EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
138K subscribers
31.8K photos
323 videos
79 files
12.3K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የ8ኛ ዙር ምልምል ሰልጣኞችን አስመረቀ
******************

በምረቃ ስነ-ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ሰው ሀብት አመራር ዋና መምሪያ ሀላፊ ሌተናል ጀኔራል ሀጫሉ ሸለመ፤ ውትድርና ራስን ለሀገር አሳልፎ የመስጠት የተከበረ ሙያ መሆኑን አውስተው የዕለቱ ተመራቂዎችም ለዚህ ክቡር ሙያ በመብቃታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

የውትድርና ስልጠና ይጀመራል እንጂ የማያልቅ መሆኑን ተረድታችሁ በቀጣይ ራሳችሁን በእውቀት እና በክህሎት አሳድጋችሁ የውጪና የውስጥ ፀረ ሰላም ሀይሎችን ጥቃት መመከት የሚያስችል አቅም በየጊዜው መገንባት የሁልግዜ ተግባራችሁ ሊሆን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።

የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት አዛዥ ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ በበኩላቸው፤ ሰራዊቱ የሀገርን ክብር ለማስጠበቅ የተቋቋመ መሆኑን ጠቅሰው፤ የዛሬ ተመራቂዎች የውትድርና ሙያን የተቀላቀሉት የሀገራቸውን ክብር አስበው የህዝባቸውን ነፃነት አልመው እና የብዙሀንን ህይወት ለመጠበቅና ለማረጋገጥ መሆኑን ገልፀዋል።

የዕለቱ ተመራቂዎች በተሰጠው የመደበኛ ምልምል ስልጠና ካሪኩለም ውስጥ የተካተቱትን የስልጠና አይነቶች በሙሉ ለተከታታይ 6 ወራት መውሰዳቸውን የገለፁት ኮሎኔል አዲሱ ተርፋሳ በቀጣይም ወደ ሚመደቡበት አሀድ ከነባሩ ሰራዊት ጋር ተቀላቅለው ለሰራዊቱ ትልቅ አቅም መሆን እንደሚችሉ የታመነባቸው ናቸው ብለዋል።

በዚሁ የምረቃ ሥነ ሥርዓት የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በእለቱ ተመራቂዎች የተለያዩ ወታደራዊ ትርዒቶችንም ማቅረባቸውን ከሃገር መከላከያ ሠራዊት ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ከተቀመጠው አሰራር ውጪ የመኖሪያ ቤት ዋጋ ጭማሪ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነው - የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
*********************

የአከራይ ተከራይ አዋጅ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በህግ ከተቀመጠው አሰራር ውጪ የመኖሪያ ቤት ዋጋ ጭማሪ ማድረግና የነበረውን የኪራይ ውል ማቋረጥ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አስታውቋል፡፡

በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን ፍትሀዊ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በማህበረሰቡ ላይ የሚፈጥረው ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት የቤት ኪራይ ስርአቱ በህግ የሚመራ እና ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ለችግሩ አፋጣኝ ምላሽ መስጠት ተገቢ ሆኖ ሰለታመነበት የመኖሪያ ቤት ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 መጋቢት 24/2016 መውጣቱ ይታወቃል።

የከተማ አስተዳደሩም የአዋጁን ማስፈፀሚያ መመሪያ ቁጥር 7/2016 በማውጣት ተግባራዊ አድርጓል።

በመሆኑም አዋጁ ወጥቶ ተግባራዊ ከሆነበት ቀን ማለትም ከመጋቢት 24/2016 ጀምሮ መንግስት ከሚያስቀምጠው የኪራይ ውሳኔ ውጪ በአከራዮች የሚደረግ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ፈፅሞ የተከለከለ በመሆኑ አዋጁ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከህግ ከተቀመጠው አሰራር ውጪ የመኖሪያ ቤት ዋጋ ጭማሪ ማድረግና የነበረውን የኪራይ ውል ማቋረጥ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን ቢሮው ገልጿል።

ይህ እንዳይፈፀምም ቢሮው ተገቢውን ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚያደርግም ማስታወቁን ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የህግ ክልከላውን ተላልፈው የተገኙ አከራዮች ላይ በመመሪያ ቁጥር 7/2016 አንቀፅ 22 መሰረት አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድም ቢሮው አሳስቧል።
በአሜሪካ የተገኘው ግዑዝ አካል የሰው ፈጠራ ወይስ የሌላ ዓለም ፍጡራን ሥራ?
********************

ምድር ላይ በሚሆኑ፣ በሚደረጉ አጀብ በሚያሰኙ የፈጠራ ስራዎች እንደነቃለን:: በተራቀቁ የጦር ጀቶች፣በተምዘግዛጊ ሚሳኤሎች፣ ተራራ በሚንጡ ታንኮች የታገዘውን የሀገራትን የጦር ሜዳ ላይ የበላይነት እሽቅድምድም አይቶ መገረምንም እንዲሁ የተላመድነው ይመስላል።

የሆነው ሆኖ ግን የሌላ ዓለም ፍጡራን በምድር ላይ አደረጓቸው እየተባሉ የሚነገሩ በጥናት የሚወጡ ጽሑፎች ግን የዓለምን ቀልብ ከየትኛውም ምድራዊ ግኝት በላይ ለረጅም ጊዜ ተቆጣጥረውት ቀጥለዋል።

ከሰሞኑ የወጣው አዲስ መረጃ የጫረው ግርምት ዓለምን እያነጋገረ ይገኛል፡፡ የላስ ቬጋሱ ሜትሮፖሊታን ፖሊስ ዲፓርትመንት በሰሜኑ የላስቬጋስ ክፍል ጋዝ ፒክ በሚባለው በረሀማ ስፍራ አንድ ሚስጥራዊ ግዑዝ አካል ማግኘታቸው ይፋ አድርገዋል።

መጀመሪያ ክስተቱ እንደተፈጠረ 10 ጫማ ርዝመት ያለውን አንፀባራቂ አካል በማህበራዊ ድረ-ገጽ ሲዘዋወርና ብዙዎችን ሲያነጋግር የነበረ ሲሆን ይህ ግዑዝ አካል በአይነቱ ለየት ያለ አንፀባራቂ የሆነ ገፅታ እንዳለውም ተገልጿል።
https://ebc.et/newsdetails.aspx?newsid=7004
የከተሞች ወግ - ሙኒክ
**********

የዘንድሮውን የአውሮፓ ዋንጫ የፍጻሜ ውድድር የሚካሄድባት የጀርመኗ ሙኒክ ከተማ
ሙኒክ በጀርመን የባቫሪያ ክልል ዋና ከተማ ስትሆን ሙኒክ በታሪኳ ፣በሥነ ሕንፃ ፣ በቢራ ባህል እና በከፍተኛ ጥራት የምትታወቅ በባህል የበለፀገች ከተማ ነች።

ሙኒክ የተመሰረተችው በ1158 ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በንጉሣዊ ቅርሶቿ በሥነ ጥበብ፣ በባህልና በሳይንስ የምትታወቅ ከጀርመን በጣም አስፈላጊ ከተሞች አንዷ ነች። ሙኒክ ብዙ ሙዚየሞች፣ ቲያትሮች እና የጥበብ ጋለሪዎች ያሏት የባህል ማዕከል ነች። https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02etnwGEtwQL66tEoAjCHvRmKXYK4EDn97PmZ6d3ESZyPkBp6XvzJ8LLztgcwKui8nl
በአውሮፓ ዋንጫ ምሽት 4 ሰዓት ስፔን እና ጣልያን የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው
***************

የ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የሁለተኛ ዙር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ዛሬ ሲቀጥሉ ከቀኑ አስር ሰዓት ላይ ስሎቫኒያ ከሰርቢያ ጋር የጫወታሉ፡፡

ስሎቬኒያ በ4-4-2 ሰርቢያ በ3-5-2 አሰላለፍ ወደ ሚዳ ይገባሉ ተብሏል፡፡ ስሎቬኒያ በምድብ 3 ላይ 1 ነጥብ ሲኖራት ሰርቢያ ምንም ነጥብ የላትም፡፡

በምድብ 3 ምሽት አንድ ሰዓት ላይ ዴንማርክ ከእንግሊዝ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታም ይጠበቃል፡፡

ዴንማርክ ከእንግሊዝ በዶቼ ባንክ ፓርክ የሚያደርጉት ጨዋታ ዴንማርክ በ3-5-2 እንዲሁም እንግሊዝ 4-2-3 አሰላለፍ ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡ እንግሊዝ በ3 ነጥብ በምድቡ አናት ላይ ስትቀመጥ ዴንማርክ 1 ነጥብ አላት፡፡

በምድብ 2 ምሽት 4:00 ሰዓት ስፔን ከጣልያን በቬልቲንስ አሬና ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታም በእጅጉ ተጠባቂ ነው፡፡

ሁለቱም ሀገራት በምድቡ 3 እኩል ነጥብ ያላቸው በመሆኑ ዛሬ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ስፔን እና ጣልያን በተመሳሳይ በ4-3-3 አሰላለፍ ወደ ሜዳ ይገባሉ ተብሏል፡፡
Forwarded from ETV መዝናኛ
የኢትዮጵያ አይዶል ምዕራፍ 3 የፍጻሜ ተወዳዳሪዎች
በድምጽና በተውኔት ሲወዳደሩ የቆዩ ድንቅ ባለተሰጥኦዎች እንሆ ለፍፃሜው ደርሰዋል፡፡

የፊታችን እሁድ ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ ለአሸናፊነት ይፋለማሉ፡፡

ውድድሩ በመዝናኛ ቻናል፣ በዜና ቻናል፣ በዩቱብና የፌስቡክ ገጽ ይተላለፋል፡፡ የሚወዱትን ተወዳዳሪ በ8600 SMS በዕለቱ የሚሰጣቸውን ኮድ በማስቀደም መምረጥ ይችላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ያላትን የዲፕሎማሲ አቅም ይበልጥ ለማጎልበት ተተኪ ዲፕሎማቶች ላይ እየሰራች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ
******************

ኢትዮጵያ ያላትን የዲፕሎማሲ አቅም ይበልጥ ለማጠናከር እና ለማሳደግ ተተኪ ዲፕሎማቶች ላይ እየሰራች እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ገለፁ፡፡

ኢትዮጵያ የረጅም ግዜ ታሪክ፣ ባህል፣ ስልጣኔ እና ጥንታዊ ህዝቦች መኖሪያ እንደመሆኗ በወቅቱ ከነበሩ ሀገራት እና ህዝቦች ጋር ግንኙነት ነበራት ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ይህም ጥንታዊ የሆነ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ካላቸው ሀገራት አንዷ እንድትሆን ማድረጉን ይገልፃሉ፡፡

የዓድዋ ድልን ተከትሎ ሀገራችን ያገኘችው እውቅና ሌሎች ሀገራት ከእርሷ ጋር የዲፕሎማሲ ግንኙነት የመመስረት ፍላጎትን ያመጣ እንደነበርም ነው የገለፁት፡፡

በ1900 ዓ.ም የተቋቋመው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ ቅርፅ አስይዞታል የሚሉት ቃል አቀባዩ፤ ከዚያ ወቅት ጀምሮ የንግድ እና የወታደራዊ ቅርፅን የተላበሱ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶች መዘውተራቸውንም ያነሳሉ፡፡
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid09kSWZ3HdDGaChuH9dG4TvUgVcUX9nXTRVQSLLd2n4ANLRtif7EGTafHU2T6k3GwNl