EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
121K subscribers
8.74K photos
40 videos
78 files
8.33K links
Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC)
Download Telegram
በዘንድሮው የረመዳን ጾም ዋጋው አልቀመስ ያለው ቴምር
**************

በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው የረመዷን ጾም መግባትን ተከትሎ በተለይ ለአፍጥር በስፋት ለገበያ የሚቀርበው ቴምር ዋጋ በቀናት ልዩነት ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ኢቢሲ ያነጋገራቸው ሸማቾች ገልፀዋል።

በመርካቶ አካባቢ ተዘዋውሮ የቴምር ገበያውን ቅኝት ያደረገው የጋዜጠኞች ቡድንም ቴምር በአማካኝ በኪሎ እስከ 300 ብር ሲሸጥ ለመመልከት ችሏል።

በዛሬው እለት የተጀመረው የ1 ሺህ 444ኛው ዓመተ ሒጅራ የረመዷን ጾም መግባትን ተከትሎ በተለያዩ ሸቀጦች ላይ የታየውን የዋጋ ንረት የተመለከቱ ጥቆማዎች በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በስፋት እየታዩ መሆኑን ተከትሎ የጋዜጠኞች ቡድን ወደ መርካቶ ተንቀሳቅሷል።

በመርካቶ ቴምር ሲሸምቱ ያገኘናቸው እና በሳኡዲ አረቢያ ለበርካታ አመታት ኗሪ የነበሩት አቶ ማህሙድ ሱሌማን ዘንድሮ ቴምር ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ጠቁመዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02UmrsCzaou1DTpiocHauo6QbZfSm34Lfj8pwAGvLUEXfhT4XBhWkrs4LPpq9mXjkDl
ዋሊያዎቹ ከጊኒ ጋር ዛሬ ምሽት 5፡30 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ
**********************

በአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ምሽት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ምሽት 5፡30 ጨዋታውን ያደርጋል።

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በኮትዲቯር አስተናጋጅነት በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ ከጊኒ ጋር የሚያደርገውን የማጣሪያ ጨዋታ 46 ሺህ ተመልካች በሚይዘው ካዛብላንካ መሐመድ 5ኛ ስታዲየም ያከናውናል።

በጨዋታው ላይ በዋሊያዎቹ በኩል በሁለት ቢጫ ምክንያት ከጨዋታ ውጭ ከሆነው ምኞት ደበበ ውጪ ሌሎቹ ተጫዋቾቹ ከጉዳትና ቅጣት ነጻ መሆናቸውን ታውቋል።

የሁለቱን አገራት ጨዋታ ቤኒናዊው ዋና አልቢትር ጂንዶ ልዊስ ሆንግናንዳንዴ የሀገራቸው ልጆች ከሆኑት ረዳቶች ኤሪክ አያማቮ እና ጊብማሲዬንዳን ኮዉቶን እንዲሁም ከአራተኛ ዳኛው አዲሳ ሊጋሊ ጋር በጋራ ይመሩታል።

ኢትዮጵያ እና ጊኒ ሁለተኛ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታቸውን የፊታችን ሰኞ መጋቢት 18 በሞሮኮ መሐመድ አምስተኛ ስታዲየም ያደርጋሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አራት ከግብጽ፣ ከማላዊ እና ከጊኒ ጋር የተደለደለ ሲሆን እስካሁን ባደረጋቸው ሁለት ጨዋታዎች በሶስት ነጥብ እና በአንድ የግብ ክፍያ ምድቡን እየመራ ይገኛል።

ዋልያዎቹ በሚገኙበት ምድብ የሚገኙት ግብጽ እና ማላዊ ዛሬ ከምሽቱ 4 ሰዓት ጨዋታቸውን የሚያድረጉ ይሆናል።
የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪቶችን ህገወጥ አካሄድ ለማስቀረት የኦንላይን አሰራር መተግበር ተጀምሯል ፡- የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር
*****************************

በመንግስት በሚደረጉ የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪቶች ላይ የሚታዩ ህገ ወጥ አሰራሮችን ለማስቀረት በኦንላይን አንዲፈፀም መደረጉን የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቋል፡፡

የስራ ስምሪቱን ከምዝገባው ጀምሮ በቴክኖሎጂ በማገዝ ከሰው ንክኪ ነፃ በማድረግ ህገ ወጥነትን ለማስቀረት የተጀመረ ስራ ውጤት በማሳየት ላይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አስታውቀዋል።

በሚኒስቴሩ የኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ አበበ ዓለሙ ለኢቢሲ ሳይበር እንደገለፁት ባለፉት ስድስት ወራት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰፊ የአሰራር ማሻሻያ ከተደረገባቸው ዳይሬክቶሬቶች መካከል የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ዘርፍ አንዱ ነው፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን አማራጭ የስራ እድል ለመጠቀም ዓለም አቀፍ የስራ ገበያን የሚያፈላልግ የስራ ክፍል ተቋቁሞ እየሰራ መሆኑንም ሀላፊው ጠቁመዋል፡፡https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02TgxQ9VVizuHFigFdAwPFHoyXbp7YZgwVdneEhqSY9M3iSWwdyDf9UtNZUXSuiGVVl
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ለብሔራዊ ቡድን 197 ጊዜ በመሰለፍ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዘገበ
*****************************

ፖርቹጋላዊው አጥቂ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለብሔራዊ ቡድን 197 ጊዜ በመሰለፍ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል፡፡

የ38 ዓመቱ አጥቂ ትናንት ምሽት ሀገሩ ፖርቹጋል ሌችተንስታይንን 4 ለ 0 ባሸነፈችበት ጨዋታ በመሰልፍ ሁለት ጎሎችን በቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡

በጨዋታው መሰለፉን ተከትሎ ሮናልዶ ለሀገሩ 197 ጨዋታዎችን በማድረግ ለብሔራዊ ቡድን በርካታ ጨዋታዎችን በማድረግ በኩዌቱ አጥቂ ባድር አል ሙታዋ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን አሻሽሏል፡፡

በተጨማሪም ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከ2004 ጀምሮ ለ20 ተከታታይ አመታት ለፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ግብ ማስቆጠር የቻለ ብቸኛ ተጫዋች ሲሆን በዓለም አቀፍ ውድድሮች ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 120 ማድረስ ችሏል፡፡

በትናንትናው ጨዋታም 60ኛ የቅጣት ምት ጎሉን በስሙ አስመዝግቧል፡፡

ለሳዑዲው አልናስር የሚጫወተው ሮናልዶ በቀድመው የፖርቹጋል አሰልጣኝ ፈርናንዶ ሳንቶስ የቋሚ አሰላለፍ እድል ተነፍጎት የነበረ ሲሆን በአዲሱ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ደግሞ የቡድኑ አምበል እና ቋሚ ተሰላፊ መሆን ችሏል፡፡
በሽሮና በርበሬ ውስጥ አደንዛዥ ዕፅ ደብቆ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ የሞከረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
************

በሽሮና በርበሬ ውስጥ አደንዛዥ ዕፅ ደብቆ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ የሞከረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።

ግለሰቡ በቁጥጥር ስር የዋለው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው መርካቶ ጣና የገበያ ማዕከል አካባቢ በሚገኝ ፖስታ ቤት ውስጥ ነው።

ተጠርጣሪው ማንም ሰው በማይገምትበት ሁኔታ ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ ዕፅ በሽሮና በርበሬ ውስጥ ደብቆ በካርቶንና በፌስታል በማሸግ ወደ እንግሊዝ ለንደን በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ለመላክ ሙከራ ሲያደርግ በፖስታ አገልግሎት ቅርንጫፍ ሰራተኞቹ የተጠናከረ ፍተሻ ሊታወቅ መቻሉንና ፖሊስ በፍጥነት ወደ ስፍራው በመሄድ ግለሰቡን ከነኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ መጀመሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0tgq9AZtwJWbX5ERGtYYF9nsGFYKikWvrGzCpwvXJCiahth91dGzftDeF6J2JcUAMl
ከጎረቤት ሀገር ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያን በማስገባት ላይ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ
**********************************

ከጎረቤት ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ህገ - ወጥ የጦር መሣሪያን በማስገባት ላይ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።

ብሬን እና ክላሽንኮቭ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያን ከመሰል ጥይቶች ጋር ከጎረቤት ሀገር ጭነው በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ሀመር ወረዳ የኦሞ ወንዝን በጀልባ በማሻገር በሞተር ሳይክል እየጫኑ እንዳሉ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ማዕከላዊ ወንጀል ኢንተለጀንስ ከአካባቢው ፖሊስና ኅብረተሰብ ጋር በመተባበር ባደረገው ኦፕሬሽን አራት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

በተመሳሳይ፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአካባቢው ፖሊስና ኅብረተሰብ ጋር ባደረገው ኦፕሬሽን በአማራ ክልል የተለያዩ ሽጉጦች፣ ዘጠኝ ክላሽንኮቭ፣ 13 ቦምቦች እና የተለያዩ በርካታ ጥይቶች በህገ-ወጥ መንገድ ሲያዘዋውሩ የነበሩ ስድስት ተጠርጣሪዎችን ከነ-ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid08nAFYZEQemKkqQ99A83mWDMjscrC1Z5VRtNVGkc6JrBfsDqzgePz2ye9Q869jvcGl
በረመዳን ዋጋው አልቀመስ ያለው ቴምር
***************
በሕዝበ ሙስሊሙ ዘንድ በየዓመቱ በጉጉት የሚጠበቀው የረመዷን ጾም መግባትን ተከትሎ በተለይ ለአፍጥር በስፋት ለገበያ የሚቀርበው ቴምር ዋጋ በቀናት ልዩነት ከፍተኛ ጭማሪ ማሳየቱን ኢቢሲ ያነጋገራቸው ሸማቾች ገልፀዋል። https://www.youtube.com/watch?v=Jom7Lq3EWak
በቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር አትሌት መዲና ኢሳ አሸናፊ ሆነች
********************************

የቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን በአትሌት መዲና ኢሳ አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን ፅጌ ገብረ ሰላማ ሁለተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን ጨርሳለች።

የዘንድሮው ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት የሚካሄደው ይህ ሩጫ መነሻ እና መድረሻውን አዲስ አበባ ቦሌ አትላስ አካባቢ አድርጎ እየተካሄደ ነው ።

በውድድሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ኋይሌ ገብረ ሥላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ አትሌት ለተሰንበት ግደይን ጨምሮ የተለያዩ አትሌቶችና እንግዶች ተገኝተዋል።

የ2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎሜትር ሩጫ ”ቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄ” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው በዚህ ውድድር አትሌቶች፣ 15 ሺህ የጤና ሯጮች፤ እንዲሁም አምባሳደሮች እየተሳተፉ ነው።

በአትሌቶች መካከል በሚደረገው ፉክክር ለአንደኛ ደረጃ 70 ሺህ ብር፣ ለሁለተኛ ደረጃ 45 ሺህ ብር እንዲሁም ለሦስተኛ ደረጃ 30 ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል።
ከሚያሽከረከረው ባጃጅ ላይ የተረሳ 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ
*****************

በድሬዳዋ ከተማ ከሚያሽከረከረው ባጃጅ ላይ የተረሳ 150ሺህ ብር ለባለቤቱ የመለሰው የባጃጅ አሽከርካሪ አድናቆት እየተቸረው ይገኛል።

መኮንን ግርማ ኑሮን ለማሸነፍ እና የነገውን ተሰፋ ብሩህ ለማድረግ ባጃጅ ላይ ተቀጥሮ የሚሰራ ወጣት ነው።

ወጣቱ መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም እንደተለመደው ለስራ በድሬዳዋ ጎዳና ላይ ከምሽቱ ሶስት ሰአት ላይ ባጃጁን እያሽከረከረ ሳለ የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ መሀመድ ዑስማን ከሳቢያን ወደ ኦርቢት ለመሄድ በሱ ባጃጅ ተሳፍረው ወደተባለው ቦታ ማድረሱን ተናግራል።

ይህ ከሆነ ከአንድ ሰአት በኋላ ስልክ ተደውሎ ባጃጁ ላይ ገንዘብ ወድቆ እንደሆነ እና እንድመለከት ተነገረኝ የሚለው ወጣቱ፤ ከተሳፋሪ ወንበር ላይ ዞሬ ስመለከት በላስቲክ የተጠቀለለ በርካታ ብር ተቀምጦ ማግኘቱን እና ወዲያው ገንዘቡን ይዞ ወደ ድሬዳዋ ፖሊስ ትራፊክ ዳሬክቶሬት በመምጣት 150ሺህ ብሩን ለባለቤቱ መመለሱን ተናግሯል።

ገንዘቡን ለባለቤቱ መመለሱ እንዳስደሰተው የተናገረው ወጣቱ፣ የራስ ያልሆነ ገንዘብ ለግል መጠቀም የህሊና ቁስል በመሆኑ በራስ ወዝ ብቻ ሀብት ማፍራት እንደሚገባ መናገሩን ከድሬዳዋ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።

ገንዘባቸው የተመለሰላቸው አቶ መሐመድ ዑስማን በበኩላቸው፤ ገንዘባቸው በጠፋ በአንድ ሰዓት ውስጥ የተሳፈሩበትን የምሽት ባጃጅ የጎን ቁጥር ለትራፊክ ፖሊስ በመናገር በፍጥነት ገንዘባቸው በመገኘቱ መደሠታቸውን ገልፀው፣ ለድሬዳዋ ትራፊክ ቁጥጥር ዳሬክቶሬት እና ለወጣት መኮንን ግርማ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።