470 ቶን ቡና ወደ ማዕከላዊው ገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በበጀት ዓመቱ በወረዳው ከቅርብ ዓመታት በፊት የቡና ልማት ብዙም ያልተለመደና ከ600 ሄክታር ያልበለጠ የጫካ ቡና መኖሩን በማስታወስ አሁን በተሰጠው ትኩረት ከ10 ሺህ 400 ሄክታር በላይ ማሳ በቡና መሸፈኑን የጣሎ ወረዳ ግብርና ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አፈወርቅ አደመ ገልጸዋል።
በወረዳው አሁን በሁሉም ቀበሌዎች ማልማት የተጀመረ መሆኑን በመጥቀስ ከዚህ ውስጥ አራቱ ቡናን ስፔሻላይዝ በማድረግ የሚያመርቱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ቡናን በብዛትና በጥራት በማልማት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት አቶ አፈወርቅ በበጀት ዓመቱ 5 ሺ ቶን ቡናን በማሰባሰብ 470 ቶን ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል።
ከዚህም ከ3400 ቶን በላይ ምርት አሁን መሰብሰቡንና 347 ቶን በላይ ቡና ደርቆ ወደ መጋዘን መግባቱን ጠቁመዋል።
ምርታማነት ማሻሻያ ፓኬጅን ከመጠቀም አንጻር ቡናን በክላስተር ማልማት፣ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና መሰጠቱ፣ ከ155 ሄክታር በላይ ቡና መጎንደሉን፣ የኮምፖስት ዝግጅት እና ሌሎች ምርታማነትን የሚጨምሩ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በግብይት ሂደት ጥራትንና የዕዝ ሰንሠለትን ጠብቆ ወደ ገበያ ከማቅረብ አንጻር ህገወጥነትን የመከላከል፣ 4 አቅራቢ ነጋዴዎችን ማዘጋጀት፣ 2 እሸት ማጠቢያ ኢንዱስትሪ መቋቋሙ፣ የተሻለ የግብይት ማዕከል በወረዳው መታጠሩን አብራርተዋል።
በወረዳው በአርሶ አደሩ ማሳ ከሚለማው ቡና በተጨማሪ የግል አልሚና ማህበራት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።
ዘርፉን ለማበረታታት ወረዳው ከሰጠው 116.8 ሄክታር ውስጥ በ2002 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ በመግባት 96 ሄክታርን በማልማት ላይ ያለው የብ አግሮ ቡና ልማት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነው።
ከተተከለው ውስጥ 63 ሄክታር አሁን ምርት እየሰጠ መሆኑን ያነሱት የማህበሩ ስራ አስኪያጅ፤ አቶ አስራት በቀለ ከማልማቱ ጎን ለጎን ምርታማነትን ለመጨመር 25 ሄክታር ጉንደላ ስራና 8 ሄክታር ነቅሎ ተከላ መደረጉን ገልጸዋል።
በያዝነው ዓመት 1398 ኩንታል ቀይ እሸት ቡና ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን ከዕቅዱ 130 በመቶ መሳካቱን ጨምረው ገልጸዋል። እስካሁን 937 ኩንታል ደርቆ ወደ መጋዘን መግባቱን ተናግረዋል።
የለማው ቡና ወደ አረብ ኢምሬትስ በመላኩ የተሻለ የገበያ ትስስር መፈጠሩንና ገቢ ማግኘቱን የገለጹት አቶ አስራት፤ 22 ቋሚና ከ300 እስከ 400 ለሚሆኑት ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ ዕድል እየተፈጠረላቸው መሆኑን ጨምረው አንስተዋል።
በመጨረሻም ድርጅቱ በዞኑ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች እርሻን ማስፋፋት ላይ እየሰራ መሆኑን አንስተው፤ መንግስት በቦንጋ ከተማ ቦታ ካመቻቸ ዘመናዊ የቡና ማበጠሪያ በማዘጋጀት ቡናውን ቀጥታ ኤክስፖርት ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ምንጭ፡ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
በበጀት ዓመቱ በወረዳው ከቅርብ ዓመታት በፊት የቡና ልማት ብዙም ያልተለመደና ከ600 ሄክታር ያልበለጠ የጫካ ቡና መኖሩን በማስታወስ አሁን በተሰጠው ትኩረት ከ10 ሺህ 400 ሄክታር በላይ ማሳ በቡና መሸፈኑን የጣሎ ወረዳ ግብርና ደን፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አፈወርቅ አደመ ገልጸዋል።
በወረዳው አሁን በሁሉም ቀበሌዎች ማልማት የተጀመረ መሆኑን በመጥቀስ ከዚህ ውስጥ አራቱ ቡናን ስፔሻላይዝ በማድረግ የሚያመርቱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ቡናን በብዛትና በጥራት በማልማት ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ ነው ያሉት አቶ አፈወርቅ በበጀት ዓመቱ 5 ሺ ቶን ቡናን በማሰባሰብ 470 ቶን ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ዕቅድ መያዙን ተናግረዋል።
ከዚህም ከ3400 ቶን በላይ ምርት አሁን መሰብሰቡንና 347 ቶን በላይ ቡና ደርቆ ወደ መጋዘን መግባቱን ጠቁመዋል።
ምርታማነት ማሻሻያ ፓኬጅን ከመጠቀም አንጻር ቡናን በክላስተር ማልማት፣ ለባለድርሻ አካላት ስልጠና መሰጠቱ፣ ከ155 ሄክታር በላይ ቡና መጎንደሉን፣ የኮምፖስት ዝግጅት እና ሌሎች ምርታማነትን የሚጨምሩ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በግብይት ሂደት ጥራትንና የዕዝ ሰንሠለትን ጠብቆ ወደ ገበያ ከማቅረብ አንጻር ህገወጥነትን የመከላከል፣ 4 አቅራቢ ነጋዴዎችን ማዘጋጀት፣ 2 እሸት ማጠቢያ ኢንዱስትሪ መቋቋሙ፣ የተሻለ የግብይት ማዕከል በወረዳው መታጠሩን አብራርተዋል።
በወረዳው በአርሶ አደሩ ማሳ ከሚለማው ቡና በተጨማሪ የግል አልሚና ማህበራት ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አንስተዋል።
ዘርፉን ለማበረታታት ወረዳው ከሰጠው 116.8 ሄክታር ውስጥ በ2002 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ስራ በመግባት 96 ሄክታርን በማልማት ላይ ያለው የብ አግሮ ቡና ልማት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ነው።
ከተተከለው ውስጥ 63 ሄክታር አሁን ምርት እየሰጠ መሆኑን ያነሱት የማህበሩ ስራ አስኪያጅ፤ አቶ አስራት በቀለ ከማልማቱ ጎን ለጎን ምርታማነትን ለመጨመር 25 ሄክታር ጉንደላ ስራና 8 ሄክታር ነቅሎ ተከላ መደረጉን ገልጸዋል።
በያዝነው ዓመት 1398 ኩንታል ቀይ እሸት ቡና ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ሲሆን ከዕቅዱ 130 በመቶ መሳካቱን ጨምረው ገልጸዋል። እስካሁን 937 ኩንታል ደርቆ ወደ መጋዘን መግባቱን ተናግረዋል።
የለማው ቡና ወደ አረብ ኢምሬትስ በመላኩ የተሻለ የገበያ ትስስር መፈጠሩንና ገቢ ማግኘቱን የገለጹት አቶ አስራት፤ 22 ቋሚና ከ300 እስከ 400 ለሚሆኑት ለአካባቢው ማህበረሰብ የስራ ዕድል እየተፈጠረላቸው መሆኑን ጨምረው አንስተዋል።
በመጨረሻም ድርጅቱ በዞኑ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች እርሻን ማስፋፋት ላይ እየሰራ መሆኑን አንስተው፤ መንግስት በቦንጋ ከተማ ቦታ ካመቻቸ ዘመናዊ የቡና ማበጠሪያ በማዘጋጀት ቡናውን ቀጥታ ኤክስፖርት ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ምንጭ፡ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
ከኢኮኖሚው ባለፈ የቱሪዝም ዘርፉን ለማሳደግ ምቹ የሆነው የኢትዮጵያ ቡና
*******
የቱሪዝም ሚኒስቴር ያዘጋጀው የቡና ቱሪዝም የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የትውውቅ ጉዞ መርሐ ግብር እየተከናወነ ይገኛል።
መርሐ ግብሩ ኢትዮጵያውያን ከቡና ጋር ያላቸውን ጥልቅ የባህል ቁርኝት በማሳየት፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ግንባር ቀደም ተመራጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ቡና በሁሉም የዓለም ክፍሎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያለው በመሆኑ፣ ከምርት እስከ ግብይት ያለውን ሂደት ለዓለም ማስተዋወቅ አስፈላጊ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወይኒቱ መልኩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቡና መገኛ በመሆኗ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም ለዓለም ለማስተዋወቅ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ቡናን መሰረት ያደረገው የትውውቅ ጉዞ እንደ ጅማ፣ ከፋ፣ ሲዳማ እና ይርጋጨፌ ያሉ ዋና ዋና የቡና አምራች አካባቢዎችን ያካተተ ሲሆን፤ በጉዞው ላይ የሚሳተፉ ጋዜጠኞችም ከቡና ለቀማ እና ዝግጅት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን በመመልከት ስለ ቡና ቱሪዝም ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።
መርሐ ግብሩ እስከ ታኅሣሥ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን፤ ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የቡና ማሳ የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል።
ቡና የኢትዮጵያውያን መገለጫ ከመሆኑ ባለፈ፣ ማኅበራዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድ ዘመናትን የተሻገረ እሴት በመሆኑ፤ ይህን ትልቅ የሀገር ሀብት ለዓለም ገልጦ ማሳየትና ማስተዋወቅ እንደሚገባም ተገልጿል
*******
የቱሪዝም ሚኒስቴር ያዘጋጀው የቡና ቱሪዝም የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የትውውቅ ጉዞ መርሐ ግብር እየተከናወነ ይገኛል።
መርሐ ግብሩ ኢትዮጵያውያን ከቡና ጋር ያላቸውን ጥልቅ የባህል ቁርኝት በማሳየት፣ ኢትዮጵያ በዘርፉ ያላትን ግንባር ቀደም ተመራጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማስተዋወቅ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ቡና በሁሉም የዓለም ክፍሎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያለው በመሆኑ፣ ከምርት እስከ ግብይት ያለውን ሂደት ለዓለም ማስተዋወቅ አስፈላጊ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወይኒቱ መልኩ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የቡና መገኛ በመሆኗ በዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም ለዓለም ለማስተዋወቅ በትኩረት ሊሠራ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
ቡናን መሰረት ያደረገው የትውውቅ ጉዞ እንደ ጅማ፣ ከፋ፣ ሲዳማ እና ይርጋጨፌ ያሉ ዋና ዋና የቡና አምራች አካባቢዎችን ያካተተ ሲሆን፤ በጉዞው ላይ የሚሳተፉ ጋዜጠኞችም ከቡና ለቀማ እና ዝግጅት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን በመመልከት ስለ ቡና ቱሪዝም ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችል መሆኑ ተጠቁሟል።
መርሐ ግብሩ እስከ ታኅሣሥ 25 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን፤ ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ የቡና ማሳ የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል።
ቡና የኢትዮጵያውያን መገለጫ ከመሆኑ ባለፈ፣ ማኅበራዊ ትስስርን በማጠናከር ረገድ ዘመናትን የተሻገረ እሴት በመሆኑ፤ ይህን ትልቅ የሀገር ሀብት ለዓለም ገልጦ ማሳየትና ማስተዋወቅ እንደሚገባም ተገልጿል
የቡና አምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው - አቶ አዲሱ አረጋ
ኦቢኤን ሣይበር ሚዲያ ታህሳስ 21/ 2018
የቡና አምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያረጋገጡ የማሻሻያ ስራዎች እየተሰሩ ነው አሉ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ፡፡
በሚኒስትሩ የተመራ ቡድን በሲዳማ ክልል ተገኝቶ የቡና ልማት እንቅስቃሴን ጎብኝቷል።
በዚህ ወቅት አቶ አዲሱ አረጋ እንዳሉት፤ በተያዘው በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን ቡና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከ3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ለማግኘት ታቅዷል።
በአርሶ አደሩ እና በህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት እየለማ ያለው ቡና ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችል ጠቅሰው፤ በሲዳማ ክልል የታየው የቡና ልማት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ቡና አምራች አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል የተለያዩ የማሻሻያ ርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ ገልጸው፤ ለአብነትም አርሶ አደሮች በቀጥታ ለውጭ ገበያ ምርት እንዲልኩ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
አርሶ አደሮቹ በቡና ስፔሻሊቲ ላይ ግንዛቤያቸው እንዲያድግ መደረጉን እና በቀላሉ ፈቃድ የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱን አብራርተዋል፡፡
በዓለም ገበያ በጣዕሙ ልዩ የሆነ ቡና የምታቀርበው ኢትዮጵያ በሚገባት ልክ እንድትጠቀም ተጨማሪ ስራዎች ያስፈልጋሉ ነው ያሉት።
የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው÷ በክልሉ የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ ክላስተር በማደራጀት አርሶ አደሩ በህብረት እንዲሰራ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ÷ ክልሉ በበጀት ዓመቱ 40 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡ ኤፍ.ኤም.ሲ
ኦቢኤን ሣይበር ሚዲያ ታህሳስ 21/ 2018
የቡና አምራች አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት የሚያረጋገጡ የማሻሻያ ስራዎች እየተሰሩ ነው አሉ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ፡፡
በሚኒስትሩ የተመራ ቡድን በሲዳማ ክልል ተገኝቶ የቡና ልማት እንቅስቃሴን ጎብኝቷል።
በዚህ ወቅት አቶ አዲሱ አረጋ እንዳሉት፤ በተያዘው በጀት ዓመት 600 ሺህ ቶን ቡና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከ3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ለማግኘት ታቅዷል።
በአርሶ አደሩ እና በህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት እየለማ ያለው ቡና ዕቅዱን ለማሳካት እንደሚያስችል ጠቅሰው፤ በሲዳማ ክልል የታየው የቡና ልማት ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ቡና አምራች አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል የተለያዩ የማሻሻያ ርምጃዎች እየተወሰዱ እንደሆነ ገልጸው፤ ለአብነትም አርሶ አደሮች በቀጥታ ለውጭ ገበያ ምርት እንዲልኩ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
አርሶ አደሮቹ በቡና ስፔሻሊቲ ላይ ግንዛቤያቸው እንዲያድግ መደረጉን እና በቀላሉ ፈቃድ የሚያገኙበት አሰራር መዘርጋቱን አብራርተዋል፡፡
በዓለም ገበያ በጣዕሙ ልዩ የሆነ ቡና የምታቀርበው ኢትዮጵያ በሚገባት ልክ እንድትጠቀም ተጨማሪ ስራዎች ያስፈልጋሉ ነው ያሉት።
የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው÷ በክልሉ የቡና ምርታማነትን ለማሳደግ ክላስተር በማደራጀት አርሶ አደሩ በህብረት እንዲሰራ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መስፍን ቃሬ÷ ክልሉ በበጀት ዓመቱ 40 ሺህ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ እንደሚያቀርብ ገልፀዋል፡ ኤፍ.ኤም.ሲ