EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
139K subscribers
33.3K photos
376 videos
79 files
12.8K links
EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation) @etvafaanoromoo1
@ETVkidschannel
@EBCWORLD1
@etventertainment1
Download Telegram
ጋብርኤል ማጋሌሽ ውሉን አራዘመ
***************

ብራዚላዊው ተከላካይ ጋብርኤል ማጋሌሽ ከአርሰናል ጋር ያለውን ውል አራዝሟል።

የ27 ዓመቱ ተጫዋች በሰሜን ለንደን እስከ 2029 የሚያቆየውን ውል ማራዘሙን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

በ2020 ከፈረንሳይዩ ሊል መድፈኞቹን የተቀላቀለው ብራዚላዊ በአርሰናል ቤት ለመቆየት በመወሰኔ ደስተኛ ነኝ ብሏል።

የአርቴታ የመጀመርያው ፈራሚ የነበረው ተከላካይ የሳዑዲ ዓረቢያ ክለቦችን ጨምሮ በትልልቅ የአውሮፓ ክለቦች ቢፈለግም መቆየትን ምርጫው አድርጓል።

ማጋሌሽ በአርሰናል መለያ ባደረጋቸው 210 ጨዋተዎች 20 ግቦችን ሲያስቆጥር ከዊሊያም ሳሊባ ጋር የፈጠሩት ጥምረት አርሰናል አስፈሪውን ተከላካይ እንዲገነባም አስችሎታል።

በአንተነህ ሲሳይ
የአብሮነት በዓል የሆነው ዓረፋ -በጉራጌ
*************

በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱ የሆነው የዒድ አል አድሃ (ዓረፋ) በዓል በጉራጌ ሕዝብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል።

በጉራጌ ሕዝብ ዘንድ ቀደም ብሎ የሚጀምረው የዓረፋ በዓል ዝግጅት ቤት ውስጥ እንዳለው የቤተሰብ ብዛት ከአንድ ወር እስከ ሦስት ወር ሊወስድ ይችላል ይችላል።

የጉራጌ እናቶች ለበዓሉ የሚሆን ቆጮ ቀድመው በልዩ ሁኔታ ያዘጋጃሉ፤ ቅቤ እና ሚጥሚጣ በልዩ ቅመማ ቅመሞች አጣፍጠው በማዘጋጀት የበዓሉን መምጣት በጉጉት ይጠባበቃሉ።

ወጣት ሴቶች ደግሞ ለዓረፋ በዓል ቤቶችን በማስዋብ ሥራ ይጠመዳሉ፤ የመመገቢያ ዕቃዎችን እና የቤት ውስጥ ጌጣጌጦችንም በማፅዳት ቤታቸውን ያደምቃሉ።

የጉራጌ አባቶች እና ወጣት ወንዶች በበኩላቸው ለበዓሉ የሚያስፈልገውን የማገዶ እንጨት ፈልጎ በማምጣት ፈልጠው ያዘጋጃሉ።

ለበዓሉ የሚሆን የእርድ ከብት የማዘጋጀት ኃላፊነቱም የእነርሱ ነው።

የበዓሉ መዳረሻ ሰሞን የጉራጌ መንደሮች በገበያተኞቸ እና በዓሉን ለማክበር ከተለያዩ ቦታዎች በሚሰበሰቡ የጉራጌ ተወላጆች ይደምቃሉ።

በሃይማኖታዊ ትርጓሜው የመሥዋዕት በዓል በሆነው በዚህ የዓረፋ በዓል፣ በብዛት እርድ የሚከናወን ሲሆን የቻለ ከቤተሰቡ ጋር ያልቻለ ደግሞ በማኅበር በመሆን ቅርጫ ይገባል።

ያለው ለሌለው ማካፈል ሃይማኖቱ የሚያዝዘው ተግባር ከመሆኑም ባሻገር በጉራጌ ማኅበረሰብ ዘንድ ይህ በእጅጉ የተለመደ ባህል ነው።

የእርድ ዕለት ሁሉም የእምነቱ ተከታዮች በአካባቢው ያሉትን አቅመ ደካሞች እና የተቸገሩትን በመጎብኘት የተለያዩ ለበዓሉ ማክበሪያ የሚሆኑ ነገሮችን ይለግሳሉ።

በዚህም ወንዶቹ ሥጋ፤ ሴቶቹ ደግሞ ቅቤ፣ ወተት እና ቡና ለተቸገሩት የማካፈል ልማድ አላቸው።

በጉራጌ ተወላጆች ዘንድ ዓረፋ በዓል ብቻ አይደለም፤ በሥራ፣ በትምህርት እንዲሁም በተለያየ ምክንያት ከቤተሰብ የራቁ ልጆች ወደ ወላጆቻቸው የሚመለሱበት ቀን ነው፡፡

ቤተሰብ በጋራ የሚሰባሰብበት የአብሮነት ቀን በመሆኑም ዓረፋ በልዩ ጉጉት የሚጠበቅ በዓል ነው።

ሌላኛው የዓረፋ ልዩ ገፅታ ዕርቅ የሚወርድበት ቀን መሆኑ ነው። ዓመቱን ሙሉ የተቀያየሙ ሰዎች በዓረፋ በዓል ጠባቸውን ሽረው ሰላም እንዲያወርዱ ይደረጋል።

የበዓሉ ቀን እናቶች የስጋ እና የጎመን ክትፎ እንዲሁም ቡና በቅቤ በማቅረብ የበዓሉን ታዳሚዎች ይጋብዛሉ።

የሃይማኖት አባቶችም ለበዓሉ ያደረሳቸውን ፈጣሪያቸውን አመስግነው ለቀጣይ ዓመትም በሰላም እንዲያደርሳቸውም ዱአ ያደርጋሉ፤ ቤተሰቡንም ይመርቃሉ።

አዝመራው ፍሬ እንዲያፈራ፣ ሀገር ሰላም እንድትሆን ይመርቃሉ፤ ልጆች ላበረከቱት ለእያንዳንዱ ስጦታ ይመሰገናሉ፤ ለዓረፋ በዓል ወደ ቤተሰቡ ያልመጣ ጓደኛ ካላቸውም፣ ለቀጣይ ዓመት ይዘው እንዲመጡ ጭምር ኃላፊነት ይሰጣቸዋል።

ለዚህም ነው ዓረፋ ከበዓልነቱም ባሻገር የቤተሰብ እና የወዳጅ ዘመድ መሰባሰቢያ ነው የሚባለው።

በሀብተሚካኤል ክፍሉ

#EBC #ebcdotstream #Eid #eiduladha #eidmubarak
ሀጅ ያደረጉ ሙስሊሞች ሁሉ ዱዓቸው ተቀባይነት እንዲያገኝ እመኛለው - ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን
*********************

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ በመልእክታቸው በዓሉ ለሀገራቸው፣ ለህዝባቸው እና ለመላው የሰው ዘር ሁሉ መልካም እንዲሆን ተመኝተዋል።

ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን የአረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግም ለመላው የቱርክ ዜጎች እንዲሁም ለሁሉም የቱርክ ወዳጆች እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል።

በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በሐጅ ወቅት የቱርክ ተጓዦችን ጸሎት ሲመሩ ከነበሩት የቱርክ ሀይማኖታዊ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሃላፊ (ዲያኔት) ሊ ኤርባስ ጋር በስልክ ተነጋግረዋል።

በዚህም በሳዑዲ አረቢያ መካ ከተማ ሀጅ ለሚያደርጉ ሀጃጆች መልካም ምኞታቸውን ገልጸው፤ ሀጅ ያደረጉ ሙስሊሞች ሁሉ ዱአቸው ተቀባይነት እንዲያገኝ እመኛለው ብለዋል።

በሴራን ታደሰ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢቲቪ ጋር በነበራቸው ልዩ ቆይታ ስለመንግስት ሰራተኞች ከተናገሩት
የቅዳሜ መልክ

ቅዳሜ መልኩ ብዙ ነው፡፡ ቅዳሜ የቤተሰብ ቀን፤ የገበያ ቀን፤ የመዝናኛ ቀን፤ የጉብኝት ቀን ፤ የጥበብ ቀን፤ የስፖርት ቀን ነው፡፡

የቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ነገ ይጀምራል፡፡

ኢቢሲ ይህን የዘርፈ ብዙ መገለጫ ቀን የሆነውን ቅዳሜን “የቅዳሜ መልክ “ ብሎ አዲስ የዜና ሾው ይዞ ቀርቧል፡፡

በቅዳሜ መልክ ለቤተሰብ የሚመጥኑ ዝግጅቶች ፤ አስገራሚና አስደናቂ የገበያ ገጠመኞች ፤ አስደናቂ እና አነጋጋሪ የሆኑ ጥበባዊ ስራዎች ፤ ሊታዩ ሊጎበኙ የሚገባቸው ስፍራዎች የሚዳሰሱበት ፤ ሰፊ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በርካታ የሀገር ውስጥና አለምአቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮች ከታዋቂ ባለሙያዎችና ተንታኞች ጋር መረጃ እየሰጠ ፤ እያዝናና እውቀትን እያስጨበጠ ወደ ርስዎ ለማድረስ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡

ግንቦት 30 / 2017 የሚጀምረው የቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ዘወትር ቅዳሜ ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 5 ሰዓት ወደ ተመልካቾች ይቀርባል፡፡

በቅዳሜ መልክ የዜና ሾው ተመልካቾች እየተሳተፉ ይሸለማሉ፤ ባህላዊ ክዋኔዎች፤ ወጎች፣ ትውፊቶች፤ የተፈጥሮ ገጽታዎች ይጎበኛሉ፤ አዝናኝና አስተማሪ የጥበብ ስራዎች ይቀርባሉ፤ አሁናዊ ትኩስና አነጋጋሪ ስፖርታዊ ክስቶች ከታዋቂ የስፖርት ተንታኞች ጋር ይቀርባል ይተነተንማል፡፡

ሁሌም ለኢትዮጵያ ልዕልና የሚተጋው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን “ወደ ይዘት” በሚል እያካሄደ ያለውን የይዘትና የአቀራረብ ሪፎርም በቅርቡም ሌሎች አዳዲስ የዜና ሾዎችና ወቅታዊ ፕሮግራሞች፤ የመዝናኛና የስፖርት ጉዳዮችን በተለያዩ ሚዲየሞቹ በአዳዲስ ይዘትና አቀራረብ ወደ ተመልካቾች ለማድረስ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ከወዲሁ መግለጽ እንወዳለን፡፡

የቅዳሜ መልክ
ነገ ቅዳሜ ግንቦት 30 ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 5 ሰዓት በኢቲቪ ዜና ይጠብቁን!!
ኢቢሲ
ለኢትዮጵያ ልዕልና
#ebcdotstream #EBC #etvzena #ለኢትዮጵያልዕልና
አንጌ ፖስቴኮግሉ ተሰናበቱ
*********************

ቶተንሀም ሆትስፐርስ አሰልጣኙ ፖስቴኮግሉን ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል።

አስቸጋሪ የውድድር ዓመት ያሳለፉት አውስትራሊያዊው አሰልጣኝ በይፋ ከሰሜን ለንደኑ ክለብ ተሸኝተዋል።

በሊጉ 17ኛ ደረጃን ይዞ የጨረሰው ቶተንሀም ሆትስፐር በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ ማንችስተር ዩናይትድን አሸንፎ ዋንጫውን ቢያነሳም አሰልጣኙ ከመሰናበት አልዳኑም።

የቀድሞው የሴልቲክ አሰልጣኝ ከሁለት ዓመት ቆይታ በኋላ ሲሰናበቱ በምትካቸው ቶማስ ፍራንክ ሊሾሙ እንደሚችሉ ቲኤንቲ ስፖርት ዘግቧል።

በአንተነህ ሲሳይ
#ebcdotstream #ebcsport #angepostecoglou #sacked #Tottenham
Live stream finished (2 minutes)
Live stream finished (2 hours)
“ተረጂነት እጅግ አሳፋሪው ነገር ነው፤ ኢትዮጵያን የሚያክል ሀገር ለራሷ አምርታ እራሷን መመገብ አቅቷት አንዳንዴ ከእሷም ካነሱ ሀገራት መለመኗ በጣም አሳፋሪ ነገር ነው። ከዚህ አሳፋሪ ነገር ይሄ ትውልድ ጨክኖ መገላገል አለበት” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ebcdotstream #EBC #PM #AbiyAhmed