Development Bank of Ethiopia (DBE)
23.3K subscribers
2.1K photos
76 videos
4 files
578 links
The development bank of Ethiopia (DBE) is one of the financial institutions engaged in providing short, medium and long term development credits.
Download Telegram
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኢቢሲ ቤተሰብ የእግር ኳስ ውድድር ሶስተኛ በመውጣት የነሐስ ሜዳሊያ ተበረከተለት፡፡
ስምንት ቡድኖችን አካቶ ሲካሄድ በነበረው ውድድር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በመጨረሻው ጨዋታ የገቢዎች ሚኒስቴርን በማሸነፍ ነበር የሶስተኛ ደረጃን ያገኘው፡፡
ኢቢሲ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባደረጉት ጨዋታ ኢቢሲ 1 ለ 0 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት ኢሳያስ ጂራና ሌሎች የክብር እንግዶች በተገኙበት የሜዳሊያና ሽልማት ስነስርአቱ ተካሂዷል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የእግር ኳስ ቡድን አባላትም በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተካሄደው የሽልማት ስነስርአት ላይ ተገኝተው ሜዳሊያቸውን ተረክበዋል፡፡
አዲሱን የኢቢሲ ዋና መስሪያ ቤት ምርቃትን ምክንያት በማድረግና በሰራተኞች መካከል መቀራረብን ብሎም ወንድማማችነትን ማጎልበት አላማ ያደረገው የእግር ኳስ ውድድር በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡
👍4424👏3
ሕልሙን እየኖረ ያለው ወጣት
ገና በለጋ እድሜው ወደ እንግሊዝ አገር ለትምህርት እንደተሰደደ ይናገራል፡፡ ከአገር ሲወጣ ትምህርቱን እየተከታተለ ለመነሻ የሚሆነውን ገንዘብ አጠራቅሞ መመለስ እንደሚገባው አምኖ ነው፡፡ ታዲያ ለቃሉ ታማኝ የሆነው የዛሬው ባለታሪካችን ዘካርያስ ዳኜ ብዙዎች ለመሰደድ የሚመኙበትን አገር ጥሎ ወደ እናት አገሩ ተመለሰ፡፡

"ብዙዎች ወደ አገር መመለሴን እንደ እብደት ቆጥረውበኛል፡፡" ይላል ዘካርያስ፡፡ እንግሊዝን ያህል የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤት እና የሰለጠነ አገር ትቶ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ከብዙዎች ሐሳብ የታቀረነ ነበርና ከዚህም ከዚያም ይደርስበት የነበረው ጫና ቀላል እንዳልነበረ የሚያስረዳው ዘካርያስ እኔ የሄደበትን ዓላማ ካሳካ ወደ አገሩ ተመልሶ ሥራውን መሥራት እንዳለበት በመወሰን ወደ አገሩ ተመለሰ፡፡

ዘካርያስ ወደ አገሩ ከተመለሰ በኋላ በ2002 ዓ.ም የመጀመሪያውን የኅትመት ቤት ሐዋሳ በመክፈት መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡ ሆኖም የኅትመት ቤቱ አዲስ እንደመሆኑ መጠን ሥራ ማግኘት ቀላል እንዳልነበረ ይናገራል፡፡ ዘካርያስ የማተሚያ ቤቱን ብቃት ለማሳየት ለሌላ ማተሚያ ቤት የተሰጠ ትዕዛዝ ከፍሎ በመውሰድ ጭምር በትዕዛዙ መሰረት በጥራት ሰርቶ በማስረከብ ማተሚያ ቤቱ ተወዳዳሪ ማተሚያ ቤት እንደሆነ ለማሳመን የሄደበትን ርቀት የማይረሳው ትዝታ መሆኑን አጫውቶናል፡፡

ዳኜ የሐዋሳ ዲስትሪክት የሊዝ ፋይናንስ ተበዳሪ ነው፡፡ በማኑፋክቸሪንግ ሲስተምስ ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ ይዟል፡፡ በ2002 ዓ.ም ወደ ንግዱ ዓለም እንደተቀላቀለ የሚናገረው ዘካርያስ በዙሪያው ካለው ችግር ተነሥቶ ለእሱ መፍትሄ ለመስጠት የሚያደርገው ትግል ዛሬ ለደረሰበት ደረጃ መሠረት እንደሆነው ይናገራል፡፡

ዘካርያስ ዛሬ ላይ እውን ያደረገው የሶፍት ማምረቻ ፋብሪካ መነሻ ከኅትመት ቤቱ የሚወጣው የወረቀት ቁርጥራጭ ነው፡፡ እለት እለት ከህትመት ቤቱ የሚወጣው የወረቀት ቁርጥራጭ ብዛት መላ እንደሚያስፈልገው ያውጠነጥን የነበረው ዘካርያስ ወረቀቶቹ ድጋሚ ለሥራ የሚውሉበት ሁኔታ ሲያጠና ፐልፕ ምርት ማምረት እንደሚቻል ደረሰበት፡፡ ሳያመነታ ሐሳቡን በወረቀተ አሰፈረው፡፡ ህልሙን እውን ማድረግ ይችል ዘንድ ያጋጠመውን የፋይናንስ ችግር እንዴት መቅረፍ እንደሚችል ሲያማክር ልማት ባንክ ሁነኛ መላ መሆኑን ሹክ አሉት፡፡

ሁለት ልብ ሆኖ ወደ ባንኩ እንዳቀና ዘካርያስ ይናገራል፡፡ "በብድር ሥርዓት ውስጥ አልፌ ስለማላውቅ ይሆናል አይሆንም የሚለው ብዙ እርግጠኛ አልነበርኩም" የሚለው ዘካርያስ ልማት ባንክ ከጠበቀው ባነሰ ጊዜ ለሥራ የሚያስፈልገውን ማሽን በስድስት ወራት ውስጥ በማስረከብ አስደመመው፡፡ ልማት ባንክ 280 ሺህ ዶላር የሚሆን ማሽን በማቅረብ ከወረቀት ቁርጥራጮች ፐልፕ እያመረተ የገበታ ሶፍት፣ የሆስፒታል፣ የመጸዳጃ ቤት፣ እና መሰል የሶፍት ወረቀቶች ለገበያ በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡

ዛሬ የዘካርያስ ፋብሪካ ከኅትመት ቤት በሚወጣ የወቀረት ተረፈ ምርት አንድም ወረቀቱ ሲወገድ የሚፈጠረውን የአየር ብክለት በማስወገድ በሌላ መልኩ ደግሞ አላስፈላጊ ተብሎ የሚወገዱ ወረቀቶችን መልሶ ጥቅም ላይ በማዋል 70 በመቶ በአገር ውስጥ ግብዓት፣ 30 በመቶ ከውጭ በሚገባ ጥሬ እቃ ግብዓት ጥራቱን የጠበቀ የሶፍት ምርት እያመረተ ይገኛል፡፡ "ሪሳይክሊንግ አገር ይጠቅማል፡፡ በእርግጥ የሶፍት ፋብሪካዎች አሉ፤ ነገር ግን የሚሰሩት ፐልፕ ከውጭ እያስገቡ ነው፡፡ ይህ ለተጨማሪ የውጭ ምንዛሬ ይዳርጋል፡፡ የእኛ ፋብሪካ እሱን ያስቀረ ነው፡፡" የሚለው ዘካሪያስ 74 የሚሆኑ ሠራተኞቹን ቀጥሮ ያሠራል፡፡ ከሌሎች ቦታዎች ወረቀት እየሰበሰቡ የሚመጡ በርካታ የተደራጁ ወጣቶች የሥራ እድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡ የካፒታል መጠኑም 50 ሚሊዮን ብር በላይ ሆኗል፡፡

ዘካሪያስ ህልሙ ትልቅ ነው፡፡ ዘካሪያ ህልሙ በአገሩ ሠርቶ ተለውጦ መኖር ነበር፡፡ አቋሙ ለስራ ያለው ጽናት ደግሞ ህልሙን እንዲኖር እረድቶታል፡፡ በቀጣይ ለፕልፕ ምርት የሚሆን የደን ልማት ላይ ለመሰማራት እቅድ ይዟል፡፡ ጥቅጥቅ የደን ማሳ ይፈልጋል፡፡ በዚህም ወረቀት ማምረት፤ ከውጭ የሚገባውን በአገር ውስጥ በማምረት ለሌላ አገራት የሚተርፍ ነገር ይዞ ብቅ ለማለት አቅዷል፡፡ ለዚህ ደግሞ ልማት ባንክ ትክክለኛ አጋር ነው ይላል፡፡ "የኢትዮጵ ልማት ባንክ ለእኔ እናት ነው፡፡ በችግራችን ጊዜ እንክብካቤ አድርገውልናል፡፡ ክትትል ያደርጋሉ፡፡ አዳዲስ ፕሮጀክት እንድንጀምር ያበረታታሉ፡፡ ብዙ ጊዜዬን በአገሬ እንዳሳልፍ እና በስራ እንድወጠር ያደረገኝ ከልማት ባንክ መበደሬ ነው፡፡ ከዚህ በኋላም ከልማት ባንክ ጋር በአጋርነት ወደፊት ነው" ይላል ዘካርያስ፡፡ በእርግጥም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሠረቶ አገርና ሕዘቡን ማሻገር ለሚፈልግ ሁሉ የሚተማመኑበት የልማት አጋር ነው፡፡
👍63👏2916
👍10249👏18
የስራ ማስታወቂያ
መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ከታች ባለው ሊንክ በመግባት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
መልካም እድል
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ

https://jobs.dbe.com.et
👍15091👏56🤝32
Team Manager Position
👍4513
Junior Officer Positions
👍7740🤝1
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በራሱ ወጭና ከጀርመን ልማት ባንክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ የገዛቸውን 27 ትራክተሮች ለደንበኞቹ አስረከበ፡፡

ባንኩ ለሊዝ ፋይናንስ ደንበኞቹ ካስረከባቸው ትራክተሮች ውስጥ 20ዎቹ ከጀርመን ልማት ባንክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ የተገዙ ሲሆን ቀሪዎቹን 7 ትራክተሮች ደግሞ በባንኩ ሙሉ ወጭ የተገኙ ናቸው፡፡

ትራክተሮቹን ለደንበኞቹ ያስረከቡት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ፋይናንሲንግ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አስፋው አበራ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የግብርና ሜካናይዜሽንን በሀገሪቱ ለማስፋፋት እና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ማሽነሪዎቹን የተረከቡ ደንበኞች በበኩላቸው የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ከማስፋፋቱ በተጨማሪ ለወጣቶች በሚፈጥሩት የስራ ዕድል እንደሀገር የሚኖራቸውን አስተዋጾ እንደሚያሳድግላቸው ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ግብርናውን ማዘመን የሚያስችሉ የእርሻ ማሽነሪዎችን በተከታታይ ዙሮች ለደንበኞቹ ሲያስተላልፍ የቆየ መሆኑን ያስታወሱት ም/ል ፕሬዝዳንቱ ባንኩ በቀጣይም ይህንኑ ተግባሩን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
👍6020🤝2
Senior Officer Positions
👍2419