ተጠባቂው የዩሮፓ ሊግ ፍፃሜ ማንችስተር ዩናይትድ ከ ቶተንሃም ሆትስፐር
*********************
የዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ሲደረግ ማንችስተር ዩናይትድ ከ ቶተንሃም ሆትስፐር ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
በስፔን ምድር በአትሌቲክ ቢልባኦ ሜዳ ሳንማሜስ የሚደረገው ይህ የፍፃሜ ጨዋታ ለሁለቱም ቡድኖች እጅግ አስፈላጊ ነው።
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ደካማ የውድድር ዓመት ያሳለፉት ሁለቱም ቡድኖች፤ ዋንጫውን ማሸነፍ አንድም ለቀጣይ ዓመት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ በሌላ በኩል በውድድር ዓመቱ የተከፋውን ደጋፊ ለመካስ ያላቸው ብቸኛ ተስፋ ነው።
ማንችስተር ዩናይትድ ምንም ጨዋታ ሳይሸነፍ ለፍፃሜ ጨዋታ የደረሰ ሲሆን ዛሬ የፍፃሜው ጨዋታ በሚደረግበት ሳንማሜስ አትሌቲክ ቢልባኦን 3 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል።
በ2017 በጆዜ ሞሪንሆ እየተመራ አያክስን አሸንፎ የዩሮፓ ሊግ አሸናፊ የነበረው ማንችስተር ዩናይትድ፤ በሌላኛው ፖርቹጋላዊ ሩበን አሞሪም እየተመራ ዋንጫውን ያሳካው ይሆን የሚለው የሚጠበቅ ሆኗል።
ቶተንሃም በሊጉ ደካማ የውድድር ዓመት ያሳለፈ ቢሆንም፤ በዩሮፓ ሊግ አሸንፎ የመጣቸው ቡድኖች ቡድኑ በዩሮፓ ሊግ የነበረውን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው።
የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ቶተንሃም 2ጊዜ ማንሳት የቻለ ሲሆን ማንችስተር ዩናይትድ 1ጊዜ የዋንጫው አሸናፊ ሆኗል።
በሀ/ሚካኤል ክፍሉ
ኢቢሲ የስፖርት ገፅ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
*********************
የዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ሲደረግ ማንችስተር ዩናይትድ ከ ቶተንሃም ሆትስፐር ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
በስፔን ምድር በአትሌቲክ ቢልባኦ ሜዳ ሳንማሜስ የሚደረገው ይህ የፍፃሜ ጨዋታ ለሁለቱም ቡድኖች እጅግ አስፈላጊ ነው።
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ደካማ የውድድር ዓመት ያሳለፉት ሁለቱም ቡድኖች፤ ዋንጫውን ማሸነፍ አንድም ለቀጣይ ዓመት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ በሌላ በኩል በውድድር ዓመቱ የተከፋውን ደጋፊ ለመካስ ያላቸው ብቸኛ ተስፋ ነው።
ማንችስተር ዩናይትድ ምንም ጨዋታ ሳይሸነፍ ለፍፃሜ ጨዋታ የደረሰ ሲሆን ዛሬ የፍፃሜው ጨዋታ በሚደረግበት ሳንማሜስ አትሌቲክ ቢልባኦን 3 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል።
በ2017 በጆዜ ሞሪንሆ እየተመራ አያክስን አሸንፎ የዩሮፓ ሊግ አሸናፊ የነበረው ማንችስተር ዩናይትድ፤ በሌላኛው ፖርቹጋላዊ ሩበን አሞሪም እየተመራ ዋንጫውን ያሳካው ይሆን የሚለው የሚጠበቅ ሆኗል።
ቶተንሃም በሊጉ ደካማ የውድድር ዓመት ያሳለፈ ቢሆንም፤ በዩሮፓ ሊግ አሸንፎ የመጣቸው ቡድኖች ቡድኑ በዩሮፓ ሊግ የነበረውን ጥንካሬ የሚያሳይ ነው።
የዩሮፓ ሊግ ዋንጫን ቶተንሃም 2ጊዜ ማንሳት የቻለ ሲሆን ማንችስተር ዩናይትድ 1ጊዜ የዋንጫው አሸናፊ ሆኗል።
በሀ/ሚካኤል ክፍሉ
ኢቢሲ የስፖርት ገፅ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
የልጆችን አዕምሯዊ እድገት የሚያጎለብት የመጫወቻ መተግበሪያ ያበለፀጉት ጓደኛሞች
*******************
በ4 ጓደኛሞች በ2011 ዓ.ም የተመሰረተው ‘እንጫወት ጌምስ’፤ የተለያዩ ሀገራዊ ይዘት ያላቸው እና የልጆችን አዕምሯዊ እድገት የሚያግዙ መተግበሪያዎች በማለጸግ ላይ መሆኑን ጓደኛሞቹ ይናገራሉ።
‘ማሞ’ የሚል ስያሜን የያዘ የመጀመሪያ ስራቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ የተለያዩ የቢዝነስ ስልጠናዎችን በመውሰድ፤ በርከት ያሉ የመጫወቻ መተግበሪያዎች ማበልፀግ መቻላቸውንም ይገልፃሉ።
እ.ኤ.አ በ2023 የአፍሪካን ጌምስ ዊክ፣ አፍሪካን ዩዝ ኮኔክት ፣ የአፍሪካን ጌማቶን እና ሌሎችም ዓለምአቀፍ እና ሀገር አቀፍ መድረኮች ላይ በመሳተፍ እና እውቅና ማግኘትም ችለዋል።
መተግበሪያዎቹ ከትምህርታዊ እገዛ ባሻገር ማኅበራዊ እሴትን የሚያስተምሩ እና ልጆች እየተዝናኑ እውቀት ሊጨብጡባቸው የሚችሉበት መሆኑም ይናገራሉ።
በቀጣይ ‘እንጫወት ልጆች’ እና ‘የፊደላት አሸናፊ’ የሚል ልጆችን ማንበብ እና መፃፍ እንዲችሉ እና እንዲያጎለብቱ የሚረዳ ኢትዮጵያዊ ይዘት ያለው መተግበሪያ በማበልፀግ ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
በአፎሚያ ክበበው
#ebc #etv #ebcdotstream #ebcnews #kidsgame #coding
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
*******************
በ4 ጓደኛሞች በ2011 ዓ.ም የተመሰረተው ‘እንጫወት ጌምስ’፤ የተለያዩ ሀገራዊ ይዘት ያላቸው እና የልጆችን አዕምሯዊ እድገት የሚያግዙ መተግበሪያዎች በማለጸግ ላይ መሆኑን ጓደኛሞቹ ይናገራሉ።
‘ማሞ’ የሚል ስያሜን የያዘ የመጀመሪያ ስራቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ የተለያዩ የቢዝነስ ስልጠናዎችን በመውሰድ፤ በርከት ያሉ የመጫወቻ መተግበሪያዎች ማበልፀግ መቻላቸውንም ይገልፃሉ።
እ.ኤ.አ በ2023 የአፍሪካን ጌምስ ዊክ፣ አፍሪካን ዩዝ ኮኔክት ፣ የአፍሪካን ጌማቶን እና ሌሎችም ዓለምአቀፍ እና ሀገር አቀፍ መድረኮች ላይ በመሳተፍ እና እውቅና ማግኘትም ችለዋል።
መተግበሪያዎቹ ከትምህርታዊ እገዛ ባሻገር ማኅበራዊ እሴትን የሚያስተምሩ እና ልጆች እየተዝናኑ እውቀት ሊጨብጡባቸው የሚችሉበት መሆኑም ይናገራሉ።
በቀጣይ ‘እንጫወት ልጆች’ እና ‘የፊደላት አሸናፊ’ የሚል ልጆችን ማንበብ እና መፃፍ እንዲችሉ እና እንዲያጎለብቱ የሚረዳ ኢትዮጵያዊ ይዘት ያለው መተግበሪያ በማበልፀግ ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።
በአፎሚያ ክበበው
#ebc #etv #ebcdotstream #ebcnews #kidsgame #coding
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያገኘው ሽልማት
************************
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዱባይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ ሽልማት አግኝቷል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሰራቸው የለውጥ ስራዎች ያገኘውን ሽልማት በሚመለከት ለሚዲያ ተቋማት መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫውም ማህበረሰቡን የሚያሳትፍና ወንጀልን መከላከል የሚያስችል ምርጥ የፖሊስ መተግበሪያ ዘርፍ፤ አንደኛ ደረጃ በመያዝ ሽልማት ማግኘቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቋል።
መተግበሪያው በማህበረሰቡ ተሳትፎ ወንጀልን ለመከላከል የሚያስችል ሲሆን፤ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው የተፈጠሩ ወንጀሎችን መረጃ መላክ የሚያስችላቸው እንደሆነ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስም የሰራው መተግበሪያ ከ130 ተወዳዳሪዎች አንደኛ በመውጣት መሸለሙም በመግለጫው ተጠቁሟል።
በሰጦ ተሾመ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
************************
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በዱባይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የፖሊስ ጉባኤ ላይ ሽልማት አግኝቷል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሰራቸው የለውጥ ስራዎች ያገኘውን ሽልማት በሚመለከት ለሚዲያ ተቋማት መግለጫ ሰጥቷል።
በመግለጫውም ማህበረሰቡን የሚያሳትፍና ወንጀልን መከላከል የሚያስችል ምርጥ የፖሊስ መተግበሪያ ዘርፍ፤ አንደኛ ደረጃ በመያዝ ሽልማት ማግኘቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቋል።
መተግበሪያው በማህበረሰቡ ተሳትፎ ወንጀልን ለመከላከል የሚያስችል ሲሆን፤ ዜጎች ካሉበት ቦታ ሆነው የተፈጠሩ ወንጀሎችን መረጃ መላክ የሚያስችላቸው እንደሆነ ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስም የሰራው መተግበሪያ ከ130 ተወዳዳሪዎች አንደኛ በመውጣት መሸለሙም በመግለጫው ተጠቁሟል።
በሰጦ ተሾመ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሁለቱ ውሳኔዎች
**************
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት በቨርቹዋል ባካሄደው 45ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።
በዚሁ መሠረት፦
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ እያደገ ከመጣው የዘርፉ ፍላጎት አንፃር መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግል ዘርፉን፣ የሕብረት ሥራ ማሕበራትንና የሙያ ማሕበራትን ማሳተፍ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን የሥርዓተ ምህዳር ክፍያ አሰራርን የተመለከተ የህግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ወጥ ባልሆነ አሰራር በተለያዩ አካላት ሲተገበር ቆይቷል። አሁን በደረስንበት የእድገት ደረጃ የፌዴራል እና የክልል ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ከግምት ውስጥ ያስገባ የህግ ማዕቀፍ መኖር አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
#PMOEthiopia #ebcdotstream #Etv #EBC
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
**************
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት በቨርቹዋል ባካሄደው 45ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ።
በዚሁ መሠረት፦
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎት በመንግሥት ብቻ ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ እያደገ ከመጣው የዘርፉ ፍላጎት አንፃር መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን፣ የግል ዘርፉን፣ የሕብረት ሥራ ማሕበራትንና የሙያ ማሕበራትን ማሳተፍ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን የሥርዓተ ምህዳር ክፍያ አሰራርን የተመለከተ የህግ ማዕቀፍ ባለመኖሩ ወጥ ባልሆነ አሰራር በተለያዩ አካላት ሲተገበር ቆይቷል። አሁን በደረስንበት የእድገት ደረጃ የፌዴራል እና የክልል ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ከግምት ውስጥ ያስገባ የህግ ማዕቀፍ መኖር አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
#PMOEthiopia #ebcdotstream #Etv #EBC
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
ማስታወቂያ
**
የባንካችን ዲያስፖራ አካውንት አገልግሎት ግዜና ቦታ ሳይገድብዎ በኦንላይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለዚሁ አገልግሎት ባመቻቸው ድህረ-ገጽ ወይም መተግበሪያ ወይም በሲንቄ ባንክ ድህረ-ገጽ በኩል በመክፈት ፈጣን እና ምቹ አገልግሎት ያግኙ፡፡
Open our bank's efficient and accessible Diaspora account online at any time and from any location using the National Bank of Ethiopia's website or app, or via Siinqee Bank's website.
#Siinqee_Bank #Baankii_Siinqee #ሲንቄ_ባንክ #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan
#EMPOWERED_TOGETHER
**
የባንካችን ዲያስፖራ አካውንት አገልግሎት ግዜና ቦታ ሳይገድብዎ በኦንላይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለዚሁ አገልግሎት ባመቻቸው ድህረ-ገጽ ወይም መተግበሪያ ወይም በሲንቄ ባንክ ድህረ-ገጽ በኩል በመክፈት ፈጣን እና ምቹ አገልግሎት ያግኙ፡፡
Open our bank's efficient and accessible Diaspora account online at any time and from any location using the National Bank of Ethiopia's website or app, or via Siinqee Bank's website.
#Siinqee_Bank #Baankii_Siinqee #ሲንቄ_ባንክ #Siinqee_Digital #Siinqee_Ihsan
#EMPOWERED_TOGETHER
ለሕይወታችን እጅግ አስፈላጊ የሆኑት ንቦች የእኛን እንክብካቤ የሚሹበት ወቅት ላይ እንገኛለን
************************
በዓለም ላይ 90 በመቶ የሚሆኑት አበባማ እጽዋት እና ሰብሎች ምርት ወይም ዘር የሚሰጡት በእንስሳት ወይም በተፈጥሯዊ መንገድ በመዳቀል ነው።
ከዚህ ውስጥ ደግሞ ለምግብነትም ለምድሃኒትነትም የሚጠቅመውን ማር የሚያመርቱት ንቦች ከፍተኛው ድርሻ እንደሚይዙ ነው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት መረጃ የሚያመላክተው።
ንቦች ከአበባ ላይ የሚፈልጉትን ኔክታር ለመቅሰም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሰብሎችን ወይም የእጽዋትን የአበባ ብናኝ ከወንዴ ወደሴቴ በመውሰድ ምርት እንዲገኝ የሚጫወቱት ሚና ትኩረት የተሰጠው አይመስልም።
በዓለም ላይ 75 በመቶ የሚሆኑት የሰው ልጆች ለምግብነት የሚጠቀሟቸው ሰብሎች ምርት እንዲሰጡ የንቦች አስተዋጽኦ ቀዳሚ ሆኖ ይገኛል።
ይሁን እንጂ አሁን ላይ የሰው ልጅ የአካባቢ ሥነ-ምሕዳርን በመበከል በተለይም በኬሚካሎች በማበላሸት ንቦች አደጋ ላይ እንዲወድቁ እያደረገ መሆኑን ነው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት ያስታወቀው።
ንቦች በተለያዩ መንገዶች ዝርያቸው እየጠፋ ቢሆንም፤ በሰው ልጆች ምክያት የመጥፋት ዕድላቸው ከ100 እስከ 1000 ጊዜ የተፋጠነ መሆኑንም ነው ድርጅቱ ያመላከተው።
እጅግ ተወዳጅ የሆነውን እና ለመድሃኒትነት ጭምር የሚያገለግለውን ማር የሚያዘጋጁትን ንቦችን መንከባከብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የዓለም የምግብ አቅርቦትን ለማሳደግም አጋዥ ነው።
እናም ዓለም ከሰው ሰራሽ አበባ ተላቆ ተፈጥሯዊ አበቦችን እና እጽዋትን በመትከል ንቦችን መንከባከብ እና ሥነ-ምሕዳርን መጠበቅ እንደሚገባው ድርጅቱ አሳስቧል።
በቢታኒያ ሲሳይ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
************************
በዓለም ላይ 90 በመቶ የሚሆኑት አበባማ እጽዋት እና ሰብሎች ምርት ወይም ዘር የሚሰጡት በእንስሳት ወይም በተፈጥሯዊ መንገድ በመዳቀል ነው።
ከዚህ ውስጥ ደግሞ ለምግብነትም ለምድሃኒትነትም የሚጠቅመውን ማር የሚያመርቱት ንቦች ከፍተኛው ድርሻ እንደሚይዙ ነው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት መረጃ የሚያመላክተው።
ንቦች ከአበባ ላይ የሚፈልጉትን ኔክታር ለመቅሰም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሰብሎችን ወይም የእጽዋትን የአበባ ብናኝ ከወንዴ ወደሴቴ በመውሰድ ምርት እንዲገኝ የሚጫወቱት ሚና ትኩረት የተሰጠው አይመስልም።
በዓለም ላይ 75 በመቶ የሚሆኑት የሰው ልጆች ለምግብነት የሚጠቀሟቸው ሰብሎች ምርት እንዲሰጡ የንቦች አስተዋጽኦ ቀዳሚ ሆኖ ይገኛል።
ይሁን እንጂ አሁን ላይ የሰው ልጅ የአካባቢ ሥነ-ምሕዳርን በመበከል በተለይም በኬሚካሎች በማበላሸት ንቦች አደጋ ላይ እንዲወድቁ እያደረገ መሆኑን ነው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት ያስታወቀው።
ንቦች በተለያዩ መንገዶች ዝርያቸው እየጠፋ ቢሆንም፤ በሰው ልጆች ምክያት የመጥፋት ዕድላቸው ከ100 እስከ 1000 ጊዜ የተፋጠነ መሆኑንም ነው ድርጅቱ ያመላከተው።
እጅግ ተወዳጅ የሆነውን እና ለመድሃኒትነት ጭምር የሚያገለግለውን ማር የሚያዘጋጁትን ንቦችን መንከባከብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና የዓለም የምግብ አቅርቦትን ለማሳደግም አጋዥ ነው።
እናም ዓለም ከሰው ሰራሽ አበባ ተላቆ ተፈጥሯዊ አበቦችን እና እጽዋትን በመትከል ንቦችን መንከባከብ እና ሥነ-ምሕዳርን መጠበቅ እንደሚገባው ድርጅቱ አሳስቧል።
በቢታኒያ ሲሳይ
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
"የፕሪቶሪያ ስምምነት ሶስት ፈታኝ ጉዳዮችን አልፎ ነው የተፈረመው"፦ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን
***
የፕሪቶሪያ የሰላም ንግግር ዋና ተደራዳሪ የነበሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ወቅት አንዱ ችግር የነበረው ዲሲፕሊን እንደነበር አንስተዋል።
በሕወሓት በኩል የተለያየ ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ስለነበሩ የምንነጋገርበትን እያንዳንዱን ነገር ይዘው ለሚዲያ ያቀርቡና በሌላ ይተረጎማል፤ ይህ በመጀመሪያ ችግር ፈጥሯል ብለዋል።
በእኛም በኩል ነገሮችን ከመንደርና ሰፈር ጋር ሰፍቶ በራሱ መንገድ የማየት ችግር ነበር፤ በኋላ ልዩነቶችን በማጥበብ ተስማምተን መቀጠል ችለናል ብለዋል።
በሁለተኛ ደረጃ ዕውነታውን እና የጠፋውን ነገር ተቀብሎ መሄድ ላይ ችግር እንደነበር አስታውሰው፤ እኛ ከመንግሥት ውጪ መሳሪያ መያዝ ስለማይቻል በ24 ሰዓት ታጣቂዎች ያስረክቡ የሚል ሃሳብ ነበረን ሲሉ ተናግረዋል።
በአንፃሩ በእነ ጌታቸው በኩል ደግሞ አሁንም መዋጋት እንቸላለን የሚል ሃሳብ ነበር ብለዋል።
ሶስተኛው ችግር የአከራካሪ ቦታዎች ጉዳይ ነበር ያሉት አምባሳደር ሬድዋን፤ በዚህ ጉዳይ ላይ በመጀመሪያው ሂደት ከስምምነት ተደርሶ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ቆይቶ ጉዳዩ እንደ አዲስ ተነሳና ስምምነታችንን ሊፈታብን ነበር፤ ግን በኋላ ሊፈጠር የሚችለውን ውድመት በማሰብ አቀራራቢ ነገሮች ላይ ስምምነት ማድረግ ችለናል ሲሉ ተናግረዋል።
በጌትነት ተስፋማሪያም
ሙሉ ዝግጅቱን እዚህ ያገኙታል
#EBC #EBCDdotstream #Ambassador_Redwan_Hussien #PretoriaAgreement
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
***
የፕሪቶሪያ የሰላም ንግግር ዋና ተደራዳሪ የነበሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ወቅት አንዱ ችግር የነበረው ዲሲፕሊን እንደነበር አንስተዋል።
በሕወሓት በኩል የተለያየ ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ስለነበሩ የምንነጋገርበትን እያንዳንዱን ነገር ይዘው ለሚዲያ ያቀርቡና በሌላ ይተረጎማል፤ ይህ በመጀመሪያ ችግር ፈጥሯል ብለዋል።
በእኛም በኩል ነገሮችን ከመንደርና ሰፈር ጋር ሰፍቶ በራሱ መንገድ የማየት ችግር ነበር፤ በኋላ ልዩነቶችን በማጥበብ ተስማምተን መቀጠል ችለናል ብለዋል።
በሁለተኛ ደረጃ ዕውነታውን እና የጠፋውን ነገር ተቀብሎ መሄድ ላይ ችግር እንደነበር አስታውሰው፤ እኛ ከመንግሥት ውጪ መሳሪያ መያዝ ስለማይቻል በ24 ሰዓት ታጣቂዎች ያስረክቡ የሚል ሃሳብ ነበረን ሲሉ ተናግረዋል።
በአንፃሩ በእነ ጌታቸው በኩል ደግሞ አሁንም መዋጋት እንቸላለን የሚል ሃሳብ ነበር ብለዋል።
ሶስተኛው ችግር የአከራካሪ ቦታዎች ጉዳይ ነበር ያሉት አምባሳደር ሬድዋን፤ በዚህ ጉዳይ ላይ በመጀመሪያው ሂደት ከስምምነት ተደርሶ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ቆይቶ ጉዳዩ እንደ አዲስ ተነሳና ስምምነታችንን ሊፈታብን ነበር፤ ግን በኋላ ሊፈጠር የሚችለውን ውድመት በማሰብ አቀራራቢ ነገሮች ላይ ስምምነት ማድረግ ችለናል ሲሉ ተናግረዋል።
በጌትነት ተስፋማሪያም
ሙሉ ዝግጅቱን እዚህ ያገኙታል
#EBC #EBCDdotstream #Ambassador_Redwan_Hussien #PretoriaAgreement
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
ድርድሩ እንዳይሳካ የሚጥሩ አመራሮች በውስጣችን ነበሩ - አቶ ጌታቸው ረዳ
****************
በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ግጭት በድርድር ለመፍታት በሚደረገው ሂደት አንዳንድ አመራሮች የሰላም ድርድሩ እንዳይሳካ ሲጥሩ እንደነበር የፕሪቶሪያ የሰላም ንግግር ዋና ተደራዳሪ የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በፊት በሲሼልስ እና በጂቡቲ የሰላም ስምምነት ለመፈጸም ተቃርበን ነበር፤ ነገር ግን በእኛ መካከል የነበሩ አንዳንድ አመራሮች በድርድር ሂደቱ ሌላ አካል እንዲገባ በመፈለጋቸው ስምምነቶቹ ፈርሰዋል ብለዋል።
በሰላም እና በድርድር የሚያምን ቡድንም በውስጣችን ነበር ያሉት አቶ ጌታቸው፤ አንዳንድ አካላት ግን በድርድሩ 3ኛ ወገን እንዲገባ ይፈልጉ ነበር ሲሉ አብራርተዋል።
እነዚህ አካላት አንዱን አካል ጥፋተኛ ሌላውን ደግሞ ሀቀኛ እያሉ ይበልጡን እንዳንስማማ የሚያደርጉን ነበሩ ሲሉ ገልጸዋል።
እንዲያም ሆኖ ማንም ጣልቃ ሳይገባብን ራሳችን አስቀድመን መወያየታችን ፕሪቶሪያ ላይ ልዩነታችንን ለመፍታት እና ወደ ስምምነት ለመምጣት አግዞናል ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
ሙሉ ዝግጅቱን እዚህ ያገኙታል
#EBC #EBCDdotstream #Getachew_Reda #PretoriaAgreement
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ
****************
በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን ግጭት በድርድር ለመፍታት በሚደረገው ሂደት አንዳንድ አመራሮች የሰላም ድርድሩ እንዳይሳካ ሲጥሩ እንደነበር የፕሪቶሪያ የሰላም ንግግር ዋና ተደራዳሪ የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በፊት በሲሼልስ እና በጂቡቲ የሰላም ስምምነት ለመፈጸም ተቃርበን ነበር፤ ነገር ግን በእኛ መካከል የነበሩ አንዳንድ አመራሮች በድርድር ሂደቱ ሌላ አካል እንዲገባ በመፈለጋቸው ስምምነቶቹ ፈርሰዋል ብለዋል።
በሰላም እና በድርድር የሚያምን ቡድንም በውስጣችን ነበር ያሉት አቶ ጌታቸው፤ አንዳንድ አካላት ግን በድርድሩ 3ኛ ወገን እንዲገባ ይፈልጉ ነበር ሲሉ አብራርተዋል።
እነዚህ አካላት አንዱን አካል ጥፋተኛ ሌላውን ደግሞ ሀቀኛ እያሉ ይበልጡን እንዳንስማማ የሚያደርጉን ነበሩ ሲሉ ገልጸዋል።
እንዲያም ሆኖ ማንም ጣልቃ ሳይገባብን ራሳችን አስቀድመን መወያየታችን ፕሪቶሪያ ላይ ልዩነታችንን ለመፍታት እና ወደ ስምምነት ለመምጣት አግዞናል ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
ሙሉ ዝግጅቱን እዚህ ያገኙታል
#EBC #EBCDdotstream #Getachew_Reda #PretoriaAgreement
ኢቢሲ የፌስቡክ ገፅ
ኢቢሲ ድረ ገፅ
ኢቢሲ ቴሌግራምን ይቀላቀሉ