Ethiopian Coffee and Tea Authority
6.03K subscribers
5.9K photos
30 videos
67 files
372 links
Ethiopian Coffee and Tea Authority
Download Telegram
አርሶ አደር ላኪዎች የገበያ ትስስር መፍጠር በሚችሉበት እና የመደራደር አቅማቸውን በሚያሳድጉበት ቴክኒክ ዙሪያ ጠቃሚ ስልጠና ተሰጠ!!
ታህሳስ 24∕2016 ዓ.ም
ሀዋሳ
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን፤ አርሶ አደር ላኪዎች አለማቀፍ የቡና ገበያውን መቆጣጠር እና የገበያ ትስስር መፍጠር በሚችሉበት እንዲሁም የመደራደር አቅማቸውን ማሳደግ በሚያስችላቸው ቴክኒክ ዙሪያ በዛሬው እለት በሀዋሳ ከተማ ጠቃሚ ስልጠና ሰጥቷል∶∶ አርሶ አደሮቹ የተውጣጡት ከኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ እንዲሁም ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሲሆን ቁጥራቸው ደግሞ ከመቶ የሚልቅ ነው∶∶
ስልጠናውን በቦታው ተገኝተው የከፈቱት ክቡር አቶ መስፍን ቃሬ የሲዳማ ክልል ቡናና ፍራፍሬ ልማት ዋና ዳይሬክተር እንዲሁም ክቡር አቶ ሬድዋን ከድር የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቡናና ቅ∕ቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ናቸው∶∶
ክቡር አቶ መስፍን ሰልጣኞችን እና ዝግጅቱን ያስተባበሩትን አካላት እንዲሁም አሰልጣኙን እንኳን ደህና መጣችሁ “ዳኢ ዊሾ“ ካሉ በኋላ፤ ቡና ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ከፖለቲካዊ፣ አካባቢያዊ እንዲሁም ማህበራዊ ህይወት ጋር በቀጥታ የተቆራኘ ከመሆን ባሻገር የአገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ግኝት መሰረት እና ኢትዮጵያ ካላት ህዝብ ቁጥር ሩብ ያህሉ የኑሮ መሰረት መሆኑን ባስተላለፉት መልእክት ገልጸዋል∶∶ ቀደም ባለው ጊዜ ቡና በቂ ትኩረት ስላልተሰጠው እና በበርካታ ውስብስብ ችግሮች የተጠላለፈ ቢሆንም አሁን ያለው መንግስት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ትኩረት በመስጠት የተለያዩ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያዎች እና የሪፎርም ተግባራት በመከናወናቸው አገሪቱም ሆነ አርሶ አደሩ የተሻለ ተጠቃሚ ቢሆኑም የታሰበው ደረጃ ላይ ለመድረስ የበለጠ ምርት እና ምርታማነትን መጨመር፣ ጥራትን መጠበቅ እንዲሁም የገበያ መዳረሻዎችን ማስፋት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል∶∶ ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ የመሰለ ውድድር በአገራችን መደረጉም በርካታ ሚሊየነር የቡና አርሶ አደሮችን መፍጠር እንዳስቻለና ከፍተኛ መነቃቃትንም እንደፈጠረ ተናግረዋል∶∶
ክቡር አቶ ሬድዋን በበኩላቸው አርሶ አደር ላኪዎች በተፈጠረላቸው ምቹ ሁኔታ የላኪነት ፈቃድ አውጥተው በዚህ ደረጃ መገኘታቸው አስደሳች መሆኑን ጠቅሰው አገሪቱ ባስቀመጥችው ግብ መሰረት በ2022 በአለም 2ኛዋ ቡና አምራች አገር እንድትሆን ለማድረግ የአርሶ አደሩ ሚና ወሳኝ እንደሆነ ተናግረዋል∶∶ ይህን ግብ ከዳር ለማድረስ ከፌዴራል ጀምሮ በየደረጃው ባለው የመንግስት እርከን ሰፊ ስራ እየተሰራ እንደሆነና በቡና እሴት ሰንሰለቱ የሚገኙ ተዋናዮችም የየድርሻቸውን መወጣት እንደሚገባቸው ጥሪ አቅርበዋል∶∶ ቡናችን ተፈጥሯዊ በመሆኑና የተፈጥሮ ማዳበሪያን ብቻ በመጠቀም የሚለማ በመሆኑ ሰፊ የገበያ እድል እንዳለው እና ጥራትን መጠበቅ እና ምርታማነትን ማሳደግ እስከተቻለ ድረስ እነብራዚል እና ኮሎምቢያ ተርታ ለመሰለፍ የሚያዳግት ነገር አለመኖሩን አስረድተዋል∶∶
ከሀላፊዎች መክፈቻ ስነስርአት በኋላ የአርደንት ኮፊ ማኔጂንግ ዳይሬክተር እና ባለቤት አቶ አሸናፊ አርጋው አለማቀፍ የቡና ገበያ ሁኔታ፣ ኢትዮጵያ ያላት የቡና መልማት ወርቃማ እድል፣ የገበያ ትስስርን እንዴት በቀላሉ መፍጠር ይቻላል? የኮንትራት አፈጻጸም ዘዴ እንዲሁም አርሶ አደር ላኪዎቹ የመደራደር አቅማቸውን በሚያሳድጉበት ቴክኒክ ዙሪያ ረዘም ያለ፣ እጅግ ሳቢ እና ጠቃሚ ስልጠና ሰጥተዋል∶∶
ስልጠናው እንደተጠናቀቀ አርሶ አደር ላኪዎቹ በርካታ ሙያዊ ጥያቄዎችን አቅርበው ከመድረክ በቂ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው የተደረገ ሲሆን ይህን መሰል ህይወታቸውን መቀየር የሚያስችል ስልጠና በመሰጠቱ በእጅጉ መርካታቸውን እና ለሌሎችም መሰሉ እድል ሊመቻች እንደሚገባ ጠቁመዋል∶∶ ለዚህም ባለስልጣን መ∕ቤቱን እና አቶ አሸናፊን እጅግ ከልብ በመነጨ ስሜት አመስግነዋል∶∶
አለም አረቢካ ቡናን የሚያደንቅበት ምስጢር ምን ይሆን?

ስብስብ እና ትርጉም: በሳህለማርያም

አረቢካ ቡና በሚከተሉት ዋና ዋና ምክንያቶች በዓለም ዙሪያ ከፍተኛ አድናቆት አለው።
1. ውስብስብ እና ስስ/የማይከብድ/ቀለል ያለ ጣዕም፡- አረቢካ ቡና እንደ Robusta ካሉ የቡና አይነቶች በበለጠ የበለፀገ እና ውስብስብ ባህርይ ያለው ጣዕም አለው። አበባ አበባ የሚል፣ ፍራፍሬ ፍራፍሬ የሚል፣ ቸኮሌት ቸኮሌት የሚል፣ ጤና አዳም ጤና አዳም የሚል፣ የደረቀ ለውዝ አይነት ጣዕም፣ ወይን ወይን የሚል፣ የሚንት እና የሌሎች ቅመማ ቅመሞች አይነት በውስጥ ደስታን እና ልዩ ቃናን መፍጠር ይችላል።
2. ምጥን አሲድ፡- አረቢካ ቡና አብዛኛውን ጊዜ ከፍ ያለ የአሲድነት መጠን ቢኖረውም ሚዛኑን የጠበቀ እና ደስ የሚያሰኝ ስሜት ያለው እንጂ እንደ ሮቡስታው የሚጎፈንን አይነት ጣዕም በምላስ የሚያስቀር ባለመሆኑ ተወዳጅ እና መንፈስን የሚያድስ ነው ይሉታል።
3. 3. ቀለል ያለ እና ሲጠጡት የማይከብድ፡- ፡- ከሮቡስታ ጋር ሲወዳደር አረቢካ ብዙ ጊዜ ቀለል ያለ አልኮል ስላለው ቡናን የማይወዱትን ጨምሮ ለመጠጥነት ቀላል፣ የማይከብድ እና ለብዙ ሰዎች ተስማሚ የሆነ ነው ይባልለታል።
4. ረዥም ጊዜ በአፍ ውስጥ መቆየት የሚችል ጣዕም፡- አረቢካ ቡና ብዙ ጊዜ በአፍ ውስጥ ረዥም እና አስደሳች የሆነ ቃናን ይተዋል፣ ከእያንዳንዱ ፉት በኋላ እርካታ እየጨመረ ይሄዳል፡፡
5. ዝቅተኛ ካፌይን፡- አረቢካ ከRobusta ያነሰ የካፌይን ይዘት ስላለው የልብና የደም ሥር (cardiovascular system) የተረጋጋ እንዲሆን ስለሚያደርገው ለካፌይን ልዩ ስሜታዊ ለሆኑ ሰዎች የበለጠ ተስማሚ ሊሆን ይችላል።
6. የአካባቢ እና የአየር ንብረት ሁኔታዎች፡- አረቢካ ብዙ ጊዜ የሚበቅለው እርጥበታማ እና ብዙም ለፀሀይ ብርሀን ገላጣ ባልሆነ ቦታ ላይ ሲሆን አፈሩም በተለያዩ ማዕድናት የበለፀገ ነው። በእነዚህ ሁኔታዎች ቡናዎች ተወዳጅ እና ልዩ ጣዕም እንዲኖራቸው ከማድረግ ባሻገር ለዘላቂ ግብርና እና አካባቢያዊ ስነምህዳሩን ምቹ ከማድረግ አንጻር/ To promote the development of distinctive flavors but also create a diverse ecosystem that contributes to sustainable agriculture. የሚያበረክተው አስተዋጽዖ የላቀ ነው።
7. ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ፡- አረቢካ ቡና ብዙውን ጊዜ በአለም አቀፍ ገበያው ላይ ተወዳጅ አን ተመራጭ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ብልሆች ሆነው ቡናቸውን በልዩ እንክብካቤ፣ በከፍተኛ ጥራት እና መጠን ለሚያዘጋጁ አዱኛን/ተዝቆ የማያልቅ ሀብትን መሰብሰብ የሚያስችላቸው ከመሆኑ ሌላ ለአገራቸውም የውጭ ምንዛሬ የላቀ አስተዋጽዖ ለማበርከት ያስችላቸዋል።
8. የተለያዩ አዘገጃጀት ሂደቶች/Processing፡- የአረቢካ ቡና ከተመረተ በኋላ በተለያዩ ዘዴዎች የታጠበ፣ ደረቅ፣ ሀኒ፣ አናሮቢክ፣ ካርቦኒክ ወዘተ. በሚል በተለያየ ጣዕም እና ልዩ ቃና በማዘጋጀት ለቆዪዎች እና ተጠቃሚዎች በማድረስ በፍቅር እንዲጠጣ ይደረጋል፡፡ ይህ ሁኔታ መገኛ የሆንንበት አረቢካ ቡናችንን ከሌሎች የተለየ እና ማራኪ ያደርገዋል።
የኢትዬጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በቡና ግብይት ዙሪያ በጅማ ከተማ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። ስልጠናውን እየወሰዱ የሚገኙት ከጅማ፣ ቡኖ በደሌ፣ ኢሉባቦር ዞኖችና እንዲሁም ከደቡብ ምዕራብ ኢትዬጵያ የመጡ አርሷደር ላኪዎች ናቸው። ይኸው ስልጠና ከቀናት በፊት በሐዋሳ ከተማ ለአርሷደር ላኪዎች እንደተሰጠ የሚታወስ ነው።