Development Bank of Ethiopia (DBE)
23.3K subscribers
2.1K photos
76 videos
4 files
579 links
The development bank of Ethiopia (DBE) is one of the financial institutions engaged in providing short, medium and long term development credits.
Download Telegram
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማበረታታት ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ባዘጋጀው "የኛ ምርት" ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ አሳውቋል፡፡

ባንኩ በስካይ ላይት ሆቴል ከታህሳስ 3 እስከ 7 ቀን 2016 ዓ.ም የተካሄደውን ኤግዚቢሽንና ባዛር ስፖንሰር በማድርግ አምራች እና ሸማቹ እንዲገናኝ የራሱን አስተዋጽዖ አበርክቷል፡፡ ኤግዚቢሽንና ባዛሩን ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አምራቹ ያለበትን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች እና በአጠቃላይ የአምራቹን ዘርፍ የሚያበረታቱ አገራዊ አቅሞችን በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ በማድረግ በኩል ላቅ ያለ አበርክቶት እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ ተናግረዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለፁት እንደሀገር በዘርፋ በስፋት ለመሰማራት የሚያስችል ሰፊ የሰው ኃይል፣ የግብርናና የተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም ሰፊ የገበያ ዕድል ያለ በመሆኑ ይህን አስተባባሮ በመምራትና በመደገፍ መንቀሳቀስ ይገባል፡፡ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ እንደሀገር መሰረት መሆን የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ያብራሩት ዶ/ር አለባቸው ሀገራዊ አቅማችንን በማጠናከር ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡

"ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው የፖናል ውይይት ላይ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ልማድና የማሻሻያ ሃሳቦች፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንን በመገንባት ሂደት የመንግስት ሚና፣ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የፋይናንስ ተቋማት ሚና በሚሉ ርዕሶች ሰፊና ገንቢ ውይይቶች ተደርገዋል፡፡

ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ ጎን ለጎን በተካሄደው የፓናል ውይይት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ለኢንዱስትሪ ልማትና ግንባታ ያላቸው ሚናና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚኖረውን ድርሻ በላቀ ደረጃ ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችና ምቹ ሁኔታና ተግዳሮች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ፣ በአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ረጅም ልምድ ያላቸው ዶ/ር ንግስት ሐይሌ እና የኢንተርፕራይዝ ባለቤት ኢንጅነር አይሸሽም ጥላሁን የተሳተፉበት የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ ውይይቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል መርተውታል፡፡

አቶ መላኩ አለበል የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ለሀገራችን አማራጭ ሳይሆን ዋነኛ የኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ታሳቢ ያደረጉ ድጋፎችን በማቅረብ የሀገር ውስጥ አምራቾችን ማበራከት፣ ማጠናከርና የገበያ ድርሻቸውንም ማሻሻል ይገባል ብለዋል።

ሚኒስትሩ አያይዘውም በዘርፉ ተኪ ምርትን ማስፋትና ኤክስፖርትን ማበረታታት እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ በመሆኑ ተቋማት ተቀናጅተው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ የስራ እድል በመፍጠር፣ አዳዲስና የፈጠራ ሀሳቦች በማመንጨትና ኢኮኖሚያዊ አቅምን በማጠናከር በኩል ጉልህ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ያነሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ይህን ታሳቢ ያደረገ ስራ እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ባንኩ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ ኢንተርፕራይዞቹ በፋይናንስ እንዲደገፉ ከፍተኛ ገንዘብ መድቦና በዚህ ላይ የሚሰራ ሰፊ የሰው ኃይል አሰማርቶ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በተመሳሳይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች እየቀረቡ ባሉ የፋይናንስ አቅርቦቶችና በዚህ ሂደት ውስጥ በሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ሚና ዙሪያ በተደረገው የፓናል ውይይት ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንሲንግ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አስፋው አበራ እንዳሉት የፋይናንስ አቅርቦቱን ለማሻሻል ባንኩ ልዩ መስኮቶችን በመክፈትና ከልዩ ልዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየሠራ ከመሆኑም በላይ የዘርፉን ልዩ ባህርይ ታሳቢ ያደረጉ አዳዲስ አሠራሮችን በመተግበር ላይ ነው፡፡

በመጨረሻም "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል የተከፈተውና "የኛ ምርት" የተሰኘው የአምራች ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እና ሌሎች ሚኒስትሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንትና የማኔጅመንት አባላት ባዛሩን የጎበኙ ሲሆን ባዛሩ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የአምራች ኢንተርፕራይዞች ቴክኖሎጂና የምርት እድገት ለመረዳት የሚያስችልና ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ በሚገኘው ልምድ የአምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና ለማሻሻል የሚረዱ የድጋፍ ማዕቀፎች ለማዘጋጀት የጎላ ሚና እንደሚኖረው ተመላክቷል፡፡

"የኛ ምርት" ኤግዚቢሽንና ባዛር በቀጣይ በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ለማካሄድ እቅድ እንደተያዘም ተመላክቷል፡፡

የአምራች ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአገር ውስጥ አምራች ኢንተርፕራይዞች የተሻለ ምርት እንዲያመርቱ ከሚሰጠው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ በተጨማሪ ምርቶቻቸው እንዲተዋወቁ ኤግዚቢሽንና ባዛር ማዘጋጀቱን በማመስገን ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia

በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍37❤4
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለሊዝ ፋይናንስ ደንበኞች የትራክተር፣ ኮምባይን ሐርቨስተር እና የኤክስካቫተር ማሽነሪዎችን አስረክቧል፡፡ ይህን አስመልክቶ የደንበኞችን አስተያየት እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው መልዕክት የተካተተበትን ፕሮግራም መስፈንጠሪያውን በመጫን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=C8JfqegidHg

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia

በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍26❤7🤝2
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዲስትሪክትን የመስክ ምልከታ በማድረግ የስራ እንቅስቃሴውን ጎበኙ::

የቋሚ ኮሚቴው ቡድን አስተባባሪ የተከበሩ አቶ እያሱ ዛላ እንዳሉት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በክልሉ የሰራው ሥራ አድንቀው ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን እና ለስራው ውጤታማነት የተበዳሪዎች የስልጠና ቀድሞ መውሰድ ውጤቱን ከፍ አድርጎታል፡፡

አስተባባሪው አያይዘውም ባንኩ ሲሰጥ የነበረው የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተር ፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል::

ቋሚ ኮሚቴው በባንኩ ብድር ተመቻችቶላቸው ምርት የጀመሩ የተለያዩ አምራች ተቋማትን በአካል ተገኝተው ምልከታ አድርገዋል::

በሌላ በኩል ባንኩ በደንበኝነት የሚያውቃቸው ተበዳሪዎች ቋሚ ኮሚቴው ባንኩ የሰጠውን ብድር የት እንደደረሰ ለመመልከት በጠየቀበት ጊዜ ድርጅታቸውን ማስጎብኘታቸው ባለሀብቱ እና ባንኩ ያላቸውን መደጋገፍ የሚያሳይ መሆኑንም በምልከታቸው ወቅት መታዘባቸውን ገልጸዋል፡፡

በአከባቢው ከሚለማው ፕሮጀክት ቀዳሚ የሆነውን የቡና ልማት ፕሮጀክትን ቋሚ ኮሚቴው በተመለከተበት ወቅት በዘርፉ ለሚታየው የቡና ገበያ መቀዛቀዝ መንግስት መፍትሔ እንዲሰጣችው አልሚዎች ጠይቀዋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሚዛን ቅርንጫፍ ምርታማነትን ለማረጋገጥ እና ለሚፈለገው የሥራ መስክ የሚያደርገው ድጋፍ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ጠቁሞ፣ በቡና ልማቱ ዙሪያ የገበያ ትስስሩ ድጋፍ ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝቧል::

በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው አስተባባሪ አቶ እያሱ ባንኩ ከነበረበት ችግር ተላቆ በሀገር ደረጃ እያበረከተ ያለው አስተዋጽጾ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው ፣ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ማድርግ ከቻሉ በባንኩ እየተመዘገበ ያለው ለውጥ እና እድገት ከዚህም ሊልቅ የሚችል ነው ሲሉ በመስክ ተገኝተው ምልከታና ጉብኝት ለተሳተፉ የቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ለባንኩ አመራሮች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia

በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍35❤4👏1
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ባለፉት ጥቂት ዓመታት እያስመዘገባቸው ያሉ ስኬቶች ባንኩ በለውጥ ጎዳና ላይ እንዳለ የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ ባንኩ ትናንትን ተሻግሮ ዛሬ ላይ ለውጥ እያመጣ ያለ ባንክ ሲሆን የልማት አጋርነቱን በተጨባጭ ማሳየት የቻለ እና ለሀገራችን ልማት መፋጠን እየተጋ ያለ ባንክ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሌሎች ሀገራት እንደሚገኙ ውጤታማ የልማት ባንኮች በሀገራችን ኢኮኖሚያዊ እድገትና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ ግልጽ ተልዕኮ በማስቀመጥ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

ባንኩ እቅዶቹን፣ በተጨባጭ እያስመዘገባቸው ያሉ ለውጦችን፣ በባንኩ እገዛ አገር መጥቀም የቻሉ ፕሮጀክቶችን ለመከታተልና አጠቃላይ ከባንካችን የሚለቀቁ ማናቸውንም መረጃዎች ለማግኘት የማህበራዊ ትስስር ገጾቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡

ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍22❤5🤝3
የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ለአንድ አገር እድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡ በተለይ ከፍተኛ የሆነ የስራ እድል በመፍጠር፣ የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በአገር ውስጥ አንዲተኩ በማድረግ እና የቴክኖሎጂ ሽግግርን በማምጣት በኩል ላቅ ያለ ፋይዳ አላቸው፡፡
የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች አገራችን ወደ ኢንዱስትሪ የምታደርገውን መዋቅራዊ ሽግግር የሚያፋጥኑ በመሆኑ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ኢንተርፕራይዞቹ ከልማዳዊ አሰራር ተላቀው የንግድ ስራቸው ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እንዲመራ የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት ይደግፋል፡፡
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍32❤11
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የግብርና ሜካናዬዝሽንን በመደገፍ የግብርና ስራውን ማዘመን ላይ ትኩረት አድርጎ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም በግብርና ስራ ላይ የሚወጣውን ጉልበት በመቆጠብ እና ምርታማነትን በመጨመር የጎላ ድርሻ እየተወጣ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው፡፡
👍41❤9🤝1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ተጠቃሚ ካደረጋቸው የሊዝ ፋይናንስ ደንበኞች መካከል የቦንጋ ዲስትሪክት ደንበኛችን አቶ አሸናፊ ዳመታ አንዱ ናቸው፡፡ የዛሬው የስኬት በስተጀርባ አሹ የቤትና የቢሮ እቃዎች ማምረቻ ድርጅት የስራ እንቅስቃሴን ይዳስሳል፡፡
👍17❤7
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ልዩ የበዓል ዝግጅት አሰናድቶ ታህሳስ 28 በኢቲቪ ዜና ቻናል ከ8 እስከ 10 ሰዓት ይጠብቃችኋል፡፡

እየተዝናኑ በጎ መስራትን የሚመለከቱበት፣ በሰዎች ደስታ ውስጥ የሚገኝ ልዩ ደስታን የሚያጣጥሙበት፣ አገር በሰው ልብ እንደሚሰራ የሚማሩበት ልዩ የበዓል ዝግጅት አሰናድቶ ይጠብቃችኋል፡፡ እንዳያመልጣችሁ፡፡

መልካም በዓል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍36❤2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለመላው የክርስትና እምነት ተካታዮች
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
❤28👍7