Ethiopian Coffee and Tea Authority
5.75K subscribers
5.52K photos
30 videos
66 files
358 links
Ethiopian Coffee and Tea Authority
Download Telegram
አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ያላቸው ተነሳሽነት እያደገ መጥቷል - ሚኒስትር አዲሱ አረጋ

ሀዋሳ፤ ታህሳስ 22/2018 በሁሉም ቡና አብቃይ ወረዳዎች በተደረገ የባለሙያ ድጋፍ አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብ ያላቸው ተነሳሽነት እየተሻሻለ መምጣቱን የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ገለጹ።

በሲዳማ ክልል ሸበዲኖ ወረዳ በቡና ልማት ላይ የተሳተፉ አርሶ አደር ማሳ የጎበኙት የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ እንዳሉት በተያዘው ዓመት 600ሺህ ቶን ቡና ለውጪ ገበያ ለማቅረብ ታቅዷል።

ለውጭ ገበያ ከሚቀርበው የቡና ምርት ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት ግብ ተይዞ ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በሲዳማ ክልሉ ቡና አምራች በሆኑ አካባቢዎች የቡና ጥራትና ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ ለመሆን እየተሰራ ያለው ሥራ በዘርፉ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ መሆኑንም ተናግረዋል።

የቡና ዝርያን ለማሻሻል፣ የአመራረት ዘዴን ለማዘመን፣ ኩታ ገጠም የቡና ልማትን ለማስፋፋትና ምርታማነታቸው የተረጋገጠ የቡና ዝርያዎችን ለማልማት የተሰራው ሥራ ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችል ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን ቡና በቻይና የማስተዋወቅ ሥራ እየተሰራ ነው ያሉት ሚኒስትሩ በተለይ ከባለ ልዩ ጣዕም ቡና ተጠቃሚነትን ለማሳደግ በቀጣይ በተለያዩ ሀገራት የማስተዋወቅ ሥራ ይሰራል ብለዋል።

ዘንድሮ ለውጪ ገበያ ለማቅረብ የተያዘውን ዕቅድ ማሳካት የሚያስችሉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እንዳሉ ጠቁመው፣ በሁሉም ቡና አብቃይ ወረዳዎች በተደረገ የባለሙያ ድጋፍ አርሶ አደሮች ቡናን በጥራት አምርቶ ለማቅረብ ያላቸው ተነሳሽነት መሻሻሉን ገልጸዋል።

የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሀላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው በክልሉ ቡና እና አቮካዶ ለውጪ ገበያ እንደሚቀርብ ታሳቢ ተደርጎ እየሰተራ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ የተለያዩ ስትራቴጂዎችን በመጠቀም የቡና ጥራትና ምርታማነትን ለማሻሻል ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው አዳዲስ የቡና ዝርያዎችን መጠቀምን ጨምሮ ምርታማነትን የሚያሳድጉ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በእርጅና ምክንያት ምርታማነቱ የቀነሰ የቡና ተክልን በአዲስ የመተካትና ባህር ዛፍን ነቅሎ በቡና የመተካት ሥራ እየተሰራ መሆኑንም አክለዋል።

የክልሉ ቡና፣ ቅመማቅመምና ፍራፍሬ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ በክልሉ በተያዘው ዓመት ወደ ውጪ ከሚላከው 40ሺህ ቶን ቡና 17 በመቶ የሚሆነው ባለልዩ ጣዕም እንደሚሆንና ይህንንም በሂደት ወደ 20 በመቶ ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አርሶ አደሮችም ባለልዩ ጣዕም ቡና አምርተው ለውጪ ገበያ በራሳቸው በቀጥታ መላክ እንዲችሉ ለ400 አርሶ አደሮች ፈቃድ በመስጠት ክትትልና ደጋፍ እየተደረጋላቸው መሆኑንም ተናግረዋል።

በክልሉ ሸበዲኖ ወረዳ ባለልዩ ጣዕም ቡና አምርተው ለውጪ ገበያ ቀጥታ ለማቅረብ ፈቃድ ከተሰጣቸው አርሶ አደሮች መካከል ቦዳ ሳጉና እንዳሉት በሁለት ሄክታር መሬት ቡና እንዳለሙና ከሄክታር 30 ኩንታል ምርት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል።

ያመረቱትን ምርት በቀጥታ ወደ ውጪ ለመላክ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው ከክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ እና ከቡና፣ ቅመማቅመምና ፍራፍሬ ባለስልጣን ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ተናግረዋል። ኢዜአ
የኢትዮጵያ የቡና ምርታማነት የወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍተኛ አቅም እየፈጠረ ነው

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 23/2018

የኢትዮጵያ የቡና ምርታማነት ዓለም አቀፍ የወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትን በማሳደግ ለውጭ ምንዛሬ ግኝት ከፍተኛ አቅም እየፈጠረ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታወቀ።

ኢትዮጵያ የግብርናውን ምርታማነት የሚያሳድጉ የተሻሻሉ ዝርያዎችንና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በዘርፉ ተጨባጭ ውጤት እያስመዘገበች ትገኛለች።

የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ግኝት ዋነኛ ምንጭ የሆነው ቡናም የዚህ አካል ሲሆን ባለፉት የለውጥ ዓመታት በቡና ምርታማነት ላይ በተከናወኑ ስራዎች አበረታች ውጤት እየተመዘገበ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሻፊ ዑመር ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል።

መንግስት ቡናን በብዛት፣ በጥራትና ዓለም አቀፍ ፍላጎትን ባገናዘበ መልኩ በማምረት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ያለው አበርክቶ እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ያረጁ የቡና ተክሎችን በአዲስ የመተካት እንዲሁም ቴክኖሎጂን የመጠቀም ባህል እያደገ መምጣቱ በቡና ምርታማነትና በውጭ ምንዛሬ ግኝት ላይ ከፍተኛ ለውጥ አንዲመዘገብ ማስቻሉን ተናግረዋል።

በተለይም በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር የሚተከሉ የቡና ችግኞች የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ አቅም እየፈጠሩ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የቡና ምርታማነትን ለማሻሻል የተደረጉ የሪፎርም ሥራዎች ከወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ በከፍተኛ መጠን ማሳደግ ማስቻላቸውን ገልጸዋል።

የለውጡ መንግስት በ2013 ዓ.ም የሪፎርም ሥራውን ሲጀመር ከቡና ወጪ ንግድ 907 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን አስታውሰው በ2014 ዓ.ም ደግሞ ገቢው ወደ አንድ ነጥብ አራት ቢሊየን ዶላር ማደጉን ጠቅሰዋል።

የሪፎርሙ ስኬታማ ጉዞ ለዘርፉ በፈጠረው መልካም ዕድል በመታገዝ  በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት አምስት ወራት ከቡና ወጪ ንግድ አንድ ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን አስታውቀዋል።

ጥሬ ቡናን ብቻ ከመላክ ባለፈ ዕሴት የተጨመረበት የቡና ምርትን ለዓለም ገበያ ለማስተዋወቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡና ማኅበር ፕሬዝዳንት ሁሴን አምቦ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የአርሶ አደሩን ግንዛቤ በማሳደግና የተሻሻሉ የቡና ችግኞች እንዲሰራጩ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በ2018 በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን የቡና ምርት ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከባለሥልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
A consultative workshop was recently held to review critical research proposals aimed at transforming the coffee value chain.

(January 1, 2026:-ECTA)
Bishoftu, Ethiopia
In a significant move toward modernizing Ethiopia’s most vital commodity sector, a high-level consultative workshop was held on January 1, 2026, at the Bin International Hotel in Bishoftu to review critical research proposals aimed at transforming the coffee value chain.

The workshop, organized by ECTA under the Food Systems, Land Use and Restoration (FOLUR) Ethiopia project, brought together elite professionals from the Ethiopian Coffee and Tea Authority (ECTA), the Agricultural Transformation Institute (ATI), and the Jimma Agricultural Research Centre (JARC). The workshop focused on proposals concerning climate change risk, the role of gender in the coffee value chain, and the assessment of technology for coffee production.

The workshop was officially opened by the Guest of Honor, Mr. Tagay Nuru, Deputy Director General of the Ethiopian Coffee and Tea Authority (ECTA) and Head of the Coffee, Tea, and Spice Development sector. In his opening remarks, Mr. Tagay highlighted that despite initial delays in budget releases, the technical teams have successfully moved forward with essential research proposals. He emphasized that the primary goal of the gathering was to harvest constructive inputs from diverse stakeholders to refine the upcoming full-scale research.

Dr. Zerihun Kebebew, National Coffee Platform Coordinator under the UNDP’s FOLUR-Ethiopia project gave a presentation on the three pivotal research proposals stated above. Dr. Zerihun at the end of his presentation stated that this workshop provided a platform to align the FOLUR project's deliverable outputs with ECTA’s strategic directions. He added that the FOLUR-Ethiopia project is a cornerstone initiative designed to prevent forest loss, promote restoration, and integrate sustainability into coffee value chains. Its success is vital for the livelihoods of enormous coffee-dependent people in Ethiopia.

Mr. Bonsa Merga, FOLUR-Ethiopia project focal person and Planning and Strategic Affairs Executive in ECTA, noted that while the initial drafts were prepared by an in-house team, the integration of external professional insights would be vital for the project's effectiveness. Mr. Bonsa added that "If assisted by external professionals, the results will be significantly more effective’’.

During the sessions, participants provided rigorous feedback, aligning the proposals with ECTA’s strategic directions and international sustainability standards. And, finally, Mr. Tagay Nuru concluded by directing that all identified gaps and confusing issues must be addressed immediately. He also stressed that the research must be completed in a shorter timeframe since time limit matters. Mr. Tagay pointed that this workshop marks a decisive step in Ethiopia's journey to harmonize coffee production with environmental conservation, ensuring that the Ethiopian coffee plantation areas remain resilient in the face of global climate and economic shifts, too.
Reported by: Tesfu Alemayehu