የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የቴክኖሎጂ አቅሙን በማሳደግ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የታገዙ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችለውን ስራ እየሰራ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ መተግበሪያዎች ዙሪያ ስልጠና ለአመራሮች ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው የመክፈቻ ፕሮግራም ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው በላይ ባለቤትነቱ የዩኒዶ የሆነው ኮንፋር የተሰኘው መተግበሪያ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው የፕሮጀክት ብድር ጥናትና ትንተና መተግበሪያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋነኛ ስራም የፕሮጀክት ብድር አቅርቦት መሆኑን ያመላከቱት አቶ ጌታቸው በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የተደገፈ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከዮኒዶ ጋር እየተሰራ እንደሚገኝ እና ባንኩ መተግበሪያዉን መጠቀም የሚያስችለውን 100 ላይሰንስ ከዩኒዶ መግዛቱንም ገልጸዋል፡፡
መተግበሪያው ከዚህ ቀደም ብድር ለማጽደቅ የሚፈጀውን ጊዜ እንደሚያሳጥር እና ከባለሙያ ስህተት በጸዳ መልኩ ሙሉ በሙሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የሚሰራ መሆኑን የገለጹት ም/ል ፕሬዝዳንቱ በቴክኖሎጅው ለመጠቀም ለባንኩ የስራ ሀላፊዎች ከዩኒዶ በመጡ አስልጣኞች እንዲሰለጥኑ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
ባንኩ ትልቅ የቴክኖሎጅ አቅም እየፈጠረ ነው ያሉት አቶ ጌታቸው ይህም ባንኩ በ5 ዓመት የስትራቴጅክ ዕቅዱ አካቶ እየፈጸመው እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በሁለት ዙሮች ተከፍሎ የሚሰጠው ስልጠና ለ15 ቀን የሚቆይ ሲሆን ከሁሉም ዲስትሪክቶች እና ከዋናው መስሪያ ቤት ለተመረጡ የስራ ሀላፊዎች የሚሰጥ ስልጠና ነው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) ጋር በመተባበር በቴክኖሎጂ መተግበሪያዎች ዙሪያ ስልጠና ለአመራሮች ሰጥቷል፡፡
በስልጠናው የመክፈቻ ፕሮግራም ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባንኩ የኮርፖሬት አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው በላይ ባለቤትነቱ የዩኒዶ የሆነው ኮንፋር የተሰኘው መተግበሪያ በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው የፕሮጀክት ብድር ጥናትና ትንተና መተግበሪያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋነኛ ስራም የፕሮጀክት ብድር አቅርቦት መሆኑን ያመላከቱት አቶ ጌታቸው በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የተደገፈ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት ከዮኒዶ ጋር እየተሰራ እንደሚገኝ እና ባንኩ መተግበሪያዉን መጠቀም የሚያስችለውን 100 ላይሰንስ ከዩኒዶ መግዛቱንም ገልጸዋል፡፡
መተግበሪያው ከዚህ ቀደም ብድር ለማጽደቅ የሚፈጀውን ጊዜ እንደሚያሳጥር እና ከባለሙያ ስህተት በጸዳ መልኩ ሙሉ በሙሉ በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የሚሰራ መሆኑን የገለጹት ም/ል ፕሬዝዳንቱ በቴክኖሎጅው ለመጠቀም ለባንኩ የስራ ሀላፊዎች ከዩኒዶ በመጡ አስልጣኞች እንዲሰለጥኑ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
ባንኩ ትልቅ የቴክኖሎጅ አቅም እየፈጠረ ነው ያሉት አቶ ጌታቸው ይህም ባንኩ በ5 ዓመት የስትራቴጅክ ዕቅዱ አካቶ እየፈጸመው እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በሁለት ዙሮች ተከፍሎ የሚሰጠው ስልጠና ለ15 ቀን የሚቆይ ሲሆን ከሁሉም ዲስትሪክቶች እና ከዋናው መስሪያ ቤት ለተመረጡ የስራ ሀላፊዎች የሚሰጥ ስልጠና ነው፡፡
👍43❤9
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአምራች ኢንዱስትሪውን ዘርፍ ለማበረታታት ከመቼውም ጊዜ በላይ በትኩረት እንደሚሰራ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ባዘጋጀው "የኛ ምርት" ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ አሳውቋል፡፡
ባንኩ በስካይ ላይት ሆቴል ከታህሳስ 3 እስከ 7 ቀን 2016 ዓ.ም የተካሄደውን ኤግዚቢሽንና ባዛር ስፖንሰር በማድርግ አምራች እና ሸማቹ እንዲገናኝ የራሱን አስተዋጽዖ አበርክቷል፡፡ ኤግዚቢሽንና ባዛሩን ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አምራቹ ያለበትን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች እና በአጠቃላይ የአምራቹን ዘርፍ የሚያበረታቱ አገራዊ አቅሞችን በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ በማድረግ በኩል ላቅ ያለ አበርክቶት እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ ተናግረዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለፁት እንደሀገር በዘርፋ በስፋት ለመሰማራት የሚያስችል ሰፊ የሰው ኃይል፣ የግብርናና የተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም ሰፊ የገበያ ዕድል ያለ በመሆኑ ይህን አስተባባሮ በመምራትና በመደገፍ መንቀሳቀስ ይገባል፡፡ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ እንደሀገር መሰረት መሆን የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ያብራሩት ዶ/ር አለባቸው ሀገራዊ አቅማችንን በማጠናከር ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡
"ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው የፖናል ውይይት ላይ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ልማድና የማሻሻያ ሃሳቦች፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንን በመገንባት ሂደት የመንግስት ሚና፣ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የፋይናንስ ተቋማት ሚና በሚሉ ርዕሶች ሰፊና ገንቢ ውይይቶች ተደርገዋል፡፡
ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ ጎን ለጎን በተካሄደው የፓናል ውይይት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ለኢንዱስትሪ ልማትና ግንባታ ያላቸው ሚናና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚኖረውን ድርሻ በላቀ ደረጃ ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችና ምቹ ሁኔታና ተግዳሮች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ፣ በአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ረጅም ልምድ ያላቸው ዶ/ር ንግስት ሐይሌ እና የኢንተርፕራይዝ ባለቤት ኢንጅነር አይሸሽም ጥላሁን የተሳተፉበት የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ ውይይቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል መርተውታል፡፡
አቶ መላኩ አለበል የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ለሀገራችን አማራጭ ሳይሆን ዋነኛ የኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ታሳቢ ያደረጉ ድጋፎችን በማቅረብ የሀገር ውስጥ አምራቾችን ማበራከት፣ ማጠናከርና የገበያ ድርሻቸውንም ማሻሻል ይገባል ብለዋል።
ሚኒስትሩ አያይዘውም በዘርፉ ተኪ ምርትን ማስፋትና ኤክስፖርትን ማበረታታት እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ በመሆኑ ተቋማት ተቀናጅተው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ የስራ እድል በመፍጠር፣ አዳዲስና የፈጠራ ሀሳቦች በማመንጨትና ኢኮኖሚያዊ አቅምን በማጠናከር በኩል ጉልህ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ያነሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ይህን ታሳቢ ያደረገ ስራ እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ባንኩ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ ኢንተርፕራይዞቹ በፋይናንስ እንዲደገፉ ከፍተኛ ገንዘብ መድቦና በዚህ ላይ የሚሰራ ሰፊ የሰው ኃይል አሰማርቶ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በተመሳሳይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች እየቀረቡ ባሉ የፋይናንስ አቅርቦቶችና በዚህ ሂደት ውስጥ በሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ሚና ዙሪያ በተደረገው የፓናል ውይይት ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንሲንግ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አስፋው አበራ እንዳሉት የፋይናንስ አቅርቦቱን ለማሻሻል ባንኩ ልዩ መስኮቶችን በመክፈትና ከልዩ ልዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየሠራ ከመሆኑም በላይ የዘርፉን ልዩ ባህርይ ታሳቢ ያደረጉ አዳዲስ አሠራሮችን በመተግበር ላይ ነው፡፡
በመጨረሻም "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል የተከፈተውና "የኛ ምርት" የተሰኘው የአምራች ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እና ሌሎች ሚኒስትሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንትና የማኔጅመንት አባላት ባዛሩን የጎበኙ ሲሆን ባዛሩ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የአምራች ኢንተርፕራይዞች ቴክኖሎጂና የምርት እድገት ለመረዳት የሚያስችልና ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ በሚገኘው ልምድ የአምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና ለማሻሻል የሚረዱ የድጋፍ ማዕቀፎች ለማዘጋጀት የጎላ ሚና እንደሚኖረው ተመላክቷል፡፡
"የኛ ምርት" ኤግዚቢሽንና ባዛር በቀጣይ በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ለማካሄድ እቅድ እንደተያዘም ተመላክቷል፡፡
የአምራች ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአገር ውስጥ አምራች ኢንተርፕራይዞች የተሻለ ምርት እንዲያመርቱ ከሚሰጠው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ በተጨማሪ ምርቶቻቸው እንዲተዋወቁ ኤግዚቢሽንና ባዛር ማዘጋጀቱን በማመስገን ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
ባንኩ በስካይ ላይት ሆቴል ከታህሳስ 3 እስከ 7 ቀን 2016 ዓ.ም የተካሄደውን ኤግዚቢሽንና ባዛር ስፖንሰር በማድርግ አምራች እና ሸማቹ እንዲገናኝ የራሱን አስተዋጽዖ አበርክቷል፡፡ ኤግዚቢሽንና ባዛሩን ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዞች ልማት አምራቹ ያለበትን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች እና በአጠቃላይ የአምራቹን ዘርፍ የሚያበረታቱ አገራዊ አቅሞችን በተመለከተ በቂ ግንዛቤ እንዲያዝ በማድረግ በኩል ላቅ ያለ አበርክቶት እንደሚኖረው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ ተናግረዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ እንደገለፁት እንደሀገር በዘርፋ በስፋት ለመሰማራት የሚያስችል ሰፊ የሰው ኃይል፣ የግብርናና የተፈጥሮ ሀብት እንዲሁም ሰፊ የገበያ ዕድል ያለ በመሆኑ ይህን አስተባባሮ በመምራትና በመደገፍ መንቀሳቀስ ይገባል፡፡ በአነስተኛና መካከለኛ አምራች ዘርፍ እንደሀገር መሰረት መሆን የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ያብራሩት ዶ/ር አለባቸው ሀገራዊ አቅማችንን በማጠናከር ተጨማሪ ጥረቶችን ማድረግ እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡
"ኢትዮጵያ ታምርት፤ እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በተካሄደው የፖናል ውይይት ላይ የሀገር ውስጥ ምርቶችን የመጠቀም ልማድና የማሻሻያ ሃሳቦች፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንን በመገንባት ሂደት የመንግስት ሚና፣ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት የፋይናንስ ተቋማት ሚና በሚሉ ርዕሶች ሰፊና ገንቢ ውይይቶች ተደርገዋል፡፡
ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ ጎን ለጎን በተካሄደው የፓናል ውይይት የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዞች ለኢንዱስትሪ ልማትና ግንባታ ያላቸው ሚናና ዘርፉ በኢኮኖሚው ውስጥ የሚኖረውን ድርሻ በላቀ ደረጃ ለማሳደግ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችና ምቹ ሁኔታና ተግዳሮች ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ንጉሴ፣ በአምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ ረጅም ልምድ ያላቸው ዶ/ር ንግስት ሐይሌ እና የኢንተርፕራይዝ ባለቤት ኢንጅነር አይሸሽም ጥላሁን የተሳተፉበት የፓናል ውይይት የተካሄደ ሲሆን፣ ውይይቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል መርተውታል፡፡
አቶ መላኩ አለበል የአምራች ኢንተርፕራይዞች ልማት ለሀገራችን አማራጭ ሳይሆን ዋነኛ የኢኮኖሚ ግንባታ ትኩረት መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ታሳቢ ያደረጉ ድጋፎችን በማቅረብ የሀገር ውስጥ አምራቾችን ማበራከት፣ ማጠናከርና የገበያ ድርሻቸውንም ማሻሻል ይገባል ብለዋል።
ሚኒስትሩ አያይዘውም በዘርፉ ተኪ ምርትን ማስፋትና ኤክስፖርትን ማበረታታት እንዲቻል በትኩረት እየተሰራ በመሆኑ ተቋማት ተቀናጅተው መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው የአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንተርፕራይዝ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ የስራ እድል በመፍጠር፣ አዳዲስና የፈጠራ ሀሳቦች በማመንጨትና ኢኮኖሚያዊ አቅምን በማጠናከር በኩል ጉልህ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ያነሱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ይህን ታሳቢ ያደረገ ስራ እየሰራ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ባንኩ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ከመስጠት ጀምሮ ኢንተርፕራይዞቹ በፋይናንስ እንዲደገፉ ከፍተኛ ገንዘብ መድቦና በዚህ ላይ የሚሰራ ሰፊ የሰው ኃይል አሰማርቶ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በተመሳሳይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለአምራች ኢንተርፕራይዞች እየቀረቡ ባሉ የፋይናንስ አቅርቦቶችና በዚህ ሂደት ውስጥ በሚገኙ የፋይናንስ ተቋማት ሚና ዙሪያ በተደረገው የፓናል ውይይት ላይ የተሳተፉት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንሲንግ ም/ፕሬዚዳንት አቶ አስፋው አበራ እንዳሉት የፋይናንስ አቅርቦቱን ለማሻሻል ባንኩ ልዩ መስኮቶችን በመክፈትና ከልዩ ልዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመቀናጀት እየሠራ ከመሆኑም በላይ የዘርፉን ልዩ ባህርይ ታሳቢ ያደረጉ አዳዲስ አሠራሮችን በመተግበር ላይ ነው፡፡
በመጨረሻም "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል የተከፈተውና "የኛ ምርት" የተሰኘው የአምራች ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እና ሌሎች ሚኒስትሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንትና የማኔጅመንት አባላት ባዛሩን የጎበኙ ሲሆን ባዛሩ ኢትዮጵያ የደረሰችበትን የአምራች ኢንተርፕራይዞች ቴክኖሎጂና የምርት እድገት ለመረዳት የሚያስችልና ከኤግዚቢሽንና ባዛሩ በሚገኘው ልምድ የአምራች ኢንተርፕራይዞችን አቅም ለማሳደግና ለማሻሻል የሚረዱ የድጋፍ ማዕቀፎች ለማዘጋጀት የጎላ ሚና እንደሚኖረው ተመላክቷል፡፡
"የኛ ምርት" ኤግዚቢሽንና ባዛር በቀጣይ በየዓመቱ በተመሳሳይ ወቅት ለማካሄድ እቅድ እንደተያዘም ተመላክቷል፡፡
የአምራች ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የአገር ውስጥ አምራች ኢንተርፕራይዞች የተሻለ ምርት እንዲያመርቱ ከሚሰጠው ሁሉን አቀፍ ድጋፍ በተጨማሪ ምርቶቻቸው እንዲተዋወቁ ኤግዚቢሽንና ባዛር ማዘጋጀቱን በማመስገን ድጋፉ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍37❤4
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለሊዝ ፋይናንስ ደንበኞች የትራክተር፣ ኮምባይን ሐርቨስተር እና የኤክስካቫተር ማሽነሪዎችን አስረክቧል፡፡ ይህን አስመልክቶ የደንበኞችን አስተያየት እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው መልዕክት የተካተተበትን ፕሮግራም መስፈንጠሪያውን በመጫን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=C8JfqegidHg
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
https://www.youtube.com/watch?v=C8JfqegidHg
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
YouTube
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሳምንታዊ የቴሌቪዥን ፕሮግራም "አፍላገ ልማት" (ክፍል 73) - ከስኬት በስተጀርባ፣ የዓለም-አቀፍ የልማት ባንኮች ተሞክሮ እና ድራማ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ "አፍላገ ልማት" የቴሌቪዥን ፕሮግራም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እሁድ 2፡50 እስከ 3፡30 የሚተላለፍ ሳምንታዊ ፕሮግራም፡፡
#DBE
#lease
#financing
#agriculture
#manufacturing
#DBE
#lease
#financing
#agriculture
#manufacturing
👍26❤7🤝2
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዲስትሪክትን የመስክ ምልከታ በማድረግ የስራ እንቅስቃሴውን ጎበኙ::
የቋሚ ኮሚቴው ቡድን አስተባባሪ የተከበሩ አቶ እያሱ ዛላ እንዳሉት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በክልሉ የሰራው ሥራ አድንቀው ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን እና ለስራው ውጤታማነት የተበዳሪዎች የስልጠና ቀድሞ መውሰድ ውጤቱን ከፍ አድርጎታል፡፡
አስተባባሪው አያይዘውም ባንኩ ሲሰጥ የነበረው የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተር ፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል::
ቋሚ ኮሚቴው በባንኩ ብድር ተመቻችቶላቸው ምርት የጀመሩ የተለያዩ አምራች ተቋማትን በአካል ተገኝተው ምልከታ አድርገዋል::
በሌላ በኩል ባንኩ በደንበኝነት የሚያውቃቸው ተበዳሪዎች ቋሚ ኮሚቴው ባንኩ የሰጠውን ብድር የት እንደደረሰ ለመመልከት በጠየቀበት ጊዜ ድርጅታቸውን ማስጎብኘታቸው ባለሀብቱ እና ባንኩ ያላቸውን መደጋገፍ የሚያሳይ መሆኑንም በምልከታቸው ወቅት መታዘባቸውን ገልጸዋል፡፡
በአከባቢው ከሚለማው ፕሮጀክት ቀዳሚ የሆነውን የቡና ልማት ፕሮጀክትን ቋሚ ኮሚቴው በተመለከተበት ወቅት በዘርፉ ለሚታየው የቡና ገበያ መቀዛቀዝ መንግስት መፍትሔ እንዲሰጣችው አልሚዎች ጠይቀዋል፡፡
ቋሚ ኮሚቴው ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሚዛን ቅርንጫፍ ምርታማነትን ለማረጋገጥ እና ለሚፈለገው የሥራ መስክ የሚያደርገው ድጋፍ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ጠቁሞ፣ በቡና ልማቱ ዙሪያ የገበያ ትስስሩ ድጋፍ ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝቧል::
በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው አስተባባሪ አቶ እያሱ ባንኩ ከነበረበት ችግር ተላቆ በሀገር ደረጃ እያበረከተ ያለው አስተዋጽጾ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው ፣ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ማድርግ ከቻሉ በባንኩ እየተመዘገበ ያለው ለውጥ እና እድገት ከዚህም ሊልቅ የሚችል ነው ሲሉ በመስክ ተገኝተው ምልከታና ጉብኝት ለተሳተፉ የቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ለባንኩ አመራሮች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
የቋሚ ኮሚቴው ቡድን አስተባባሪ የተከበሩ አቶ እያሱ ዛላ እንዳሉት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በክልሉ የሰራው ሥራ አድንቀው ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን እና ለስራው ውጤታማነት የተበዳሪዎች የስልጠና ቀድሞ መውሰድ ውጤቱን ከፍ አድርጎታል፡፡
አስተባባሪው አያይዘውም ባንኩ ሲሰጥ የነበረው የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተር ፕራይዝ አንቀሳቃሾች ስልጠና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል::
ቋሚ ኮሚቴው በባንኩ ብድር ተመቻችቶላቸው ምርት የጀመሩ የተለያዩ አምራች ተቋማትን በአካል ተገኝተው ምልከታ አድርገዋል::
በሌላ በኩል ባንኩ በደንበኝነት የሚያውቃቸው ተበዳሪዎች ቋሚ ኮሚቴው ባንኩ የሰጠውን ብድር የት እንደደረሰ ለመመልከት በጠየቀበት ጊዜ ድርጅታቸውን ማስጎብኘታቸው ባለሀብቱ እና ባንኩ ያላቸውን መደጋገፍ የሚያሳይ መሆኑንም በምልከታቸው ወቅት መታዘባቸውን ገልጸዋል፡፡
በአከባቢው ከሚለማው ፕሮጀክት ቀዳሚ የሆነውን የቡና ልማት ፕሮጀክትን ቋሚ ኮሚቴው በተመለከተበት ወቅት በዘርፉ ለሚታየው የቡና ገበያ መቀዛቀዝ መንግስት መፍትሔ እንዲሰጣችው አልሚዎች ጠይቀዋል፡፡
ቋሚ ኮሚቴው ለኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሚዛን ቅርንጫፍ ምርታማነትን ለማረጋገጥ እና ለሚፈለገው የሥራ መስክ የሚያደርገው ድጋፍ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ጠቁሞ፣ በቡና ልማቱ ዙሪያ የገበያ ትስስሩ ድጋፍ ማጠናከር እንደሚገባም አስገንዝቧል::
በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው አስተባባሪ አቶ እያሱ ባንኩ ከነበረበት ችግር ተላቆ በሀገር ደረጃ እያበረከተ ያለው አስተዋጽጾ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸው ፣ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ማድርግ ከቻሉ በባንኩ እየተመዘገበ ያለው ለውጥ እና እድገት ከዚህም ሊልቅ የሚችል ነው ሲሉ በመስክ ተገኝተው ምልከታና ጉብኝት ለተሳተፉ የቋሚ ኮሚቴ አባላት እና ለባንኩ አመራሮች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሚለቃቸውን ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ዌብሳይት፡- www.dbe.com.et
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/dbethiopia
ቴሌግራም፦ https://t.me/DBE1900
ትዊተር፡- https://twitter.com/DBE_Ethiopia
ሊንክድኢን፡- https://www.linkedin.com/in/dbe1900/
ዩቱብ:- https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
በመወዳጀት፣ ለሌሎች በማጋራትና ገንቢ አስተያየትዎን በመስጠት ቤተሰብ ይሁኑ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍35❤4👏1