Development Bank of Ethiopia (DBE)
23.3K subscribers
2.11K photos
76 videos
4 files
580 links
The development bank of Ethiopia (DBE) is one of the financial institutions engaged in providing short, medium and long term development credits.
Download Telegram
በትጋት የተገኘ ውጤት
ዜማ ያሬድ

ወደ ንግድ አለም የገቡት ገና በልጅነታቸው ነው፡፡ ገጠር ውስጥ በንግድ ላይ ከተሰማሩ ባለሃብት ጋር በመጠጋት ንግድን እንደተለማመዱ ይናገራሉ የዛሬው ባለታሪካችን አቶ ታምራት አንጋሳ፡፡ አቶ ታምራት ንግድን አንድ ብለው የጀመሩት በየከፍለ አገሩ ረጅም ጉዞ በእግራቸው በመጓዝ ቡና በብቅሎ ጭነው በማከፋፈል ነበር፡፡ ታዲያ የአሰሪዎቻቸውን ቡና ጭነው ሩቅ ሄደው በማከፋፈል የጫኑትን አንድ አራተኛ ለጉልበታቸው ዋጋ በመቀበል ቀስ በቀስ የራሳቸውን ስራ ወደመስራት እንደተሸጋገሩ አጫውተውናል፡፡

ታታሪው አቶ ታምራት ከብዙ ልፋት በኋላ የራሳቸውን ጭነት ማጓጓዣ በቅሎ በመግዛት ከአሰሪያቸው በተጨማሪ የራሳቸውን ጭነት ይዘው በማከፋፈል ካፒታላቸውን ማሳደግ ቀጠሉ፡፡ እንዲህ እያሉ ቀስ በቀስ ለሌላ ስራ ማስጀመሪያ የሚሆን ገንዘብ ካጠራቀሙ ሙሉ በሙሉ የእህል ንግድ ጀመሩ፡፡

በመስራት ውስጥ በመልፋት ውስጥ ስኬት እንዳለ የሚያምኑት አቶ ታምራት ከብዙ ጥረት በኋላ ወዳሰቡት መንገድ መድረስ መቻላቸውን ይናገራሉ፡፡ "ስኬታማ የሚያደርገው መስራት ነው፡፡ እኔ ሁሌም ቢሆን ወደኋላ ተመልሼ የወደኩበትን ሳይሆን ወደፊት ማድረግ የምችለውን ብቻ ነው የማስበው ለዛም ነው በብዙ ችግር ውስጥ አልፌ ስኬታማ መሆን የቻልኩት" ይላሉ፡፡

አቶ ታምራት በአንድ በቅሎ የጀመሩትን ስራ እያሳደጉ የስራ መኪና ወደመግዛት ተሸጋገሩ፡፡ ጥረታቸውን በመቀጠልም ስራቸውን እያሰፉ ተጨማሪ መኪኖችን በመግዛት የካፒታል አቅማቸውን ማጠናከር ችለዋል፡፡

በዚህ ሁኔታ ላይ እያሉ ህልማቸውን እውን የሚያደርግ ዜና ሰሙ፡፡ አቶ ታምራት ፋብሪካ መትከል እቅዳቸው ነበርና ወሊሶ ውስጥ አንድ የዱቄት ፋብሪካ እንደሚሸጥ ይፋ ይሆናል፡፡ በባለቤትነት የያዙት ዱቄት ፋብሪካ ለሽያጭ ቀረበ፡፡ ይህን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም አቶ ታምራት እጃቸው ላይ ያለውን መኪና በመሸጥ በ2006 ለሽያጭ የቀረበውን የዱቄት ፋብሪካ ገዙ፡፡

አቶ ታምራት የወሊሶ የዱቄት ፋብሪካን እንዳሰቡት ገዝተው ወደስራ ከገቡ በኋላ ግን ማሽኑ አሮጌ በመሆኑ ለስራ አስቸጋሪ ሆነባቸው፡፡ በተደጋጋሚ እየተበላሸ ያስቸገራቸውን ማሽን ለማስጠገን የመንቀሳቀሻ መኪና ሳይቀር በመሸጥ ፋብሪካው የመክሰር አደጋ ውስጥ እያለ ነው ልማት ባንክ በ2010 ዓ.ም ፋብሪካቸውን የታደገላቸው፡፡

"ልማት ባንክ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ሆኜ የደረሰልኝ፡፡ ልማት ባንክ ለእኔ ችግሬን ያቃለለልኝ ባንክ ነው" የሚሉት አቶ ታምራት በ2010 ዓ.ም በሊዝ ፋይናንስ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የስንዴ ዱቄት መፍጫ ማሽን አቅርቦላቸዋል፡፡ አቶ ታምራት ለአምስት ተከታታይ ዓመታት ብድራቸውን ሳያዛንፉ በመከፈል ፋብሪካው በእግሩ እንዲቆም ማድረግ የቻሉ ታታሪ ናቸው፡፡ አቶ ታምራት ተጨማሪ የበቆሎ ዱቄት መፍጫ ማሽን በሊዝ ፋይናንስ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በመውሰድ የተከሉ ሲሆን በራሳቸው ወጪ ደግሞ ሁለት የዳቦ ማሽኖች እና የከብቶች መኖ ማቀነባበሪያ እውን ማድረግ ችለዋል፡፡

በወሊሶ የዱቄት ፋብሪካ 72 ጊዜያውና ቋሚ ሰራተኞች ተቀጥረው የሚሰሩ ሲሆን በቀጣይ የመኮረኒ እና የፓስታ ፋብሪካም ለመትከል እቅድ እንደያዙ አጫውተውናል፡፡ "ለእኔ ስኬት መስራት ነው፡፡ ሰው ከሰራ ይለወጣል፡፡ እኔ በብዙ ድካም ውስጥ ነው እዚህ የደረስኩት፡፡" ያሉት አቶ ታምራት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሰራተኞች ያላቸው መተባበር እና የሚሰጡት ምክር አዳዲስ ስራዎችን እንዲያስቡ እንደረዳቸው በመግለጽ በችግሬ ጊዜ የደረሰልኝ ባንክ ላመሰግን እፈልጋለሁ ብለዋል፡፡

በትጋት፣ በትዕግስት መስራት ከራስ አልፎ ማህበረሰብን ብሎም አገርን መለወጥ የሚያስችል ኢኮኖሚያዊ አቅም ለመፍጠር ያሳችላል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዓላማ በጋራ ጥረት አገር ለማሻገር የቆረጡ እጆችን ማገዝ ነው፡፡ በዚህም ባለፉት ዓመታት በፈጸማቸው ተግባራት በርካቶችን መጥቀም የቻለ የፖለሲ ባንክ ነው፡፡
👍42❤14
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርና ሜካናይዜሽን ስራ ላይ ለተሰማሩ የባንኩ ደንበኞች ትራክተሮችንና የኮምባይነር ሀርቨስተር ማሽኖችን በካፒታል ዕቃ ኪራይ የፋይናንስ ሞዳሊቲ በማቅረብ የእርሻውን ክፍለ ኢኮኖሚ እየደገፈ ይገኛል፡፡

ባንካችን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ የግብርና ስራውን ማቀላጠፍ የሚችሉ የትራክተር እና ኮምባይነር ሀርቨስተር ማሽኖችን ለደንበኞች በሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት በማቅረብ የራሱን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡

በተመሳሳይ በማዕድን ዘርፍ ለተሰማሩ የኤክስካቫተር እንዲሁም በማስጎብኘት ስራ ላይ ለተሰማሩ ደንበኞች ደግሞ የተለያዩ ዓይነት መኪኖችን በማቅረብ አገልግሎቱን ለደንበኞች ተደራሽ እያደረገ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍46❤19🤝3
የጃፓን ልማት ባንክ
ድብቁ የኢኮኖሚ የልማት ኃይል

ሙሉ መረጃውን መስፈንጠሪያውን ተጭነው ይመልከቱ:-

https://www.youtube.com/watch?v=P4WwEoVGlCA&t=524s
👍25❤4👏3
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ከነበረበት 2 ቢሊየን ብር ወደ 11 ቢሊየን ብር አደገ፡፡

ከሰሞኑ በግብርና ዘርፍ ለተሰማሩ ደንበኞቹ 15 ትራክተርና 10 ኮምባይን ሀርቨስተር እንዲሁም በማዕድን ዘርፍ ለተሰማሩ ደንበኞቹ 14 ኤክስካቫተር በሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ዘርፍ አቅርቧል።

የኮምባይን ሀርቨስተር መሳሪያዎቹ 72 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመቱ ሲሆን፤ ትራክተሮቹ ከ43 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲሁም ኤክስካቫተሮቹ  áЍ87 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ መሆናቸው ነው በርክክብ ስርዓቱ ላይ የተገለጸው።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው፤ ባንኩ ላለፉት አምስት ዓመታት የተለያዩ የሪፎርም ሥራዎችን አከናውኖ በኢትዮጵያ ካሉ ባንኮች ሁለተኛውን ከፍተኛ ካፒታል ማስመዝገብ መቻሉን በርክክቡ ወቅት ገልጸዋል።

በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ አገልግሎትና ሌሎችም ዘርፎች  ለተሰማሩ ዜጎች የሚያደርገው ድጋፍ በየጊዜው እድገት እያሳየ መሆኑንም አንስተዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ባንኩ ለደንበኞች ለማቅረብ ካቀደው 51 ቢሊዮን ብር ውስጥ 15 ቢሊዮን ብር የሚሆነውን ለግብርና ዘርፉ የተመደበ መሆኑንም ገልፀዋል።

በግብርናው ዘርፍ የተደረገው ግብርና ማሽነሪዎች ርክክብ የግብርና ሜካናይዜሽንን በማጠናከር የምርት ብክነትን ለመቀነስ የሚያስችል ከመሆኑም ባሻገር የአርሶ አደሩን ጊዜና ጉልበት ለመቆጠብ አስተዋፅዖ የሚኖረው መሆኑንም አስረድተዋል።
የግብርና ዘርፉን ማዘመንና ምርታማነቱን ማሳደግ ኢንዱስትሪዎች በቂ ጥሬ ዕቃ አግኝተው በሙሉ አቅማቸው እንዲያመርቱ እገዛ ያደርጋልም ተብሏል።

በማዕድን ዘርፉ የተሰጡ መሳሪያዎችም አገሪቱ በዘርፉ ያላትን ሰፊ ዕድል እንድትጠቀም የሚያስችል መሆኑን ጠቅሰው፤ በሊዝ ፋይናንሲንግ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ባንኩ በትኩረት እየሰራ መሆኑም ነው የተገለጸው።

ባንኩ ለ486 ደንበኞች ከ580 በላይ ለግብርና አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዘመናዊ ማሽነሪዎችን ከ100 በላይ የሚሆኑ ለማዕድን ዘርፉ የሚያግዙ  ኤክስካቫተሮችን ለደንበኞቹ ማቅረቡንም ተናግረዋል።

አቶ እንዳለ መኩሪያ እና አቶ ፈይሳ  ቡታ፤ የተረከቧቸው መሳሪያዎች ሥራቸውን የሚያዘምኑ ከመሆናቸው ባሻገር ገቢ ምርቶችን ለመተካትና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን ለማሳደግ የሚያስችሉ መሆኑን ገልፀዋል።

ሌላኛው ተረካቢ አቶ ዳንኤል ወልደሰንበት፤ የተረከቡት ኤክስካቫተር በተሰማሩበት የማዕድን ዘርፉ የላቀ ጠቀሜታ የሚሰጣቸው መሆኑን ተናግረዋል ።
👍41❤7