንሲሳ በበኩላቸው፤ በወረዳው ካለው ከፍተኛ የቡና ልማት የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማሳደግ የተጀመሩ ተግባራት ውጤት እያመጡ ነው ብለዋል፡፡
ምርታማነቱን ለማሳደግም በወረዳው ባሉ ከ19 በላይ ቡናን የሚያዘጋጁ ኢንዱስትሪዎችና አርሶ አደሮች ማሳ ከ365 ሺህ ቶን በላይ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት መቻሉን አንስተዋል።
ምንጭ፡ ኢዜአ
የቡና ምርታማነትን የሚያሻሽሉ ችግኞችን በማፍላት አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 23/2018
የቡና ምርታማነትን የሚያሻሽሉ ችግኞችን በማፍላት አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን የጅማ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
ቱሪዝም ሚኒስቴር "የቡና ቱሪዝም" የመገናኛ ብዙኅን ሙያተኞች የትውውቅና የግንዛቤ ማስጨበጫ የጉብኝት መርሃ ግብር እያካሄደ አንደሚገኝ ይታወቃል።
በዛሬው ውሎም የቡና ቱሪዝምን ማነቃቃት ዓላማ ያደረገ የመገናኛ ብዙኅን ሙያተኞች የቡና አብቃይ አካባቢዎች የመስክ ምልከታ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ጎማ ወረዳ በሻሻ ቀበሌ ቀጥሏል።
በዚሁ ወቅት የጅማ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አብዲ መሐመድኑር፤ የጅማ ሕዝብ ከቡና ምርታማነት ጋር ጥብቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቁርኝት እንዳለው ገልጸዋል።
በዞኑ በቡና ምርታማነት ላይ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሻሽሉ ውጤታማ የቡና ልማት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል።
በዞኑ የቡና ጥራትና ምርታማነትን በማሳደግ ከለቀማ እስከ ውጭ ገበያ የሚቀርብበት ሥርዓት በጥንቃቄ እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የአርሶ አደሩን የቡና ምርታማነት ለማሳደግ ምርታማነታቸው የተረጋገጠ የችግኝ ዝርያዎችን ተደራሽ በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ባለሙያ የሆኑት መሐመድሰፋ ከድር በበኩላቸው፣ የአርሶ አደሮችን የቡና ምርታማነት በማሳደግ በተለያዩ የደረጃ መለኪያዎች በውጭ ገበያ ጭምር ቀጥታ ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ለኢዜአ ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 23/2018
የቡና ምርታማነትን የሚያሻሽሉ ችግኞችን በማፍላት አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን የጅማ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለጸ።
ቱሪዝም ሚኒስቴር "የቡና ቱሪዝም" የመገናኛ ብዙኅን ሙያተኞች የትውውቅና የግንዛቤ ማስጨበጫ የጉብኝት መርሃ ግብር እያካሄደ አንደሚገኝ ይታወቃል።
በዛሬው ውሎም የቡና ቱሪዝምን ማነቃቃት ዓላማ ያደረገ የመገናኛ ብዙኅን ሙያተኞች የቡና አብቃይ አካባቢዎች የመስክ ምልከታ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ጎማ ወረዳ በሻሻ ቀበሌ ቀጥሏል።
በዚሁ ወቅት የጅማ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አብዲ መሐመድኑር፤ የጅማ ሕዝብ ከቡና ምርታማነት ጋር ጥብቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቁርኝት እንዳለው ገልጸዋል።
በዞኑ በቡና ምርታማነት ላይ የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሻሽሉ ውጤታማ የቡና ልማት ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል።
በዞኑ የቡና ጥራትና ምርታማነትን በማሳደግ ከለቀማ እስከ ውጭ ገበያ የሚቀርብበት ሥርዓት በጥንቃቄ እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም የአርሶ አደሩን የቡና ምርታማነት ለማሳደግ ምርታማነታቸው የተረጋገጠ የችግኝ ዝርያዎችን ተደራሽ በማድረግ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው ብለዋል።
በዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ባለሙያ የሆኑት መሐመድሰፋ ከድር በበኩላቸው፣ የአርሶ አደሮችን የቡና ምርታማነት በማሳደግ በተለያዩ የደረጃ መለኪያዎች በውጭ ገበያ ጭምር ቀጥታ ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ ለኢዜአ ገልጸዋል።
🍒☕️ The coffee picking season is almost coming to an end and our focus now shifts to nurturing the next crop......preparing the fields, caring for the trees and laying the foundation for another exceptional harvest.
In coffee, every ending is also a beginning and the quality of tomorrow’s cup is shaped by the work we do today.
#☕️
In coffee, every ending is also a beginning and the quality of tomorrow’s cup is shaped by the work we do today.
#☕️
አለማቀፍ መስፈርቶችን አሟልቶ መገኘት እስከተቻለ ድረስ ጥሩ የሚባል/Premium ዋጋ ማግኘት እንደሚቻል ተገለጸ!!
ታህሳስ 25/2018
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በሀንስ ኒውማን ፋውንዴሽን ከሚደገፈው EU YAYU DESIRA ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ወርክሾፕ ላይ ነው፡፡ የወርክሾፑ ዓላማ ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ የመጡ ምሁራን ኢትዮጵያ ቡናዎቿን ዓለማቀፉ ማህበረሰብ በተለይም አውሮፓውያን በሚጠይቁት መስፈርት መሰረት GI ሰርቲፋይ መሆን ስለሚችሉበት መንገድ ገለጻ ለማድረግ እና አእምሯዊ ንብረቶች/ IP Based Strategy በመከተል ላመረትነው ምርት ጥሩ የሚባል/Premium ዋጋ ማግኘት ስለሚቻልበት ሁኔታ ከባለሙያዎች ጋር ለመምከር ነው፡፡
ምሁራኑ አጠቃላይ የንግድ ምልክት/Trade Mark ከ GI ጋር ያላቸውን አጠቃላይ አንድነት እና ልዩነት እንዲሁም ዘመኑን የተከተለውን GI በመጠቀም አገሪቱም ሆነ ቡና አብቃይ ማህበረሰብ የልፋቱ ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ያለውን ጠቀሜታ አስረድተዋል፡፡ EU YAYU DESIRA ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረግባቸው ወረዳዎችም ከዚሁ ጋር በተያያዘ እስካሁን በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ኢኮኖሚያዊ እና ህጋዊ አንድምታውን ጠቋሚ አንድ ጠቃሚ ጥናታዊ ሰነድ እንደሚያቀርቡ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ ሰነድ እንደአገር ወጥ የሆነ አካሄድ እንዲኖር ለማድረግ የሚረዳ ከመሆኑም ሌላ የሻይና ቅ/ቅመም ሰብሎችንም በዚሁ ቅኝት እንዲጓዙ የሚስችል እንደሆነም ተብራርቷል፡፡
ክቡር ዋና ዳይሬክተሩን ወክለው የተገኙት በባለስልጣን መ/ቤቱ የዋና ዳ/ር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሰፊሳ አባቡ ሴክተሩ እንደአየር ንብረት ለውጥ፣ አለማቀፉ ተለዋዋጭ የገበያ ሁኔታ እና ሌሎች መሰል ችግሮች የሚፈትኑት ከመሆኑ አንጻር በእውቀት የተደገፈ እንዲሆን ለማድረግ ባለስልጣን መ/ቤቱ ከተለያዩ ምርምር ተቋማት እና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በያዩ በሚገኙ የጫካ ቡናዎች ዙሪያ የሚሰራው ይህ ሰነድ በብዙ መልኩ ጠቃሚ በመሆኑ ከመቱ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀንስኒውማን፣ ECF, PHE እንዲሁም ከባለስልጣን መ/ቤቱ የተገኙ አመራር እና ባለሙያዎች ሙያዊ ግብዓታቸውን ያለማሰለስ መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡ ውይይቱ በዚህ መልኩ ቀጥሎ ውሏል፡፡
ታህሳስ 25/2018
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በሀንስ ኒውማን ፋውንዴሽን ከሚደገፈው EU YAYU DESIRA ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው ወርክሾፕ ላይ ነው፡፡ የወርክሾፑ ዓላማ ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ የመጡ ምሁራን ኢትዮጵያ ቡናዎቿን ዓለማቀፉ ማህበረሰብ በተለይም አውሮፓውያን በሚጠይቁት መስፈርት መሰረት GI ሰርቲፋይ መሆን ስለሚችሉበት መንገድ ገለጻ ለማድረግ እና አእምሯዊ ንብረቶች/ IP Based Strategy በመከተል ላመረትነው ምርት ጥሩ የሚባል/Premium ዋጋ ማግኘት ስለሚቻልበት ሁኔታ ከባለሙያዎች ጋር ለመምከር ነው፡፡
ምሁራኑ አጠቃላይ የንግድ ምልክት/Trade Mark ከ GI ጋር ያላቸውን አጠቃላይ አንድነት እና ልዩነት እንዲሁም ዘመኑን የተከተለውን GI በመጠቀም አገሪቱም ሆነ ቡና አብቃይ ማህበረሰብ የልፋቱ ተጠቃሚ በማድረግ በኩል ያለውን ጠቀሜታ አስረድተዋል፡፡ EU YAYU DESIRA ፕሮጀክት ተግባራዊ በሚደረግባቸው ወረዳዎችም ከዚሁ ጋር በተያያዘ እስካሁን በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ኢኮኖሚያዊ እና ህጋዊ አንድምታውን ጠቋሚ አንድ ጠቃሚ ጥናታዊ ሰነድ እንደሚያቀርቡ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ ሰነድ እንደአገር ወጥ የሆነ አካሄድ እንዲኖር ለማድረግ የሚረዳ ከመሆኑም ሌላ የሻይና ቅ/ቅመም ሰብሎችንም በዚሁ ቅኝት እንዲጓዙ የሚስችል እንደሆነም ተብራርቷል፡፡
ክቡር ዋና ዳይሬክተሩን ወክለው የተገኙት በባለስልጣን መ/ቤቱ የዋና ዳ/ር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሰፊሳ አባቡ ሴክተሩ እንደአየር ንብረት ለውጥ፣ አለማቀፉ ተለዋዋጭ የገበያ ሁኔታ እና ሌሎች መሰል ችግሮች የሚፈትኑት ከመሆኑ አንጻር በእውቀት የተደገፈ እንዲሆን ለማድረግ ባለስልጣን መ/ቤቱ ከተለያዩ ምርምር ተቋማት እና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በያዩ በሚገኙ የጫካ ቡናዎች ዙሪያ የሚሰራው ይህ ሰነድ በብዙ መልኩ ጠቃሚ በመሆኑ ከመቱ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀንስኒውማን፣ ECF, PHE እንዲሁም ከባለስልጣን መ/ቤቱ የተገኙ አመራር እና ባለሙያዎች ሙያዊ ግብዓታቸውን ያለማሰለስ መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡ ውይይቱ በዚህ መልኩ ቀጥሎ ውሏል፡፡