EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
138K subscribers
31.8K photos
323 videos
79 files
12.3K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
ከታሪፍ በላይ በማስከፈልና ትርፍ በመጫን ህዝብን ያማረሩ 247 ግለሰቦች ርምጃ ተወሰደባቸው
****************

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከአስሩም የክላስተር ከተሞች ተነስተው ወደ አዲስ አበባ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ሕግ እና ሥርዓት ያላከበሩ 247 ግለሰቦች ላይ ርምጃ መወሰዱን የክልሉ የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ገለፀ፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የመሰረተ ልማት አስተባባሪና የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑሪዬ (ዶ/ር) ከኢቢሲ ዶትስትሪም ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ በተወሰደው ርምጃ 14 የአሽከርካሪዎች ማህበራት ተቀጣሪዎች መባረራቸውን ተናግረዋል፡፡

10 የስምሪት ባለሙያዎችና ሌሎች የትራፊክ ቁጥጥር ባለሙያዎች የእርምት ርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡

ከታሪፍ በላይ በማስከፈልና ትርፍ በመጫን ህዝብን ባማረሩ 247 ግለሰቦች ላይ የተወሰደ ርምጃ
አማድ ዲያሎ ወደ ሜዳ ሊመለስ ነው
**********

ወሳኙ የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋች አማድ ዲያሎ ካጋጠመው ከባድ ጉዳት በማገገም በግሉ ልምምድ ማድረግ የጀመረ ሲሆን ከሰኞ ጀምሮ ወደ መደበኛ የቡድን ልምምድ እንደሚመለስ ታውቋል፡፡

አማድ ዲያሎ ባጋጠመው ጉዳት ከውድድር ዓመቱ ውጪ ሆኗል ተብሎ የነበረ ቢሆንም ከተጠበቀው ጊዜ ፈጥኖ ማገገም ችሏል፡፡

በዘንድሮው የውድድር ዘመን ለማንችስተር ዩናይትድ ወሳኝ ከሚባሉት ተጨዋቾች አንዱ የሆነው አማድ ዲያሎ ለማንችስተር ዩናይትድ በወሳኝ ሰዓት ወደ ሜዳ መመለሱ ጥሩ ዜና ነው ተብሏል፡፡

በዩሮፓ ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ ከአትሌቲክ ቢልባኦ ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ የመድረስ እድል እንዳለውም ተገልጿል።

በሀብተሚካኤል ክፍሉ


የስፖርት ፌስቡክ ገፅን ይወዳጁ

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
“የጋራ የሆኑ ብዙ ሚነገሩ ታሪኮች አሉን” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

(መስከረም 29, 2016 ዓ.ም. በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ አውደ ርዕይ መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ያደረጉት ንግግር)

#PMOEthiopia

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW
የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ
****************

የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ለሁለት ቀናት የሚያካሂደውን መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ ከሰዓት በኋላ ጀምሯል።

ኮሚቴው በዚህ ስብሰባው ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊና የፓርቲ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት እና የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ስብሰባውን አስመልከቶ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክት፤ "ከዛሬ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በሀገራዊ ቁልፍ ጉዳዮች እንዲሁም በፓርቲ ተኮር ጭብጦች ላይ ለመጪዎቹ ሁለት ቀናት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል" ብለዋል፡፡

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW
ከዛሬ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ የብልጽግና ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በሀገራዊ ቁልፍ ጉዳዮች እንዲሁም በፓርቲ ተኮር ጭብጦች ላይ ለመጪዎቹ ሁለት ቀናት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW
“ለ8 ሰዓታት ብቻ በመሥራት በንግዱ ማኅበረሰብ ዘንድ አመርቂ ዕድገት ማስመዝገብ አይቻልም” - የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ
****************************


በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያደርገው ደንብ ለማኅበረሰቡ አዲስ የሥራ ባህል የሚያላብስ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ ገለጹ።

“የከተማ ልማት እና የንግዱ እንቅስቃሴ የአንድ ሣንቲም ሁለት ገፅታ ናቸው” ያሉት ኃላፊዋ፣ መዲናዋ በለውጥ የተላበሰችው ገፅታ አዲስ አሠራር፣ ዘመናዊ እና ያደገ የንግድ ማኅበረሰብን የሚፈልግ ነው ሲሉ ለኢቢሲ ዶትስትሪም ገልጸዋል።

የንግድ እና ትራንስፖርት የምሽት አገልግሎት

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW
ማሜሎዲ ሰንዳውስ እና ፒራሚድስ ለፍጻሜ ደረሱ

በካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ማሜሎዲ ሰንዳውስ አል አህሊን በማሸነፍ ለፍጻሜ ደርሷል።

በካይሮ ኢንተርናሽናል ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ የደቡብ አፍሪካው ክለብ ሰንዳውስ ከአል አህሊ አንድ አቻ ተለያይቷል።

ሁለቱ ቡድኖች ፕሪቶሪያ ላይ የተገናኙበት ጨዋታ 0 ለ 0 መጠናቀቁን ተከትሎ ማሜሎዲ ሰንዳውስ ከሜዳ ውጭ ባገባ በሚለው ህግ ለፍጻሜ የደረሰበትን ውጤት አስመዝግቧል።

የ12 ጊዜ የካፍ ሻምፒዮንስ ሊግ አሸናፊው አል አህሊ ከ2021 በኋላ ሰንዳውስን ማሸነፍ አልቻለም።

በዚያው በግብፅ በተደረገ ሌላ የግማሽ ፍጻሜ የመልስ ጨዋታ ፒራሚድስ ኦርላንዶ ፓይሬትስን 3 ለ 2 አሸንፎ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል።

የግብጹ ክለብ ፒራሚድስ በታሪኩ ለመጀመርያ ጊዜ በሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ ሲደርስ ኦርላንዶ ፓይሬትስ 2ኛ ዋንጫውን ለማሳካት ቢቃረብም ለፈጻሜ ሳይደረስ ቀርቷል።

በፍጻሜው ፒራሚድስ ከማሜሎዲ ሰንዳውስ የሚገናኙ ይሆናል።

በአንተነህ ሲሳይ

የስፖርት ፌስቡክ ገፅን ይወዳጁ

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW
የአንቾሎቲ 31ኛ የፍጻሜ ጨዋታ ኤል

እስከ 700 ሚሊየን የእግር ኳስ አፍቃሪ የሚከታተለው  ከእግር ኳስም ከፍ ያለ ባላንጣነት፡፡

በአንድ ሀገር ውስጥ የሚገኙ ሁለት ሀገራት የሚያደርጉት ጨዋታ ነው ይሉታል፡፡ ሪያል ማድሪድ ከባርሴሎና ኤል ክላሲኮ::   

የዋና ከተማዋ ማደሪድ ትክክለኛ ተወካይ እኔ ነኝ በሚለው ሪያል ማድሪድ እና የካታላን ብሔርተኝነት ምልክት ሆኖ በተሳለው ባርሴሎና መካከል የሚደረገው ደርቢ  ከእግር
ኳስ ከፍ ያለ ነው::

የስፔን ፖለቲካ  ጭምር የሚቀነቀንበት ሆኖ አመታትን ቢያልፍም ሁሌም እንደ አዲስ የሚጠበቅ ጨዋታንም ሀሳብንም ለማሸነፍ የሚደረግ ብርቱ ትግል፡፡

የአኗኗርም የባህልም የመደብም ልዩነት የሚስተዋልበት ደርቢ 120 አመታትን ሲሻገር አሁን ደግሞ በስፔን የንጉስ ዋንጫ ፍጻሜ ተፋጠዋል፡፡

በግማሽ ፍጻሜው ሌላኛውን የማድሪድ ክለብ አትሌቲኮን አሸንፎ የመጣው ባርሴሎና እና ሪያል ማድሪድ የሚገናኙበት 260ኛው ደርቢ ዛሬ  በሴቪያ ይደረጋል፡፡

በሁሉም የጨዋታ ክፍል ከዋክብትን የሰበሰቡት አሰልጣኝ ካርሎ አንቾሎቲ ይሔኛው መርሀ ግብር ምን አልባትም የመጨረሻቸው ሊሆን ይችላል፡፡

በስፔን የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ክብሩን በባርሴሎና የተነጠቁት ሰው አመቱን ካለ ዋንጫ ላለማጠናቀቅ አሁን የቀራቸው ነገር ቢኖር የኮፓ ደልሬይ እና የሊጉ ዋንጫ ብቻ ነው፡፡

ነገር ግን የሁለቱም ክብሮች እንቅፋት
ሆኖ ከፊታቸው የቆመው የምንጊዜም ተቀናቃኛቸው ባርሴሎና መሆኑ ሲታሰብ የአንጋፋውን ሰው የማድሪድ ቆይታ ያበቃለት ያስመስለዋል፡፡

ካርሎ አንቾሎቲ  ሎስ ብላንኮዎቹን በድጋሜ ከተረከቡ በኋላ ካደረጓቸው 11 የፍጻሜ ጨዋታዎች ዘጠኙን ሲያሸንፉ   በሁለቱ የተሸነፉት በባርሴሎና ነው።

ይህ ደግሞ  አንጋፋው አሰልጣኝ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የካታላኑ ክለብ ሁነኛ ፈተናቸው ስለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡  

30 አመትን በተሻገረው የአሰልጣኝነት ዘመናቸው ለ30 ፍጻሜዎች ደርሰው በ5ቱ ብቻ የተሸነፉት ጣልያናዊ  በ31ኛው ደግሞ በዚህ አመት ግንኙነታቸው ፍጹም ብልጫ ከወሰደባቸው ክለብ ይገናኛሉ፡፡

ባርሴሎናን በተረከቡበት የመጀመርያው አመታቸው 4 ዋንጫዎችን ለማሳካት ጥሩ ግስጋሴ ላይ የሚገኙት ጀርመናዊው አሰልጣኝ ሀንሲ ፍሊክ በሊጉ ወደ ሳንቲያ ቤርናባው አምርተው 4 ለ 0 አሸንፈው ሲመለሱ ሪያድ ላይ ባደረጉት  የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ ፍጻሜም 5 ግቦችን አስቆጥረው በማድሪድ ላይ ያላቸውን የበለይነት አሳይተዋል፡፡ 

በፍጻሜ ጨዋታዎች ተሸንፈው የማያውቁት የ60 አመቱ አሰልጣኝ  7ኛ የፍጻሜ ጨዋታቸውን በድል ለማጠናቀቅ አስቸጋሪ ጊዜ እያሳለፈ  የሚገኘውን ማድሪድ ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡

በ4 '3' 3 እና 4' 2'3'1 የጨዋታ መንገድ በወጣቶቹ አስፈሪ ቡድን ለመገንባት ሌላ አመት ያላስፈለጋቸው ሀንሲ ፍሊክ ከአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች የእሳቸውን ቡድን ያክል ግብ ያስቆጠረ የለም፡፡ 

በሮበርት ሌቫንዶቭስኪ ላን ያማል እና ራፊናህ የሚመራው የፊት መስመር በሊጉ 89 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡

እንደ አስፈላጊነቱ ተጫዋቾችን በመቀያር የሚጠቀሙት ፍሊክ በመከላካሉ መጠነኛ ድክመት ቢኖርባቸው በርካታ የግብ ዕድሎችን በሚፈጥረው የአማካይ ክፍላቸው ከሁለት እና ከ3 በላይ ግቦችን በማስቆጠር ልዩነት የፈጠሩባቸው ጨዋታዎች ቀላል አይደሉም፡፡

በጉዳትም ባለመረጋጋትም እየታመሰ የሚገኝው የሪል ማድሪድ የተከላካይ ክፍል በስፔን ኮፓ ደልሬም አስፈሪውን የባርሴሎና የፊት መስመር እንቅስቃሴ ለማስቆም ትልቅ የቤት ስራ ይጠብቀዋል፡፡

በጨዋታው ሮቤርት ሎቫንዶቭስኪ በጉዳት ከስብስቡ ውጭ ሲሆን  በማድሪድ በኩል ኢድዋርዶ ካማቪንጋ እና ደቪድ አልባ በጉዳት የማይሰለፉ ተጫዋቾች ናቸው።

ባርሴሎና ለ32ኛ ጊዜ ማድሪድ ደግሞ ለ21ኛ ጊዜ የስፔን የንጉሱ ዋንጫን ለማንሳት የሚገናኙበት ጨዋታ ምሽት 5 ሰአት ላይ ይጀመራል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

የስፖርት ፌስቡክ ገፅን ይወዳጁ

ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ

ኢቢሲ ድረ ገፅ

https://t.me/EBCNEWSNOW