የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ለአገራችን ከሚሰጡት የላቀ ፋይዳ በመነሳት ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ የሚያስችል ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ኢንተርፕራይዞቼ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ የቴክኖሎጂ ችግሮችን በመቅረፍ እና የማሽነሪ አቅርቦት ከነድጋፉ በማዘጋጀት፣ የክህሎት ክፍተታቸውን መሙላት የሚያስችል ስልጠና በመስጠት እና በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማገዝ በኩል ተጨባጭ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡
በአራተኛ ዙር የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ላይ ስራ ፈላጊው ወደስራ ሊገባ የሚችልበትን ቀላል እና አዋጭ መላ በማቅረብ የብዙዎቻችሁን ቀልብ የያዘው አባ መላ በስልጠና ወቅት ያቀረባቸውን የስራ አማራጮች በድጋሚ እንድናጋራችሁ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቻችን ላይ ጠይቃችኋል፡፡ በመሆኑም በአባ መላ የቀረቡ የስራ መላዎችን ቀላልና ተነባቢ በሆነ መልኩ እንዲህ አጋርተናል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
በአራተኛ ዙር የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስልጠና ላይ ስራ ፈላጊው ወደስራ ሊገባ የሚችልበትን ቀላል እና አዋጭ መላ በማቅረብ የብዙዎቻችሁን ቀልብ የያዘው አባ መላ በስልጠና ወቅት ያቀረባቸውን የስራ አማራጮች በድጋሚ እንድናጋራችሁ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቻችን ላይ ጠይቃችኋል፡፡ በመሆኑም በአባ መላ የቀረቡ የስራ መላዎችን ቀላልና ተነባቢ በሆነ መልኩ እንዲህ አጋርተናል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍53❤13👏5🤝4
የግብርና ሜካናይዜሽን የምርታማነት መሰረት
በ ዜማ ያሬድ
ለውጥ በባህሪው ሂደት ነው፡፡ የራሱን ጊዜና ስልት ይፈልጋል፡፡ ዛሬ ላይ የአለማችንን ኢኮኖሚ የሚዘውሩት አገራት መሰረታቸው ግብርና ሲሆን፣ በሂደት ስልታቸውን እየቀሩ ግብርናቸውን ከዘመኑ ጋር እያዘመኑ ወደፊት መስፈንጠር የቻሉ ናቸው፡፡
የግብርና ሜካናይዜሽን ላይ የተፃፉ ጽሁፎች እንደሚያመላክቱት የግብርና ሜካናይዜሽን በአገራት የለውጥ ሂደት ውስጥ የጎላ ድርሻ ያለው መሆኑን ነው፡፡ የግብርና ሜካናይዜሽን ቀላል የሆነ፣ ነገር ግን ምርታማነትን ሊያመጡ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ግብርናን የማዘመን ሂደት ነው፡፡
ግብርና ለአብዛኛው የዓለማችን ክፍል የኑሮ መሰረት ሲሆን፣ እንደ አገር ደግሞ ለአጠቃላይ እድገት ከፍተኛውን አስተወጽዖ የሚያበረክት ነው፡፡ በዓለማችን እያደገ የመጣውን የህዝብ ቁጥር መመገብ የሚችል የግብርና ስርዓት አስፈላጊ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የግብርና ሜካናይዜሽን ያለውን የምግብ ፍላጎት ማሟላት የሚችል ምርት ለማምረት የሚያግዝ ስልት ነው፡፡
በአገራችንም ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር የምግብ ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው የግብርና ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት እና ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ የግብርና ሜካናይዜሽን የአርሶ አደሩን ህይወት የሚቀይር፣ የግብርና ምርታማነትን የሚያሳድግ እና በአጠቃላይ ግብርና በአገር ኢኮኖሚ ላይ ያለው አሳተዋጽዖ እንዲያድግ የሚያደርግ ነው፡፡
በኢትዮጵያ የግብርና ሜካናይዜሽን እድገት ዝቅተኛ ሲሆን፣ ከአንድ በመቶ በታች የሚሆነው የግብርና መሬት ብቻ በትራክተር እንደሚታረስ ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የግብርና ማሽነሪዎችን በመጠቀም ግብርናን የማዘመን ሂደት እየተፋጠን ይገኛል፡፡ በአገራችን በገበሬው ጉልበት ብቻ ይሸፈን የነበረው የእርሻ ማሳ አሁን ላይ ወደአገራችን በስፋት እየገቡ ባሉ የአጭዶ መውቂያ እና ማረሻ ማሽኖች እየተተካ የግብርና ምርታማነትም እየጨመረ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክም በግብርና ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ የሊዝ ፋይናንስ ደንበኞቹ የአጭዶ መውቂያ እና ማረሻ ማሽኖችን በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡ ግብርናን ማዘመን የገበሬውን ጉልበት በመቆጠብ በሌሎች ተያያዥ የስራ መስኮች ላይ በመሰማራት ገቢውን እና የኑሮ ሁኔታውን እንዲያሻሽል ሰፊ እድል የሚፈጥር ነው፡፡
በአገራችን የግብርና ልማት ብክነትን የሚቀንሱ እና ምርታማነትን የሚጨምሩ ዘመኑ ያፈራቸውን የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የግብርና ስራን አድካሚ ባለሆነ መንገድ የመስራት ልምምድ ገና መሆኑ ይታመናል፡፡ ይሁንና ከ80 በመቶ በላይ አርሶ አደር ባለበት አገር ከራስ ፍጆታ አልፎ ለገበያ መትረፍ የሚችል ምርት ለማምረት ግብርናን ማዘመን ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑ የማይታበይ ሃቅ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ግብርና ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 33 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን፣ የአገራችን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከ70 በመቶ በላይ ምንጩ ግብርና እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ በተመሳሳይ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑ የሀገራችን ዜጎች መተዳደሪያቸው ግብርና እና ከግብርና ጋር ተያያዥ የሆኑ ዘርፎች ናቸው፡፡
በአገራችን እየተስፋፋ የመጣ የግብርና ሜካናይዜሽን በተለይ የስንዴ ምርታማነትን እየጨመረ መሆኑን በመንግስት በኩል ሲገለጽ ይደመጣል፡፡ በመሆኑም ከአገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለዓለም ገበያ መቅረብ የሚችል የሰብል ምርታማነትን ለማምጣት የግብርና ሜካናይዜሽንን ማስፋፋት ያስፈልጋል፡፡
ለግብርና ዘርፍ በቂ ሃብት በመመደብ ግብርናን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከዚህ አኳያ እየሰራቸው ያሉ ተግባራት የሚበረታቱና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ግብርናን ፋይናንስ በማድረግ በኩል የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የሚያነቃ ተግባር ነው የሚል እይታ አለኝ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአዲሱ ሪፎርምና የቢዝነስ ሞዴል ራሱን እንደገና ካደራጀና ወደስራ ከገባ በኋላ የተለያዩ የፋይናስ ምንጮችን በማሰባበስ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የእርሻ ማሽኖችን እያቀረበ መሆኑን በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ሲገለጽ ሰምተናል፡፡ 303 ዋና ዋና የግብርና ማሽነሪዎች ለደንበኞች አቅርቧል፡፡ አሁንም በግዥ ሂደት ላይ ካሉት በተጨማሪ ከደንበኞች እየቀረበ ያለውን ፍላጎት መመለስ የሚያስችል ፋይናንስ ለማሰባሰብ ባንኩ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በአንድ ወቅት ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ተደምጧል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትም የግብርና ሜካናይዜሽንን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ግብርናን እንደግብዓት የሚጠቀሙ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፎችን የማስፋፋት ስራም በስፋት እየተሰራ መሆኑ በተለያየ አጋጣሚ ሲጠቀስ ይሰማል፡፡
ከ120 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ ከአጠቃላይ ሕዝቧ 76 ሚሊዮን የሚሆነው እድሜው ከ29 ዓመት በታች እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይህ ቁጥር ትልቅ የአገር አቅም እንደሚሆንም ይታመናል፡፡ በመሆኑም ለአንድ አገር እድገት ለውጥ መሰረት የሆነው አምራች የሰው ሃይል ለግብርና ምቹ የሆነ መሬት በአገራችን በበቂ ሁኔታ ያለ መሆኑ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መንግስት፣ ባለድርሻ አካላት እና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት በቅንጅት ሆነው የግብርና ዘርፍን ለውጥ ለማፋጠን መስራት እንደሚገባቸው የሚያመላክት ነው፡፡
በአጠቃላይ ያለንን የሰው ሃይልና የመሬት ሃብት እንደ መልካም እድል ተጠቅሞ አገራችንን ከጥገኝነት የሚያላቅቅ፤ የህዝባችንን የምግብ ዋስትናውን ማረጋገጥ የሚችልበት ሁኔት ለመፍጠር መትጋት ያስፈልጋል፡፡ ጉልበት፣ መሬት፣ ፋይናንስና ቴክኖሎጂ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መሰረቶች በመሆናቸው ትኩረታችን እነዚህ መሰረታዊ ጉዳዮችን አቀናጅቶ ተግባር ላይ በማዋል ለውጥ ማምጣት ሊሆን ይገባል፡፡
በ ዜማ ያሬድ
ለውጥ በባህሪው ሂደት ነው፡፡ የራሱን ጊዜና ስልት ይፈልጋል፡፡ ዛሬ ላይ የአለማችንን ኢኮኖሚ የሚዘውሩት አገራት መሰረታቸው ግብርና ሲሆን፣ በሂደት ስልታቸውን እየቀሩ ግብርናቸውን ከዘመኑ ጋር እያዘመኑ ወደፊት መስፈንጠር የቻሉ ናቸው፡፡
የግብርና ሜካናይዜሽን ላይ የተፃፉ ጽሁፎች እንደሚያመላክቱት የግብርና ሜካናይዜሽን በአገራት የለውጥ ሂደት ውስጥ የጎላ ድርሻ ያለው መሆኑን ነው፡፡ የግብርና ሜካናይዜሽን ቀላል የሆነ፣ ነገር ግን ምርታማነትን ሊያመጡ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ግብርናን የማዘመን ሂደት ነው፡፡
ግብርና ለአብዛኛው የዓለማችን ክፍል የኑሮ መሰረት ሲሆን፣ እንደ አገር ደግሞ ለአጠቃላይ እድገት ከፍተኛውን አስተወጽዖ የሚያበረክት ነው፡፡ በዓለማችን እያደገ የመጣውን የህዝብ ቁጥር መመገብ የሚችል የግብርና ስርዓት አስፈላጊ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የግብርና ሜካናይዜሽን ያለውን የምግብ ፍላጎት ማሟላት የሚችል ምርት ለማምረት የሚያግዝ ስልት ነው፡፡
በአገራችንም ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር የምግብ ፍላጎት ማሟላት የሚቻለው የግብርና ሜካናይዜሽንን በማስፋፋት እና ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ የግብርና ሜካናይዜሽን የአርሶ አደሩን ህይወት የሚቀይር፣ የግብርና ምርታማነትን የሚያሳድግ እና በአጠቃላይ ግብርና በአገር ኢኮኖሚ ላይ ያለው አሳተዋጽዖ እንዲያድግ የሚያደርግ ነው፡፡
በኢትዮጵያ የግብርና ሜካናይዜሽን እድገት ዝቅተኛ ሲሆን፣ ከአንድ በመቶ በታች የሚሆነው የግብርና መሬት ብቻ በትራክተር እንደሚታረስ ይነገራል፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የግብርና ማሽነሪዎችን በመጠቀም ግብርናን የማዘመን ሂደት እየተፋጠን ይገኛል፡፡ በአገራችን በገበሬው ጉልበት ብቻ ይሸፈን የነበረው የእርሻ ማሳ አሁን ላይ ወደአገራችን በስፋት እየገቡ ባሉ የአጭዶ መውቂያ እና ማረሻ ማሽኖች እየተተካ የግብርና ምርታማነትም እየጨመረ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክም በግብርና ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ የሊዝ ፋይናንስ ደንበኞቹ የአጭዶ መውቂያ እና ማረሻ ማሽኖችን በማቅረብ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡ ግብርናን ማዘመን የገበሬውን ጉልበት በመቆጠብ በሌሎች ተያያዥ የስራ መስኮች ላይ በመሰማራት ገቢውን እና የኑሮ ሁኔታውን እንዲያሻሽል ሰፊ እድል የሚፈጥር ነው፡፡
በአገራችን የግብርና ልማት ብክነትን የሚቀንሱ እና ምርታማነትን የሚጨምሩ ዘመኑ ያፈራቸውን የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅሞ የግብርና ስራን አድካሚ ባለሆነ መንገድ የመስራት ልምምድ ገና መሆኑ ይታመናል፡፡ ይሁንና ከ80 በመቶ በላይ አርሶ አደር ባለበት አገር ከራስ ፍጆታ አልፎ ለገበያ መትረፍ የሚችል ምርት ለማምረት ግብርናን ማዘመን ያለው ፋይዳ የላቀ መሆኑ የማይታበይ ሃቅ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ግብርና ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 33 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን፣ የአገራችን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከ70 በመቶ በላይ ምንጩ ግብርና እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ በተመሳሳይ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑ የሀገራችን ዜጎች መተዳደሪያቸው ግብርና እና ከግብርና ጋር ተያያዥ የሆኑ ዘርፎች ናቸው፡፡
በአገራችን እየተስፋፋ የመጣ የግብርና ሜካናይዜሽን በተለይ የስንዴ ምርታማነትን እየጨመረ መሆኑን በመንግስት በኩል ሲገለጽ ይደመጣል፡፡ በመሆኑም ከአገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ለዓለም ገበያ መቅረብ የሚችል የሰብል ምርታማነትን ለማምጣት የግብርና ሜካናይዜሽንን ማስፋፋት ያስፈልጋል፡፡
ለግብርና ዘርፍ በቂ ሃብት በመመደብ ግብርናን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ መቀጠል ይገባዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከዚህ አኳያ እየሰራቸው ያሉ ተግባራት የሚበረታቱና ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ግብርናን ፋይናንስ በማድረግ በኩል የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ የሚያነቃ ተግባር ነው የሚል እይታ አለኝ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በአዲሱ ሪፎርምና የቢዝነስ ሞዴል ራሱን እንደገና ካደራጀና ወደስራ ከገባ በኋላ የተለያዩ የፋይናስ ምንጮችን በማሰባበስ ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የእርሻ ማሽኖችን እያቀረበ መሆኑን በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ሲገለጽ ሰምተናል፡፡ 303 ዋና ዋና የግብርና ማሽነሪዎች ለደንበኞች አቅርቧል፡፡ አሁንም በግዥ ሂደት ላይ ካሉት በተጨማሪ ከደንበኞች እየቀረበ ያለውን ፍላጎት መመለስ የሚያስችል ፋይናንስ ለማሰባሰብ ባንኩ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዮሐንስ አያሌው በአንድ ወቅት ባደረጉት ቃለምልልስ ሲናገሩ ተደምጧል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስትም የግብርና ሜካናይዜሽንን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየሰራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ግብርናን እንደግብዓት የሚጠቀሙ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ዘርፎችን የማስፋፋት ስራም በስፋት እየተሰራ መሆኑ በተለያየ አጋጣሚ ሲጠቀስ ይሰማል፡፡
ከ120 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ ከአጠቃላይ ሕዝቧ 76 ሚሊዮን የሚሆነው እድሜው ከ29 ዓመት በታች እንደሆነ ይነገራል፡፡ ይህ ቁጥር ትልቅ የአገር አቅም እንደሚሆንም ይታመናል፡፡ በመሆኑም ለአንድ አገር እድገት ለውጥ መሰረት የሆነው አምራች የሰው ሃይል ለግብርና ምቹ የሆነ መሬት በአገራችን በበቂ ሁኔታ ያለ መሆኑ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም መንግስት፣ ባለድርሻ አካላት እና ሌሎች የፋይናንስ ተቋማት በቅንጅት ሆነው የግብርና ዘርፍን ለውጥ ለማፋጠን መስራት እንደሚገባቸው የሚያመላክት ነው፡፡
በአጠቃላይ ያለንን የሰው ሃይልና የመሬት ሃብት እንደ መልካም እድል ተጠቅሞ አገራችንን ከጥገኝነት የሚያላቅቅ፤ የህዝባችንን የምግብ ዋስትናውን ማረጋገጥ የሚችልበት ሁኔት ለመፍጠር መትጋት ያስፈልጋል፡፡ ጉልበት፣ መሬት፣ ፋይናንስና ቴክኖሎጂ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መሰረቶች በመሆናቸው ትኩረታችን እነዚህ መሰረታዊ ጉዳዮችን አቀናጅቶ ተግባር ላይ በማዋል ለውጥ ማምጣት ሊሆን ይገባል፡፡
👍60🤝5❤4👏1
ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ብድር ወስደው በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች ሃብት መፍጠር የቻሉ ኢንቨስተሮች ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም በጥያቄያችሁ መሰረት የስኬታማ ሰዎችን የስራና የህይወት ልምድ አጋርተናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡
ከአንድ ብርቱ….
በወረታ ከተማ በአነስተኛ የቢዝነስ መስክ ላይ በመሰማራት በህይወታቸው ያጋጠማቸውን ጉድለት ለመሙላት እረፍት የለሽ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ወጣቶች ናቸው፡፡ የተለመደ ስራቸውን በመከወን ላይ ሳሉ በ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የጎንደር ዲስትሪክት ወረታ ቅርንጫፍ በከተማዋ ለሚገኙ ነዋሪዎች አንድ ዜና ይዞ ብቅ አለ፡፡
በተለያየ የስራ መስክ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ነገር ግን በፋይናንስ እጥረት ስራቸውን ማሳደግ ያልቻሉ ተሰባስበው ለስራ መነሻ የሚሆናቸውን ገንዘብ በማፈላለግ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንስ የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚጋብዝ መልካም ዜናን ሰሙ፡፡
ይህን የሰሙት አምስቱ ወጣቶች በጋራ ሆነው እንደ አንድ ለመስራትና ከተሰማሩበት የስራ መስክ ከፍ ወዳለው የቢዝነስ አማራጭ ለመሰማራት በማቀድ ወደ ልማት ባንክ አመሩ፡፡ ደርበውና መንግስቱ የድንጋይና ጠጠር ማምረት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በዚህ መንገድ ተመሰረተ፡፡ ከእኛ የሚገባውን ሁሉ አሟልተን በመሄዳችን የኢትዮጵያ ልማት ባንክን አገልግሎት መጠቀም ችለናል ይላል የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ደርበው ሙላት፡፡
ደርበውና መንግስቱ የድንጋይና ጠጠር ማምረት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አባላት አምስት ሆነው የየራሳቸውን ስራ በመተው በጋራ ሆነው የትልቅ ድርጅት ባለቤት የመሆን ፍላጎታቸውን ልማት ባንክ አሟልቶላቸው ዛሬ በወረታ ከተማ የትልቅ ጠጠር ማምረቻ ባለቤት መሆን ችለዋል፡፡
ባንኩ በሊዝ ፋይናንስ የብድር አገልግሎት የጠጠር ማምራቻ ማሽኑን አቅርቦላቸዋል፡፡ እነዚህ ባለራዕዮች የተሻለ ስራ መስራት እንችላለን በሚል የስራ መነሳሳት የገቡበት ስራ ዛሬ የግል ሕይወታቸውን ከመቀየር አልፎ ድርጅታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ የማህበሩ ሰብሳቢ ተናግሯል፡፡ ጤናማ የሆነ የብድር አመላለስ ውስጥ እንደሆነ የተናገረው ሰብሳቢው የብድር አመላለሳችን ወቅታዊ ችግር ቢገጥም እንኳን የባንኩን ብድር ከመመለስ ወደኋላ አንልም ሲል አክሏል፡፡
አንድ ሰው ብቻውን ማድረግ ወይም ማሳካት የማይችለውን ሰብሰብ ብሎ እንደኛ ማድረግ ይችላል፡፡ እኛ በግላችን ስራ የነበረን ሰዎች ብንሆንም እያንዳንዳችን በተናጥል ማድረግ የማንችለውን ሰብሰብ ብለን አቅም በመፍጠር ተጠቃሚ መሆን ችለናል ብሏል የማህበሩ ሰብሳቢ፡፡
የነበረባችውን የፋይናንስ ችግር በመፍታት ህብረታቸውን ወደ ውጤት ከቀየረው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በሌላ ስኬት ለመምጣት ዝግጅታችንን አጠናቀናል ይላሉ፡፡
በቀጣይም እንደ እነ ደርበውና ጓደኞቹ ሁሉ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስራ ጀምረው ስራቸውን ማሳደግ ለሚሹ፣ ወደ ቢዝነስ ለመግባት እቅድ ያላቸውን ሁሉ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስተማማኝ አጋር በመሆን የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
ከአንድ ብርቱ….
በወረታ ከተማ በአነስተኛ የቢዝነስ መስክ ላይ በመሰማራት በህይወታቸው ያጋጠማቸውን ጉድለት ለመሙላት እረፍት የለሽ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ወጣቶች ናቸው፡፡ የተለመደ ስራቸውን በመከወን ላይ ሳሉ በ2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የጎንደር ዲስትሪክት ወረታ ቅርንጫፍ በከተማዋ ለሚገኙ ነዋሪዎች አንድ ዜና ይዞ ብቅ አለ፡፡
በተለያየ የስራ መስክ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ነገር ግን በፋይናንስ እጥረት ስራቸውን ማሳደግ ያልቻሉ ተሰባስበው ለስራ መነሻ የሚሆናቸውን ገንዘብ በማፈላለግ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሊዝ ፋይናንስ የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚጋብዝ መልካም ዜናን ሰሙ፡፡
ይህን የሰሙት አምስቱ ወጣቶች በጋራ ሆነው እንደ አንድ ለመስራትና ከተሰማሩበት የስራ መስክ ከፍ ወዳለው የቢዝነስ አማራጭ ለመሰማራት በማቀድ ወደ ልማት ባንክ አመሩ፡፡ ደርበውና መንግስቱ የድንጋይና ጠጠር ማምረት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በዚህ መንገድ ተመሰረተ፡፡ ከእኛ የሚገባውን ሁሉ አሟልተን በመሄዳችን የኢትዮጵያ ልማት ባንክን አገልግሎት መጠቀም ችለናል ይላል የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ደርበው ሙላት፡፡
ደርበውና መንግስቱ የድንጋይና ጠጠር ማምረት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር አባላት አምስት ሆነው የየራሳቸውን ስራ በመተው በጋራ ሆነው የትልቅ ድርጅት ባለቤት የመሆን ፍላጎታቸውን ልማት ባንክ አሟልቶላቸው ዛሬ በወረታ ከተማ የትልቅ ጠጠር ማምረቻ ባለቤት መሆን ችለዋል፡፡
ባንኩ በሊዝ ፋይናንስ የብድር አገልግሎት የጠጠር ማምራቻ ማሽኑን አቅርቦላቸዋል፡፡ እነዚህ ባለራዕዮች የተሻለ ስራ መስራት እንችላለን በሚል የስራ መነሳሳት የገቡበት ስራ ዛሬ የግል ሕይወታቸውን ከመቀየር አልፎ ድርጅታቸውን ማሳደግ እንደቻሉ የማህበሩ ሰብሳቢ ተናግሯል፡፡ ጤናማ የሆነ የብድር አመላለስ ውስጥ እንደሆነ የተናገረው ሰብሳቢው የብድር አመላለሳችን ወቅታዊ ችግር ቢገጥም እንኳን የባንኩን ብድር ከመመለስ ወደኋላ አንልም ሲል አክሏል፡፡
አንድ ሰው ብቻውን ማድረግ ወይም ማሳካት የማይችለውን ሰብሰብ ብሎ እንደኛ ማድረግ ይችላል፡፡ እኛ በግላችን ስራ የነበረን ሰዎች ብንሆንም እያንዳንዳችን በተናጥል ማድረግ የማንችለውን ሰብሰብ ብለን አቅም በመፍጠር ተጠቃሚ መሆን ችለናል ብሏል የማህበሩ ሰብሳቢ፡፡
የነበረባችውን የፋይናንስ ችግር በመፍታት ህብረታቸውን ወደ ውጤት ከቀየረው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በሌላ ስኬት ለመምጣት ዝግጅታችንን አጠናቀናል ይላሉ፡፡
በቀጣይም እንደ እነ ደርበውና ጓደኞቹ ሁሉ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ስራ ጀምረው ስራቸውን ማሳደግ ለሚሹ፣ ወደ ቢዝነስ ለመግባት እቅድ ያላቸውን ሁሉ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስተማማኝ አጋር በመሆን የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍72❤12
የጠባቧ ቤት ሰፊ በረከት
ብዙዎች የግል ሥራቸውን ለመጀመር እንቅፋት የሆነባቸው የቦታ እጦት እንደሆነ ሲናገሩ ይደመጣል፡፡ የመንቀሳቀሻ ገንዘብ አይቸግረኝም፤ ሆኖም የመሥሪያ ቦታ የለኝም የሚሉ ግለሰቦችን በተለያየ አጋጣሚ እንሰማለን፡፡ ወደምስራቅ ያገኘናቸው የቢዝነስ ሰው ‹‹የለም ለሥራ መሠረቱ ፍላጎትና እና ቁርጠኝነት ነው እሱ ካለ መላ አለ›› ይላሉ፤ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ድሬዳዋ ዲስትሪክት ሐረር ቅርንጫፍ ደንበኛ አቶ ሳሊ መሐመድ፡፡
ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሊዝ ፋይናንስ የጥልፍ እና የስፌት ማሽኖችን ተረክበው እየሠሩ ነው፡፡ 35 ካሬ በሆነች ቦታቸው 24 ሰዓት በፈረቃ ይሠራሉ ለነገ ስኬት ዛሬ ላይ የሚጣለው መሰረት ወሳኝ ነውና፡፡ አቶ ሳሊ ባላቸው ቦታ ላይ ትልቁን የቢዝነስ ትልማቸውን እስኪያሳኩ ድረስ ሌት ተቀን እየሠሩ መሠረታቸውን አስተማማኝ በሆነ ልምድና እና ካፒታል ላይ እየገነቡ ይገኛል፡፡
በ1994 ዓ.ም ከቤተሰብ ጋር ወደ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የገቡት አቶ ሳሊ የቤተሰባቸውን ሥራ ጥለው በራሳቸው ሥራ የጀመሩት በ2000 ዓ.ም እንደነሆነ ይናገራሉ፡፡ የጨርቃ ጨርቅ ሥራን ከቤተሰብ የወረሱት ሙያ ሲሆን፣ በእውቀት እና በፍላጎት እየሠሩት እንደሚገኙም አጫውተውናል፡፡
ሐረር ከተማ የስፌት ማዕከል ናት፡፡ አቶ ሳሊም የጨርቃጨርቅ ሥራቸውን ለማስፋፋት ጥናት ጨርሰው ለኢንቨስትመንት የሚሆን ቦታ ተረክበው በግንባታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡ ወደ ትልቁ የቢዝነስ ሥራቸው ከመግባታቸው በፊት ባላቸው ቦታ ላይ እዳቸውን እየከፈሉ፣ ሠራተኞቻቸውንም ቤታቸውንም እየመሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
አንድ ሰው ወደ ሥራ ከመሰማራቱ በፊት ለሥራው ያለውን ፍላጎት እና በሚሰማራበት መስክ ላይ ያለውን እውቀት ማጤን እንዳለበትም ይመክራሉ፡፡ የአቶ ሳሊ 35 ካሬ የሥራ ቦታ ላይ 12 የድርጅቱ ሠራተኞች በፈረቃ ለ24 ሰዓት ይሠሩበታል፡፡ ግለሰቡ ቱርክ በነበራቸው የጉብኝት ቆይታ በጠባብ ቤት ተሠርተው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን መመልከታቸው በትንሽ ቦታ ላይ ምርታማ መሆን እንደሚቻል ልምድ እንደቀሰሙበት አልሸሸጉም፡፡
ኢንቨስትመንት የራሱ የሆነ ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በተገኘው ቦታ ሥራን እየሠሩ ወደ ትልቅ የኢንቨስትመንት ሥራ መሸጋገር እንደሚቻል አቶ ሳሊ ምስክር ናቸው፡፡ 24 ሰዓት እረፍት በሌላት ጠባቧ ክፍል በርካታ ጥልፍ፣ የሎጎ ሥራ፣ የፖለሲ አርማዎች ተሠርቷል፡፡ የ12 ሰው ደሞዝ የሚከፈል ገቢን ከመሸፈን ባሻገር፣ እዳ እየከፈለች የአቶ ሳሊን ቤተሰብ እያስተዳደረች ትገኛለች፡፡ ለዛም ነው አቶ ሳሊ ‹‹ይህቺ ቤት ታምረኛ ናት›› የሚሉት፡፡ ለብዙ ሰዎች የሥራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት ለመጀመር በሂደት ላይ ያሉት አቶ ሳሊ ህልማቸውን እንደሚያሳኩ ጅምር እንቅስቃሴያቸው ምስክር ነው፡፡
በአቶ ሳሊ ድርጅት የሚመረቱ ትራስ ጨርቆች ከ40 በመቶ በላይ ወደ ውጭ ነው የሚላኩት፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአቶ ሳሊ የስፌትና የጥልፍ ማሽኖች በሊዝ ፋይናንስ የብድር አገልግሎት አቅርቦላቸዋል፡፡ የባንኩ ባለሙያዎች በቅርብ እየተከታተሉ የሚደግፉ፤ የሚያነቁ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ሳሊ የባንክ የብድር ሂደትን በመሰልቸት የሚያፈገፍጉ ወደባንኩ ጠጋ ብለው የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይመክራሉ፡፡
ትልልቅ ቢዝነሶች ገበያውን በመቋቋም ሳይናጉ ቀጣይ መሆን የሚችሉት መሠረታቸው ጠንካራ ሲሆን ነው፡፡ ሥራን በእውቀት እና በፍላጎት መምራት ውጤታማ ያደርጋል፡፡ አንድ ሥራ ለመሥራት ቦታ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሆኖ ሳለ ባለ ውስን ካፒታል እና ቦታ ውጤታማ ሥራ መሥራት እንደሚቻል አቶ ሳሊን ጨምሮ የብዙ ግለሰቦች ታሪክ ያስተምረናል፡፡ ሁሉንም ነገር በአንዴ ማሟላት የማይቻልበት ምክንያቶች ቢኖሩ ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ተደምረው የምንፈልገውን ውጤት ማምጣት ይቻላል፡፡
ብዙዎች የግል ሥራቸውን ለመጀመር እንቅፋት የሆነባቸው የቦታ እጦት እንደሆነ ሲናገሩ ይደመጣል፡፡ የመንቀሳቀሻ ገንዘብ አይቸግረኝም፤ ሆኖም የመሥሪያ ቦታ የለኝም የሚሉ ግለሰቦችን በተለያየ አጋጣሚ እንሰማለን፡፡ ወደምስራቅ ያገኘናቸው የቢዝነስ ሰው ‹‹የለም ለሥራ መሠረቱ ፍላጎትና እና ቁርጠኝነት ነው እሱ ካለ መላ አለ›› ይላሉ፤ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ድሬዳዋ ዲስትሪክት ሐረር ቅርንጫፍ ደንበኛ አቶ ሳሊ መሐመድ፡፡
ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ በሊዝ ፋይናንስ የጥልፍ እና የስፌት ማሽኖችን ተረክበው እየሠሩ ነው፡፡ 35 ካሬ በሆነች ቦታቸው 24 ሰዓት በፈረቃ ይሠራሉ ለነገ ስኬት ዛሬ ላይ የሚጣለው መሰረት ወሳኝ ነውና፡፡ አቶ ሳሊ ባላቸው ቦታ ላይ ትልቁን የቢዝነስ ትልማቸውን እስኪያሳኩ ድረስ ሌት ተቀን እየሠሩ መሠረታቸውን አስተማማኝ በሆነ ልምድና እና ካፒታል ላይ እየገነቡ ይገኛል፡፡
በ1994 ዓ.ም ከቤተሰብ ጋር ወደ ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ የገቡት አቶ ሳሊ የቤተሰባቸውን ሥራ ጥለው በራሳቸው ሥራ የጀመሩት በ2000 ዓ.ም እንደነሆነ ይናገራሉ፡፡ የጨርቃ ጨርቅ ሥራን ከቤተሰብ የወረሱት ሙያ ሲሆን፣ በእውቀት እና በፍላጎት እየሠሩት እንደሚገኙም አጫውተውናል፡፡
ሐረር ከተማ የስፌት ማዕከል ናት፡፡ አቶ ሳሊም የጨርቃጨርቅ ሥራቸውን ለማስፋፋት ጥናት ጨርሰው ለኢንቨስትመንት የሚሆን ቦታ ተረክበው በግንባታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡ ወደ ትልቁ የቢዝነስ ሥራቸው ከመግባታቸው በፊት ባላቸው ቦታ ላይ እዳቸውን እየከፈሉ፣ ሠራተኞቻቸውንም ቤታቸውንም እየመሩ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
አንድ ሰው ወደ ሥራ ከመሰማራቱ በፊት ለሥራው ያለውን ፍላጎት እና በሚሰማራበት መስክ ላይ ያለውን እውቀት ማጤን እንዳለበትም ይመክራሉ፡፡ የአቶ ሳሊ 35 ካሬ የሥራ ቦታ ላይ 12 የድርጅቱ ሠራተኞች በፈረቃ ለ24 ሰዓት ይሠሩበታል፡፡ ግለሰቡ ቱርክ በነበራቸው የጉብኝት ቆይታ በጠባብ ቤት ተሠርተው ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን መመልከታቸው በትንሽ ቦታ ላይ ምርታማ መሆን እንደሚቻል ልምድ እንደቀሰሙበት አልሸሸጉም፡፡
ኢንቨስትመንት የራሱ የሆነ ጊዜ የሚፈልግ በመሆኑ በተገኘው ቦታ ሥራን እየሠሩ ወደ ትልቅ የኢንቨስትመንት ሥራ መሸጋገር እንደሚቻል አቶ ሳሊ ምስክር ናቸው፡፡ 24 ሰዓት እረፍት በሌላት ጠባቧ ክፍል በርካታ ጥልፍ፣ የሎጎ ሥራ፣ የፖለሲ አርማዎች ተሠርቷል፡፡ የ12 ሰው ደሞዝ የሚከፈል ገቢን ከመሸፈን ባሻገር፣ እዳ እየከፈለች የአቶ ሳሊን ቤተሰብ እያስተዳደረች ትገኛለች፡፡ ለዛም ነው አቶ ሳሊ ‹‹ይህቺ ቤት ታምረኛ ናት›› የሚሉት፡፡ ለብዙ ሰዎች የሥራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት ለመጀመር በሂደት ላይ ያሉት አቶ ሳሊ ህልማቸውን እንደሚያሳኩ ጅምር እንቅስቃሴያቸው ምስክር ነው፡፡
በአቶ ሳሊ ድርጅት የሚመረቱ ትራስ ጨርቆች ከ40 በመቶ በላይ ወደ ውጭ ነው የሚላኩት፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአቶ ሳሊ የስፌትና የጥልፍ ማሽኖች በሊዝ ፋይናንስ የብድር አገልግሎት አቅርቦላቸዋል፡፡ የባንኩ ባለሙያዎች በቅርብ እየተከታተሉ የሚደግፉ፤ የሚያነቁ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ሳሊ የባንክ የብድር ሂደትን በመሰልቸት የሚያፈገፍጉ ወደባንኩ ጠጋ ብለው የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይመክራሉ፡፡
ትልልቅ ቢዝነሶች ገበያውን በመቋቋም ሳይናጉ ቀጣይ መሆን የሚችሉት መሠረታቸው ጠንካራ ሲሆን ነው፡፡ ሥራን በእውቀት እና በፍላጎት መምራት ውጤታማ ያደርጋል፡፡ አንድ ሥራ ለመሥራት ቦታ ወሳኝ ሚና የሚጫወት ሆኖ ሳለ ባለ ውስን ካፒታል እና ቦታ ውጤታማ ሥራ መሥራት እንደሚቻል አቶ ሳሊን ጨምሮ የብዙ ግለሰቦች ታሪክ ያስተምረናል፡፡ ሁሉንም ነገር በአንዴ ማሟላት የማይቻልበት ምክንያቶች ቢኖሩ ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ተደምረው የምንፈልገውን ውጤት ማምጣት ይቻላል፡፡
👍54❤8👏3🤝1