የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ2016 በጀት ዓመት 51 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።
የባንኩ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በባንኩ ላይ ይነሱ የነበሩ የፍትሃዊነት ጥያቄዎች እየተቀረፉ በመምጣታቸው ከተለያየ የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ ባለሀብቶች ለባንኩ የብድር ጥያቄ እያቀረቡ ነው።
ይህንን ጥያቄ ለመመለስም በ2016 በጀት ዓመት 51 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል። ባንኩ የፖሊሲ ባንክ እንደመሆኑ ግብርናና አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ባለፈው በጀት ዓመት የሁለት ግዙፍ የሲሚንቶ ፋብሪካዎችን የብድር ጥያቄ አጽድቋል።
በተጨማሪም የቡናን ምርታማነት በሦስት እጥፍ ማሳደግ ለሚችል ሥራ ብድር ማጽደቁንም ገልጸዋል። በቀጣይ ጊዜያትም የውጭ ምንዛሪ ለሚያስገኙ ምርቶች እና ተኪ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ፋይናንስ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።
አሁን ላይ ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ ለማድረግ በሚያቀርቡት የአዋጭነት ጥናት መሠረት የብድር አገልግሎት እያቀረበ መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ዮሐንስ፤ በ2015 በጀት ዓመት 50 ሺህ ዜጎችን ለማሰልጠን አቅዶ የተፈጠረው ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ ለ110 ሺህ ዜጎች ሥልጠና ሰጥቷል።
በ2016 በጀት ዓመትም ሥልጠናው ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ ያለውን ፍላጎት መሠረት በማድረግም ከፍ ያለ በጀት ተይዟል ብለዋል። ለእነዚህ ዜጎች ፋይናንስ ለማቅረብም ባንኩ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ከዚህ ቀደም በዋስትና ምክንያት የብድር አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥማቸው ፕሮጀክቶችን በማስያዣነት ተጠቅሞ ብድር ሲሰጥ መቆየቱን ያስታወሱት ዶክተር ዮሐንስ፤ ይህም ባለሀብቶች በዋስትና ችግር ከኢንቨስትመንት እንዳይወጡ ማድረግ አስችሏል ሲሉ አስረድተዋል።
በቀጣይነትም ሀሳብ ላላቸው ዜጎች ፋይናንስ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም በ2016 የተያዘው በጀት ከወለድ ነጻ የፋይናንስ አቅርቦትን የሚያካትት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ባንኩ ብድር ሰጥቶ የማያስመልስ ከሆነ የሕዝብ ገንዘብ ብክነት ምክንያት ይሆናል ያሉት ዶክተር ዮሐንስ፤ ለዚህም ለብድር ማስመለስ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም 13 ነጥብ አምሥት ቢሊዮን ብር ማስመለስ ችሏል ብለዋል።
ከብድር አቅርቦት ፍትሃዊነት ጋር ተያይዘው የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፤ ከሁሉም ክልሎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በሙሉ እያስተናገደ ነው ብለዋል።
በቀጣይነትም ፍትሐዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አጠቃላይ የብድር መጠኑ 75 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱም ተመላክቷል።
ባንኩ በ2015 በጀት ዓመት ስድስት ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር ማትረፉን እና የባንኩ አጠቃላይ ካፒታልም በ2011 በጀት ዓመት ከነበረበት ሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር፤ በ2015 በጀት ዓመት ወደ 38 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱን መግለጹ ይታወሳል።
የባንኩ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው እንደገለጹት፤ ባለፉት ዓመታት በባንኩ ላይ ይነሱ የነበሩ የፍትሃዊነት ጥያቄዎች እየተቀረፉ በመምጣታቸው ከተለያየ የሀገሪቱ ክፍሎች በርካታ ባለሀብቶች ለባንኩ የብድር ጥያቄ እያቀረቡ ነው።
ይህንን ጥያቄ ለመመለስም በ2016 በጀት ዓመት 51 ቢሊዮን ብር ብድር ለመስጠት ዝግጅት ተደርጓል። ባንኩ የፖሊሲ ባንክ እንደመሆኑ ግብርናና አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ባለፈው በጀት ዓመት የሁለት ግዙፍ የሲሚንቶ ፋብሪካዎችን የብድር ጥያቄ አጽድቋል።
በተጨማሪም የቡናን ምርታማነት በሦስት እጥፍ ማሳደግ ለሚችል ሥራ ብድር ማጽደቁንም ገልጸዋል። በቀጣይ ጊዜያትም የውጭ ምንዛሪ ለሚያስገኙ ምርቶች እና ተኪ ምርቶች ላይ ትኩረት አድርጎ ፋይናንስ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።
አሁን ላይ ዜጎችን አሰልጥኖ ወደ ኢንቨስትመንት እንዲገቡ ለማድረግ በሚያቀርቡት የአዋጭነት ጥናት መሠረት የብድር አገልግሎት እያቀረበ መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ዮሐንስ፤ በ2015 በጀት ዓመት 50 ሺህ ዜጎችን ለማሰልጠን አቅዶ የተፈጠረው ፍላጎት ከፍተኛ በመሆኑ ለ110 ሺህ ዜጎች ሥልጠና ሰጥቷል።
በ2016 በጀት ዓመትም ሥልጠናው ተጠናክሮ ይቀጥላል፤ ያለውን ፍላጎት መሠረት በማድረግም ከፍ ያለ በጀት ተይዟል ብለዋል። ለእነዚህ ዜጎች ፋይናንስ ለማቅረብም ባንኩ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅርበት እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ከዚህ ቀደም በዋስትና ምክንያት የብድር አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥማቸው ፕሮጀክቶችን በማስያዣነት ተጠቅሞ ብድር ሲሰጥ መቆየቱን ያስታወሱት ዶክተር ዮሐንስ፤ ይህም ባለሀብቶች በዋስትና ችግር ከኢንቨስትመንት እንዳይወጡ ማድረግ አስችሏል ሲሉ አስረድተዋል።
በቀጣይነትም ሀሳብ ላላቸው ዜጎች ፋይናንስ ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልጸዋል። በተጨማሪም በ2016 የተያዘው በጀት ከወለድ ነጻ የፋይናንስ አቅርቦትን የሚያካትት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ባንኩ ብድር ሰጥቶ የማያስመልስ ከሆነ የሕዝብ ገንዘብ ብክነት ምክንያት ይሆናል ያሉት ዶክተር ዮሐንስ፤ ለዚህም ለብድር ማስመለስ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም 13 ነጥብ አምሥት ቢሊዮን ብር ማስመለስ ችሏል ብለዋል።
ከብድር አቅርቦት ፍትሃዊነት ጋር ተያይዘው የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለማስወገድ ትኩረት ሰጥቶ ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፤ ከሁሉም ክልሎች የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በሙሉ እያስተናገደ ነው ብለዋል።
በቀጣይነትም ፍትሐዊ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል ብለዋል። የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አጠቃላይ የብድር መጠኑ 75 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱም ተመላክቷል።
ባንኩ በ2015 በጀት ዓመት ስድስት ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር ማትረፉን እና የባንኩ አጠቃላይ ካፒታልም በ2011 በጀት ዓመት ከነበረበት ሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር፤ በ2015 በጀት ዓመት ወደ 38 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱን መግለጹ ይታወሳል።
👍58❤10👏4
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ትኩረት በተሰጣቸው የልማት ዘርፎች እድገትና ልማት እንዲመጣ የሚያደርገውን ድጋፍ እና ተሳትፎ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው የባንኩን የ2015 በጀት አመት አፈጻጸም እና የ2016 እቅድን አስመልክቶ ከማኔጅመንት አባላትና በተለያዩ ደረጃዎች ከሚገኙ የስራ መሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ነው ይህን የገለጹት፡፡
ባንኩ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ሰፊ አሻራን የማሳረፍ ሃላፊነት ያለበት መሆኑን ያብራሩት ዶክተር ዮሐንስ ሃገራዊ ሃብት እንዲፈጠር ብሎም የዜጎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከእስካሁኑ የበለጠ ስራ ከፊታችን ይጠብቀናል ብለዋል፡፡
ከዚህ አንጽር ባንኩ የተገበረውን ሪፎርም ተከትሎ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት በላቀ ደረጃ ማስቀጠል በቀጣይ በከፍተኛ ትኩረት የሚከናወን ተግባር ይሆናል ነው ያሉት፡፡
ባንኩ 11.1 በመቶ የደረሰውን የተበላሸ ብድር ምጣኔ በ2016 በጀት አመት ወደ 5 በመቶ በማውረድ በአለም አቀፍ የልማት ባንኮች ደረጃ የመሰለፍ ግቡን ለማሳካት ማቀዱን በውይይቱ ተገልጿል፡፡
ከብድር አቅርቦት ጋር ተያይዞ ባንኩ በ2016 በጀት አመት 51 ቢሊዮን ብር ለማበደር ያቀደ ሲሆን ፣ይህም ከ2015 በጀት አመት አንጻር የ10 በመቶ እድገት ያለው ነው፡፡
ባንኩ በ2015 በጀት አመት ላስመዘገበው ስኬት የባንኩ የስራ አመራር ቦርድ፤ ማኔጅመንት እና መላው ሰራተኛ ከፍተኛ አስተዋጽዖ የነበራቸው መሆኑን የገለጹት የባንኩ ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው ለ2016 በጀት አመት እቅድ መሳካትም ሁሉም ባለድርሻ አካል ይህንኑ አስተዋጽዖ አጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው የባንኩን የ2015 በጀት አመት አፈጻጸም እና የ2016 እቅድን አስመልክቶ ከማኔጅመንት አባላትና በተለያዩ ደረጃዎች ከሚገኙ የስራ መሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ነው ይህን የገለጹት፡፡
ባንኩ በሃገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ሰፊ አሻራን የማሳረፍ ሃላፊነት ያለበት መሆኑን ያብራሩት ዶክተር ዮሐንስ ሃገራዊ ሃብት እንዲፈጠር ብሎም የዜጎች ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ከእስካሁኑ የበለጠ ስራ ከፊታችን ይጠብቀናል ብለዋል፡፡
ከዚህ አንጽር ባንኩ የተገበረውን ሪፎርም ተከትሎ እየተመዘገበ ያለውን ስኬት በላቀ ደረጃ ማስቀጠል በቀጣይ በከፍተኛ ትኩረት የሚከናወን ተግባር ይሆናል ነው ያሉት፡፡
ባንኩ 11.1 በመቶ የደረሰውን የተበላሸ ብድር ምጣኔ በ2016 በጀት አመት ወደ 5 በመቶ በማውረድ በአለም አቀፍ የልማት ባንኮች ደረጃ የመሰለፍ ግቡን ለማሳካት ማቀዱን በውይይቱ ተገልጿል፡፡
ከብድር አቅርቦት ጋር ተያይዞ ባንኩ በ2016 በጀት አመት 51 ቢሊዮን ብር ለማበደር ያቀደ ሲሆን ፣ይህም ከ2015 በጀት አመት አንጻር የ10 በመቶ እድገት ያለው ነው፡፡
ባንኩ በ2015 በጀት አመት ላስመዘገበው ስኬት የባንኩ የስራ አመራር ቦርድ፤ ማኔጅመንት እና መላው ሰራተኛ ከፍተኛ አስተዋጽዖ የነበራቸው መሆኑን የገለጹት የባንኩ ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው ለ2016 በጀት አመት እቅድ መሳካትም ሁሉም ባለድርሻ አካል ይህንኑ አስተዋጽዖ አጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
👍45👏23❤19
የመንግሰት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የ2022/2023 ዓ.ም የስራ አፈጻጸምን በዛሬው እለት የገመገመ ሲሆን በቀጣይ እቅዶች ላይም ውይይት በማድረግ መሻሻል የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
በውይይቱ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ያለፈው በጀት ዓመት አፈጻጸምን በተመለከተ ሪፖርት ያቀረቡት የባንኩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው ባንኩ በሪፎርሙ እተገብራቸዋለሁ ብሎ ካስቀመጣቸው ሰባት ምሰሶች አኳያ በበጀት ዓመቱ በሁሉም መለኪያ የተሻለ የሚባል አፈጸጸም ማስመዝገቡን ተናግረዋል፡፡
የመንግሰት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃብታሙ ኃ/ሚካኤል በበኩላቸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በጥሩ መሰረት ላይ እየተገነባ የሚገኝ ባንክ መሆኑን በመግለጽ የባንኩ ቦርድ፣ ማኔጅመነት እና ሰራተኞች በተቀናጀ መልኩ በመስራት የመበተን አደጋ ውስጥ የነበረን ባንክ እንዲያንሰራራ በማድረግ ትርፋማ እንዲሆን በማድረጋቸው ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል፡፡
በመንግሰት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የቀረቡ ዝርዝር ግምገማዎችን በዝርዝር የምንመለስበት ይሆናል፡፡
በውይይቱ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ያለፈው በጀት ዓመት አፈጻጸምን በተመለከተ ሪፖርት ያቀረቡት የባንኩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው ባንኩ በሪፎርሙ እተገብራቸዋለሁ ብሎ ካስቀመጣቸው ሰባት ምሰሶች አኳያ በበጀት ዓመቱ በሁሉም መለኪያ የተሻለ የሚባል አፈጸጸም ማስመዝገቡን ተናግረዋል፡፡
የመንግሰት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃብታሙ ኃ/ሚካኤል በበኩላቸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በጥሩ መሰረት ላይ እየተገነባ የሚገኝ ባንክ መሆኑን በመግለጽ የባንኩ ቦርድ፣ ማኔጅመነት እና ሰራተኞች በተቀናጀ መልኩ በመስራት የመበተን አደጋ ውስጥ የነበረን ባንክ እንዲያንሰራራ በማድረግ ትርፋማ እንዲሆን በማድረጋቸው ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል፡፡
በመንግሰት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር የቀረቡ ዝርዝር ግምገማዎችን በዝርዝር የምንመለስበት ይሆናል፡፡
👍65👏15❤10
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ለማግኘት መሟላት ያለባቸዉ መስፈርቶችን በሚመለከት ዝርዝር መረጃ በዚህ የፌስ ቡክ ገጻችን ላይ ማጋራታችን ይታወሳል፡፡ ሆኖም በተደጋጋሚ መስፈረቱ ምን እንደሆነ መረጃ እንድናጋራችሁ በጠየቃችሁት መሰረት መረጃውን አጋርተናል፡፡ ለበለጠ መረጃ በአቅራቢያችሁ ወደሚገኝ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዲስትሪክት እና ቅርንጫፎች እንዲሁም በዋና መስሪያ ቤት በመምጣት መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
👍70❤45👏5🤝2
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ115 ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ለአገር ልማት የሚጠቅሙ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ፋይናንስ በማድረግ አገራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ የሚገኝ የፖሊሲ ባንክ ነው፡፡ ባንኩ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በርካታ ተግዳሮቶች የገጠሙት ቢሆንም ዛሬ ላይ አገራዊ ኃላፊነቱን መወጣት የሚያስችለውን ሁለንተናዊ ብቃት በመላበስ ስኬታማ መሆን የቻለ ባንክ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በያዝነው በጀት ዓመት ብቻ ቆጥሮ ያስቀመጣቸውን እቅዶች ሳያዛንፍ በተሟላ መልኩ መፈጸም መቻሉ ቦርዱ፣ ማኔጅመንቱና ሰራተኛው በተናበበ መልኩ ተግባራትም ለመፈጸማቸውን ማረጋገጫ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በተጨማሪ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ባንኩ በለውጥ ጎዳና ውስጥ መሆኑን እውቅና በመስጠት በተለይ በበጀት ዓመቱ ላስመዘገበው ስኬት እውቅና በመስጠት አገራዊ የልማት እቅዶችን በማፋጠን በኩል ገንቢ ሚና የሚጫወትና ተስፋ የሚጣልበት ባንክ መሆኑን በቅርቡ ባደረገው የአፈጻጸም ግምገማ ላይ ማረጋገጡ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከአመሠራረቱ ጀምሮ በተለይ ለአርሶ አደሩ ቅርብ በመሆን የገበሬን ሥራ በሚያቀሉና ምርታማነትን በሚያፋጥኑ መላዎች ላይ አተኩሮ ሲሠራ የቆየ ነው፤ በዚህም ውጤት ማስመዝገብ የቻለ ባንክ እንደሆነ ከታሪኩ መረዳት ይቻላል፡፡
ባንኩ ባለፉት አራት የለውጥ ዓመታት ውጫዊና ውስጣዊ ተግዳሮቶችን መፍታት የሚችል ሁሉን አቀፍ የሆነ የሪፎርም ስትራቴጂ በመንደፍ አንጋፋነቱን ወደሚመጥን ለውጥ እየተሸጋገረ ይገኛል፡፡ በዚህም ከዓመት ዓመት ትርፋማ እየሆነ፣ ተደራሽነቱንም እያሰፋ የገበያ ክፍተት ባለባቸው መስኮች ላይ የሚመጡ የፋይናንስ ድጋፎችን አሠራሩን በጠበቀ መንገድ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ወደፊትም አገራችን በአራቱም ማዕዘን ያሏትን እምቅ አቅሞች በመጠቀም፣ ልማታችንን በማፋጠን ለአገራዊ እድገት የላቀ ፋይዳ ባላቸው ዘርፎች ላይ በትኩረት መሥራቱን ይቀጥላል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከአመሠራረቱ ጀምሮ በተለይ ለአርሶ አደሩ ቅርብ በመሆን የገበሬን ሥራ በሚያቀሉና ምርታማነትን በሚያፋጥኑ መላዎች ላይ አተኩሮ ሲሠራ የቆየ ነው፤ በዚህም ውጤት ማስመዝገብ የቻለ ባንክ እንደሆነ ከታሪኩ መረዳት ይቻላል፡፡
ባንኩ ባለፉት አራት የለውጥ ዓመታት ውጫዊና ውስጣዊ ተግዳሮቶችን መፍታት የሚችል ሁሉን አቀፍ የሆነ የሪፎርም ስትራቴጂ በመንደፍ አንጋፋነቱን ወደሚመጥን ለውጥ እየተሸጋገረ ይገኛል፡፡ በዚህም ከዓመት ዓመት ትርፋማ እየሆነ፣ ተደራሽነቱንም እያሰፋ የገበያ ክፍተት ባለባቸው መስኮች ላይ የሚመጡ የፋይናንስ ድጋፎችን አሠራሩን በጠበቀ መንገድ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ወደፊትም አገራችን በአራቱም ማዕዘን ያሏትን እምቅ አቅሞች በመጠቀም፣ ልማታችንን በማፋጠን ለአገራዊ እድገት የላቀ ፋይዳ ባላቸው ዘርፎች ላይ በትኩረት መሥራቱን ይቀጥላል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍75❤18
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ያሳለፍነውን የ2015 በጀት ዓመት ያቀዳቸውን ከግብ በማድረስ በውጤት አጠናቋል፡፡ ለዚህም የቦርድ አመራር አባላት፣ የማኔጅመንት አባላት እና ሰራተኞች ከፍ ያለ አበርክቶት ነበራቸው፡፡
ባንካችን 2016 ዓ.ም በአገራችን በግብርናውም ሆነ በኢንዱስትሪ መስክ የተሻለ እምርታ የሚያመጡ ፕሮጀክቶች ፋይናንስ በማድረግ በሙሉ ኃላፊነት እና ቁርጠኝነት ለመስራት ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡
ከባንካችን ጋር ለመስራት ለተዘጋጁ ሁሉ ያለውን የገበያ ክፍተት የሚሞላ፣ አገራችንን ያላትን አቅም መጠቀም የሚያስችል፣ አዳዲስና የስራ እድሎችን የሚፈጥር የስራ ሃሳብ ይዞ ለመጣ በአዳዲስ አገልግሎቶች እና በተሻለ ቅልጥፍና ደንበኞች የሚፈልጉትን አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናችንን በድጋሚ ያረጋግጣል፡፡
ኑ አብረን እንስራ፤ ልማታችንን በማፋጠን አገራችንን እናሻግር፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
ባንካችን 2016 ዓ.ም በአገራችን በግብርናውም ሆነ በኢንዱስትሪ መስክ የተሻለ እምርታ የሚያመጡ ፕሮጀክቶች ፋይናንስ በማድረግ በሙሉ ኃላፊነት እና ቁርጠኝነት ለመስራት ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡
ከባንካችን ጋር ለመስራት ለተዘጋጁ ሁሉ ያለውን የገበያ ክፍተት የሚሞላ፣ አገራችንን ያላትን አቅም መጠቀም የሚያስችል፣ አዳዲስና የስራ እድሎችን የሚፈጥር የስራ ሃሳብ ይዞ ለመጣ በአዳዲስ አገልግሎቶች እና በተሻለ ቅልጥፍና ደንበኞች የሚፈልጉትን አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናችንን በድጋሚ ያረጋግጣል፡፡
ኑ አብረን እንስራ፤ ልማታችንን በማፋጠን አገራችንን እናሻግር፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍66❤18👏7
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ባሰለፍነው በጀት ዓመት 241,272,016 ብር በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ለተቋማትና ለግለሰቦች በማበርከት ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የ2016 አዲስ አመት አስመልክቶም ባንኩ ለአቅመ ደካሞችና ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ የሕጻናት የልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ ለሰሊሆም የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ድርጅት፣ ለዲቦራ ፋውንዴሽንና በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ጨምሮ ነው ድጋፉን ያደረገው፡፡
በተለይም የሀገር ባለውለታዎችን ለሀገር ለአበረከቱት ሀገራዊ አስተዋጽዖ በምስጋና መልክ ላሉባቸው ጊዜያዊ ችግሮች ማቃለያ የተለያዩ ድጋፎችን አድርጓል፡፡
በአዲሱ 2016 ዓመት አከባበርን ምክንያት በማድረግም ከልብስ ስፌት ማሽን እስከ ተሸከርካሪ ድጋፎችን አድርጓል፡፡
ለወጣት ምንታምር በለጠ ግምቱ ከ1 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር በላይ የሆነ የልብስ ስፌት ማሽን፤ በእግር ሕመም ለሚሰቃየው ወጣት አማረ አምሳሉ ከቀረጥ ነጻ ተሸከርካሪ ማስገቢያ እና ለህክምና 800 ሺህ ብር፤ ለቀድሞው የሰርከስ ስፖርተኛ ለአቶ አረጋ ታደሰ ለሕክምና ወጭ የ500 ሺህ ብር ድጋፍ፤ ለቀድሞው የባንኩ ሰራተኛና የባንኩን ረቂቃ ታሪክ ለጻፉት ለአቶ አባት ባዬ 500 ሺህ ብር በተለያዩ አካባበዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች 19 ሚሊዮን ብር በድምሩ 23,167,500 ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
ባንኩ ለኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን መርጃ ማዕከል 31,000,000 ብር፤ ለነቀምቴ ከተማ አቅመ ደካማ ሴቶች የቤት እድሳት ማሰሪያ 1,009,900 ብር፣ በተለያዩ ምክንያቶች ተፈናቅለው በወለጋ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ድጋፍ ለማድረግ 7,000,000፣ በሌሎች አካባቢዎች ተፈናቅለው ለሚገኙ ወገኖች 12 ሚሊዮን ብር፣ ለእንሰት ምርምር ፕሮጀክት ለምርምር ቡድኑ አባላት 2,250,000 ብር በድምሩ 41,259,900 ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
ድጋፉን ያስረከቡት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው ባንኩ በማሕበራዊ ሃላፊነት ዘርፍ የሚያከናውናቸውን መልካም ተግባራት በአዲሱ ዓመትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
አሁን ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት ለናሙና ባንኩ ደገፈ እንጂ በየአካባቢው ያሉ ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻችን ሁሉም በጋራ በመረባረብ መረዳዳት ቢቻል ለብዙዎች መድረስ እንደሚቻል ዶክተር ዮሐንስ ጠይቀዋል፡፡
የ2016 አዲስ አመት አስመልክቶም ባንኩ ለአቅመ ደካሞችና ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ከ23 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ የሕጻናት የልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ ለሰሊሆም የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ድርጅት፣ ለዲቦራ ፋውንዴሽንና በቦረና ዞን በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ጨምሮ ነው ድጋፉን ያደረገው፡፡
በተለይም የሀገር ባለውለታዎችን ለሀገር ለአበረከቱት ሀገራዊ አስተዋጽዖ በምስጋና መልክ ላሉባቸው ጊዜያዊ ችግሮች ማቃለያ የተለያዩ ድጋፎችን አድርጓል፡፡
በአዲሱ 2016 ዓመት አከባበርን ምክንያት በማድረግም ከልብስ ስፌት ማሽን እስከ ተሸከርካሪ ድጋፎችን አድርጓል፡፡
ለወጣት ምንታምር በለጠ ግምቱ ከ1 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር በላይ የሆነ የልብስ ስፌት ማሽን፤ በእግር ሕመም ለሚሰቃየው ወጣት አማረ አምሳሉ ከቀረጥ ነጻ ተሸከርካሪ ማስገቢያ እና ለህክምና 800 ሺህ ብር፤ ለቀድሞው የሰርከስ ስፖርተኛ ለአቶ አረጋ ታደሰ ለሕክምና ወጭ የ500 ሺህ ብር ድጋፍ፤ ለቀድሞው የባንኩ ሰራተኛና የባንኩን ረቂቃ ታሪክ ለጻፉት ለአቶ አባት ባዬ 500 ሺህ ብር በተለያዩ አካባበዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች 19 ሚሊዮን ብር በድምሩ 23,167,500 ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
ባንኩ ለኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን መርጃ ማዕከል 31,000,000 ብር፤ ለነቀምቴ ከተማ አቅመ ደካማ ሴቶች የቤት እድሳት ማሰሪያ 1,009,900 ብር፣ በተለያዩ ምክንያቶች ተፈናቅለው በወለጋ መጠለያ ጣቢያ ለሚገኙ ተፈናቃዮች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ድጋፍ ለማድረግ 7,000,000፣ በሌሎች አካባቢዎች ተፈናቅለው ለሚገኙ ወገኖች 12 ሚሊዮን ብር፣ ለእንሰት ምርምር ፕሮጀክት ለምርምር ቡድኑ አባላት 2,250,000 ብር በድምሩ 41,259,900 ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡
ድጋፉን ያስረከቡት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው ባንኩ በማሕበራዊ ሃላፊነት ዘርፍ የሚያከናውናቸውን መልካም ተግባራት በአዲሱ ዓመትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
አሁን ድጋፍ የተደረገላቸው አካላት ለናሙና ባንኩ ደገፈ እንጂ በየአካባቢው ያሉ ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻችን ሁሉም በጋራ በመረባረብ መረዳዳት ቢቻል ለብዙዎች መድረስ እንደሚቻል ዶክተር ዮሐንስ ጠይቀዋል፡፡
👍58❤19🤝3
የሥልጠናው ዓላማ ምንድነው?
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ሥልጠና በመስጠት ወደ ቢዝነስ እንዲገቡ ድጋፍ የሚያደርግበት መሠረታዊ ዓላማ አለው፡፡
የዳበረ ኢኮኖሚ ባላቸው አገራት ውስጥ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሥራ ዕድል ፈጠራን በማስፋት፣ ለግዙፍ ኩባንያዎች ግብዓት በማቅረብ እና የገበያ ክፍተትን በመሙላት ኢኮኖሚያዊ እድገትን የሚያፋጥኑ ናቸው፡፡ በበርካታ ያደጉ አገራት ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ውስጥ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ድርሻ ላቅ ያለ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
የዓለምን ኢኮኖሚ እየመሩ ከሚገኙ አገራት መካከል ቻይና ተጠቃሽ ናት፡፡ ሰፊ የሕዝብ ቁጥር እንዳላት በሚነገርላት ቻይና የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት እድገት ያላቸው ድርሻ ከ60 በመቶ በላይ ነው፡፡ ከ75 በመቶ በላይ ያለውን የሰው ኃይል የሚሸከሙትም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸው፡፡ በጀርመን እና አሜሪካ ያለው ልምድም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ በአገራችን የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኵል የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ይታወቃል፡፡
በኢትዮጵያም ኢንተርፕራይዞችን በፋይናንስ እና በሥልጠና በመደገፍ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ በኵል መንግሥት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ብልጽግናንም ለማረጋገጥ ሀገር በቀል የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በሊዝ ፋይናንሲንግ ሞዳሊቲ መደገፍን እንደ አንድ አማራጭ ወስዶ በከፍተኛ ትኩረት እየሠራ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እንደ አንድ የፖሊሲ ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና በመስጠት እና በሊዝ ፋይናንስ የብድር ሞዳሊት የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ኢንተርፕራይዞች ለአገር ልማት የላቀ ሚና እንዲወጡ ለማስቻል እየሠራ ይገኛል፡፡
ባንኩ በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎቱ አሁን ባለው የፋይናንስ ገበያ ውስጥ ዋስትና (collateral) አስይዞ ብድር ለመበደርና ሥራ ለመሥራት ዕድሉ የሌላቸውን ነገር ግን በሀገር በኢኮኖሚ ውስጥ የላቀ ትርጉም ማምጣት የሚችሉትን የኅብረተሰብ ክፍሎች (The missing middle) ለመደገፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል፡፡ ባንኩ ለአገር ልማት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባላቸው ዘርፎች ላይ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች እንዲሰማሩ ለማነቃቃት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ መድቦ በተከታታይ እያሠለጠነ ነው፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአገራችን ያለውን እምቅ አቅም አሟጦ በመጠቀም ለአገር ልማት እንዲውል ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራቱን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ሥልጠና በመስጠት ወደ ቢዝነስ እንዲገቡ ድጋፍ የሚያደርግበት መሠረታዊ ዓላማ አለው፡፡
የዳበረ ኢኮኖሚ ባላቸው አገራት ውስጥ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሥራ ዕድል ፈጠራን በማስፋት፣ ለግዙፍ ኩባንያዎች ግብዓት በማቅረብ እና የገበያ ክፍተትን በመሙላት ኢኮኖሚያዊ እድገትን የሚያፋጥኑ ናቸው፡፡ በበርካታ ያደጉ አገራት ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ውስጥ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ድርሻ ላቅ ያለ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
የዓለምን ኢኮኖሚ እየመሩ ከሚገኙ አገራት መካከል ቻይና ተጠቃሽ ናት፡፡ ሰፊ የሕዝብ ቁጥር እንዳላት በሚነገርላት ቻይና የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት እድገት ያላቸው ድርሻ ከ60 በመቶ በላይ ነው፡፡ ከ75 በመቶ በላይ ያለውን የሰው ኃይል የሚሸከሙትም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ናቸው፡፡ በጀርመን እና አሜሪካ ያለው ልምድም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ በአገራችን የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር በኵል የላቀ ድርሻ እንዳላቸው ይታወቃል፡፡
በኢትዮጵያም ኢንተርፕራይዞችን በፋይናንስ እና በሥልጠና በመደገፍ በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ በኵል መንግሥት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን፣ ብልጽግናንም ለማረጋገጥ ሀገር በቀል የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን በሊዝ ፋይናንሲንግ ሞዳሊቲ መደገፍን እንደ አንድ አማራጭ ወስዶ በከፍተኛ ትኩረት እየሠራ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እንደ አንድ የፖሊሲ ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሥልጠና በመስጠት እና በሊዝ ፋይናንስ የብድር ሞዳሊት የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ኢንተርፕራይዞች ለአገር ልማት የላቀ ሚና እንዲወጡ ለማስቻል እየሠራ ይገኛል፡፡
ባንኩ በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎቱ አሁን ባለው የፋይናንስ ገበያ ውስጥ ዋስትና (collateral) አስይዞ ብድር ለመበደርና ሥራ ለመሥራት ዕድሉ የሌላቸውን ነገር ግን በሀገር በኢኮኖሚ ውስጥ የላቀ ትርጉም ማምጣት የሚችሉትን የኅብረተሰብ ክፍሎች (The missing middle) ለመደገፍ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል፡፡ ባንኩ ለአገር ልማት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ባላቸው ዘርፎች ላይ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች እንዲሰማሩ ለማነቃቃት ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ መድቦ በተከታታይ እያሠለጠነ ነው፡፡
በመሆኑም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአገራችን ያለውን እምቅ አቅም አሟጦ በመጠቀም ለአገር ልማት እንዲውል ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራቱን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
👍91❤16👏10
ህብረተሰቡ ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቦንድ እንዲገዛና ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ።
መስከረም 10 ቀን 2016 ዓ.ም በሳይንስ ሙዚየም በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ እንደተደረገው ለ አንድ ወር የሚቆይ ንቅናቄ "ግድቤን ለማጠናቀቅ ቃሌን አድሳለሁ" በሚል መርህ የሚካሄድ ሲሆን፣ ግድቡን በስኬት ለማጠናቀቅ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል፡፡
የ4ኛ ዙር የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎ ሀገር አቀፍ የሀብት ማሰባሰብ ንቅናቄ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጋራ ለመስራት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ነው በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ያስታወቁት።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የካፒታል ገበያና የሀብት ማሰባሰብ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳዊት አማረ እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአንድ ወር ለሚካሄደው የቦንድ ሽያጭና ሀብት ማሰባሰብ ንቅናቄን ጨምሮ በ2016 በጀት ዓመት ከ3.3 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ቦንዶች ታትመው ተሰራጭተዋል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ምትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍቅርተ ታምር በተያዘው 2016 ዓ.ም ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ለመሰብሰብ እቅድ መያዙን ገልጸው ቦንድ በማዘጋጀት እና በማስተባበር በኩል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ንግድ ባንክ በዋናነት የሚሰሩት ይሆናልም ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረ ጀምሮ ላለፉት 12 ዓመታት ቦንድ በማተም፣ በማሰራጨትና በመሸጥ እየተሳተፈ ሲሆን፣ ግንባታው እየተጠናቀቀ በመሆኑ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
መስከረም 10 ቀን 2016 ዓ.ም በሳይንስ ሙዚየም በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ይፋ እንደተደረገው ለ አንድ ወር የሚቆይ ንቅናቄ "ግድቤን ለማጠናቀቅ ቃሌን አድሳለሁ" በሚል መርህ የሚካሄድ ሲሆን፣ ግድቡን በስኬት ለማጠናቀቅ የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል፡፡
የ4ኛ ዙር የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎ ሀገር አቀፍ የሀብት ማሰባሰብ ንቅናቄ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጋራ ለመስራት ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ነው በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ያስታወቁት።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የካፒታል ገበያና የሀብት ማሰባሰብ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዳዊት አማረ እንዳስታወቁት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአንድ ወር ለሚካሄደው የቦንድ ሽያጭና ሀብት ማሰባሰብ ንቅናቄን ጨምሮ በ2016 በጀት ዓመት ከ3.3 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ቦንዶች ታትመው ተሰራጭተዋል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ምትል ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፍቅርተ ታምር በተያዘው 2016 ዓ.ም ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ለመሰብሰብ እቅድ መያዙን ገልጸው ቦንድ በማዘጋጀት እና በማስተባበር በኩል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ንግድ ባንክ በዋናነት የሚሰሩት ይሆናልም ነው ያሉት።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጀመረ ጀምሮ ላለፉት 12 ዓመታት ቦንድ በማተም፣ በማሰራጨትና በመሸጥ እየተሳተፈ ሲሆን፣ ግንባታው እየተጠናቀቀ በመሆኑ ህብረተሰቡ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
👍49❤14🤝3