EBC (Ethiopian Broadcasting Corporation)
136K subscribers
20.5K photos
169 videos
79 files
10.6K links
Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC)
Download Telegram
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያደረጓቸው ንግግሮች እና ያስተላለፏቸው መልዕክቶችን የያዘው 'ከመስከረም እስከ መስከረም' መጽሕፍ ዛሬ ይፋ ይሆናል
*****************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመስከረም 24 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ያደረጓቸው ንግግሮች እና ያስተላለፏቸው መልዕክቶችን የያዘው 'ከመስከረም እስከ መስከረም' መጽሕፍ ዛሬ ይፋ እንደሚሆን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
የሼካ ፋጢማ ቢንት ሙባረክ የዐይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤት
ኢትዮጵያና ሞሮኮ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
*******************

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሁለትዮሽ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ፉዓድ ያዙሁር የተመራ የልዑካን ቡድን ተቀብለው አነጋግረዋል።

ሁለቱ ወገኖች ኢትዮጵያና ሞሮኮ ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት አጠናክሮ ማስቀጠል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።

በተለይም ሁለቱ አገራት ቀደም ሲል አብረው ለመስራት ስምምነት የደረሱባቸውን የንግድ፣ የኢንቬስትመንት፣ የፋይናንስ፣ የአየር አገልግሎት እና የትምህርት ዘርፍ የትብብር ስምምነቶች መልሶ በመቃኘት ለማጠናከር ተስማምተዋል።

አገራቱ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባለፈ በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችም በትብብር መስራት በሚችሉባቸው መስኮች ላይ መክረዋል።

ውይይቱን ተከትሎም በሞሮኮ እና በኢትዮጵያ መካከል የጋራ የሚኒስትሮች ኮሚሽን ስብሰባ በቅርቡ ለማካሄድ ከስምምነት መደረሱን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በሕግ እና በሕግ የበላይነት መከበር የሚያምን ትውልድ ሊኖረን ይገባል - የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ
***************

የአማራ ክልል ከነበረው የፀጥታ ችግር በመሻሻል አንፃራዊ ሰላም ላይ እንደሚገኝ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ደሳለኝ ጣሰው ገለጹ።

ክልሉ በቀደሙት ጊዜያት ባልተጠበቀ ያለመረጋጋት ውስጥ ማለፉን አስታውሰው፤ ይህን ለመቅረፍ መንግሥታዊ ተልዕኮውን የሚወጣ አደረጃጀት የማዋቀር ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።

ለተገኘው ሰላም የመከላከያ ሠራዊት ሚና ላቅ ያለ ነው ብለዋል ኃላፊው።

የአመለካከት እና የአስተሳሰብ አንድነት በመፍጠር የተገኘውን ሰላም ለማስቀጠል የክልሉ የፀጥታ መዋቅር የአቅም ግንባታ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02Hy1oNPBhvRbPtoj9oSJqzKQDUux3rDEhzp4wXgX3Ft7fHowSRKNREHuJG5QdC1wul
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ለኢራን ሪፐብሊክ መንግሥትና ህዝብ የኀዘን መልዕክት አስተላለፈ
**********

የኢራን ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ራኢሲ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሁሴን አሚር አብዱላሂያንን ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በሄሊኮፕተር አደጋ ሕይወታቸው ማለፉን ተከትሎ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት ለኢራን ሪፐብሊክ መንግሥትና ህዝብ የኀዘን መልዕክት አስተላልፏል።

ከፍተኛ ባለስልጣናቱን ያሳፈረች ሄሊኮፕተር ላይ ትናንት አመሻሹን አደጋ መድረሱ ይታወቃል።

አደጋውን ተከትሎም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ የኀዘን መግለጫቸውን ለኢራን ሪፐብሊክ መንግሥትና ህዝብ አስተላልፈዋል።

በኀዘን በመግለጫው ሕይወታቸው ላለፈው ባለሥልጣናት ቤተሰቦችና ወዳጆች መፅናናትን መመኘታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር በተለያዩ ወታደራዊ ጉዳዮች ያላትን ትብብር ማጠናከር እንደምትፈልግ ገለጸች
***********************

በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የተመራው የኢትዮጵያ መከላከያ የልዑካን ቡድን በጣሊያን ወገን በተደረገለት ግብዣ መሠረት ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ ይገኛል።

የልዑካን ቡድኑ ጣሊያን ሲገባ በሀገሪቱ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም አድሚራል ጁሴፔ ካቮ ድራጎን እና በሌሎች ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣናት ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዛሬው ዕለት ከጣሊያኑ አቻቸው አድሚራል ጁሴፔ ካቮ ድራጎን ጋር በወታደራዊ ትብብሮች ዙሪያ ውጤታማ ውይይት አድርገዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በውይይቱ ወቅት በሁለቱ ሀገራት መካከል እያደገ የመጣውን ግንኙነት አውስተው፣ ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጣሊያን ያደረጉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነት መጠናከር አመላካች መሆኑን አንስተዋል።

አክለውም፥ አድሚራል ጁሴፔ ካቮ ድራጎን በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት በዘርፉ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳበረከተም ገልጸዋል።

አድሚራል ጁሴፔ ካቮ ድራጎን በበኩላቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል በተለያዩ ወታደራዊ ጉዳዮች ያለውን ትብብር ይበልጥ ለማጠናከር ጣሊያን ያላትን ፍላጎት ገልጸዋል።

አያይዘውም፥ በዘርፉ በተለያዩ ደረጃዎች ያለውን ግንኙነት ማስቀጠል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው መናገራቸውን በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግሮችና መልዕክቶችን የያዘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
***********************

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ንግግሮችና መልዕክቶችን የያዘና "ከመስከረም እስከ መስከረም" የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ።

በመጽሐፉ ላይ የዳሰሳ ውይይት በወዳጅነት ፓርክ ተካሂዷል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሪታሪያት የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከመስከረም 24 ቀን 2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 24 ቀን 2016 ዓ.ም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎችና ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች ላይ ያደረጓቸው 91 ንግግሮችና መልዕክቶችን ያያዘ ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሪታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም በውይይት መድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር፥ መጽሐፉ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግሮችና መልዕክቶች የያዘ 6ኛው መድብል መሆኑን ገልጸዋል።

የመሪ ታሪክ የሀገር ታሪክ አካል መሆኑን ጠቅሰው፤ ከዚህ አኳያ መጽሐፉ ለታሪክ አጥኚዎች፣ ለፖሊሲ አውጭዎችና ለፖለቲካ ተመራማሪዎች ግብዓት እንደሚሆን ተናግረዋል።

በመድረኩ ተማሪዎች ከመጽሐፉ የተመረጡ ገጾችን እንደ ውይይት መነሻ ሃሳብ በንባብ አቅርበዋል።

"ከመስከረም እስከ መስከረም" መጽሐፍ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ በእንግሊዝኛ እና በአረቢኛ ቋንቋዎች ያስተላላፏቸውን ንግግሮችና መልዕክቶች ይዟል።

በሮዛ መኮንን
1 ሺህ 175 ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
****************

በዛሬው ዕለት በ3 ዙር በረራ በተከናወነ በሳውዲ አረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ስራ፣ 1 ሺህ 175 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።

ወደ ሀገር የተመለሱት 1 ሺህ 175 ዜጎች ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ፤ ከተመላሾች መካከል 18 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊ ህጻናት ይገኙበታል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

ከሚያዚያ 04 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ በሚገኘው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ፣ እስካሁን ከ27 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን መመለስ መቻሉ ተገልጿል።
ሽንታችን ስለጤናችን ምን ይነግረናል?
*************

ሽንት በምንመገበው ምግብ፣ በምንወሰደው መድኃኒት እንዲሁም በምንጠጣው የውኃ መጠን ምክንያት ቀለሙ፣ ጠረኑ እንዲሁም ዓይነቱ ይቀያየራል።

ሽንት ሰውነታችን በፈሳሽ መልክ ቆሻሻን የሚያስወግድበት አንዱ መንገድ ሲሆን በዋናነት ውኃ፣ ጨው፣ ኤሌክትሮላይቶች እንደ ፖታሺየም እና ፎስፈረስ፣ ዩሪያ እና ዩሪክ አሲድ የሚባሉ ኬሚካሎች በውስጡ ይዞ ይገኛል።

እነዚህም ኩላሊት መርዛማ ንጥረ ነገሮችን እና ሌሎች መጥፎ ነገሮችን ከደም ውስጥ ሲያጣራ የሚከሰቱ ሲሆኑ፤ መድኃኒት፣ የተለያዩ ዓይነት ምግቦች እና ሕመሞች የሚወገደው የሽንት ዓይነት ላይ ለውጥ እንዲኖረው ያደርጋሉ።

ጤናችን ያለበትን ሁኔታ የሚነግሩን የቀለም ዓይነቶች እንዳሉ ስንቶቻችን እናውቃለን?

ጤናማ የሽንት ቀለም ምን ዓይነት ነው?

ሽንት ፈዛዛ ቢጫ ወይንም ወርቃማ ቀለም ሲኖረው ሰውነት በቂ ውኃ አግኝቷል፤ ጤናማ ነው እንላለን።

ሽንት ምንም ዓይነት ቀለም ከሌለው (ውኃ ቀለም) ከሆነ ደግሞ ሰውነታችን በብዛት ውኃ እንዳገኘ እና እንዳበዛን ያመላክታል።

ከልክ በላይ ውኃ ማብዛት በሰውነታችን ወስጥ የኤሌክትሮላይት መዛባት ያስከትላል፤ በመሆኑም የምንወስደውን የውኃ መጠን በመቀነስ በቀን ውስጥ ከ6 እስከ 8 ብርጭቆ ውኃ እንድንጠጣ ይመከራል።

ቀላ ያለ ሮዝ ቀለም ለኩላሊት እና ለተለያዩ በሽታዎች መጋለጥን ሊያመላክት ይችላል።https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02u2BPuvN94L3mR5QgzsH2onD5wwzJvsGMEBQbxBHJMgw26QLHHPo6JRJvhqJuZrfsl
የግንቦት 13 ቀን 2016 የውጭ ምንዛሬ ዋጋ
ለመጀመሪያው ዙር የሐጅ ተጓዦች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሽኝት ተደረገ
***************

ለዘንድሮው ለ1 ሺህ 445ኛው የሐጅ ሥነ-ሥርዓት የመጀመሪያ ዙር ተጓዦች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሽኝት ተደረገ።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመራርና ሰራተኞች በተገኙበት ሽኝቱ መደረጉ ታውቋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ጸሃፊ ሸኽ ሃሚድ ሙሳ፤ በሂደቱ የምዝገባ፣ የቪዛ፣ የምክርና ተያያዥ አገልግሎቶች በተቀላጠፈ መልኩ መሰጠታቸውን ገልጸዋል።

ለሐጅ ሥነ-ሥርዓቱ ከጉዞ እስከ መመለሻ ድረስ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በባለፈው ዓመት 11 ሺህ ሑጃጆች መጓዛቸውን አስታውሰው ዘንድሮ ደግሞ ከ12 ሺህ በላይ ተጓዦች ወደ ስፍራው የሚያቀኑ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት በዛሬው እለት የመጀመሪያው ዙር የሑጃጆች የሽኝት ሥነ-ሥርዓት መደረጉን ተናግረዋል።https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid0SoktYNCqtamPpThxFMcJ7TsJKct81qZNPfCzy9qPigBBU8Srns1qxUNMvhZWsVzdl
ባለፉት ጥቂት አመታት ዋናውን የዝናብ ወቅት ምርት ሳናስተጓጉል የበጋ ስንዴ ልማት ጥረታችንን ለማስፋፋት ችለናል። የዛሬው ምልከታ የስራዎችን ቀጣይነት የተመለከትንበት ነበር። ግብርና ጠንካራ ኢንቨስትመንት ይፈልጋል። በሰብል የምንሸፍነው የመሬታችን ይዞታም ቀስ በቀስ በመጨመር ላይ ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) https://www.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02waGXZW9S5uzfBsB9bVnZ2jmf2YfHTCnKRLki48aCCzmxDiKuHP1rP4vJdcYW11isl