የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለደንበኞች የሚሰጣቸው አገልግሎቶች ባንኩ ከተቋቋመበት ዓላማ አንፃር የተቀረፁና የአገራችንን ኢኮኖሚያዊ ሽግግር የሚያፋጥኑ ናቸው። ባንካችን በሊዝ ፋይናንስ አሰራር የሚሰጠው የብድር አሰጣጥ የራሱ መንገድ ያለው መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል።
ደንበኞች አንድም የሚያቀርቡት ፕሮፖዛል አዋጭነቱን ደጋግሞ ማየት ይጠብቅባቸዋል። ባንካችን ሁሉንም የብድር ሂደቶች ካላቸው አገራዊ ፋይዳ አንፃር እየመዘነ እንደአመጣጣቸው የሚያስተናግድ መሆኑን መገንዘብ ይገባል።
ከባንካችን አገልግሎት የሚጠይቅ አካል ግዴታውን ማሟላቱን እና ጥያቄው ባንኩ ብድር ከሚሰጥባቸው ዘርፎችና ንዑስ ዘርፎች መካከል መሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ እየገለፅ የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስፈልጉ ዝርዝር መስፈርቶች አያይዘንላችኋል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
ደንበኞች አንድም የሚያቀርቡት ፕሮፖዛል አዋጭነቱን ደጋግሞ ማየት ይጠብቅባቸዋል። ባንካችን ሁሉንም የብድር ሂደቶች ካላቸው አገራዊ ፋይዳ አንፃር እየመዘነ እንደአመጣጣቸው የሚያስተናግድ መሆኑን መገንዘብ ይገባል።
ከባንካችን አገልግሎት የሚጠይቅ አካል ግዴታውን ማሟላቱን እና ጥያቄው ባንኩ ብድር ከሚሰጥባቸው ዘርፎችና ንዑስ ዘርፎች መካከል መሆናቸውን ማረጋገጥ እንደሚገባ እየገለፅ የሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስፈልጉ ዝርዝር መስፈርቶች አያይዘንላችኋል።
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍82❤28🤝3👏1
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ያካሄደውን ሪፎርም ተከትሎ ተደራሽነቱን ለማስፋት በወሰደው እርምጃ በሶማሌ ክልል ዲስትሪክት በመክፈቱ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ደንበኛ ወደ ባንኩ እንዲመጣ እያደረገ መሆኑን የባንኩ ጂግጂጋ ዲስትሪክት አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የጂግጂጋ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድወሰን ተመስገን እንዳሉት ባንኩ ዲስትሪክቱን በክልሉ መክፈቱ ቀደም ሲል የነበረውን ከፍያለ የደንበኞች ቁጥር እና የሚቀርበውን የብድር ጥያቄ በእጅጉ አሳድጎታል፡፡
ቀደም ሲል በሁለት ቅርንጫፎች ብቻ በክልሉ ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት የባንኩን ሪፎርም ተከትሎ በአሁኑ ወቅት ወደ አንድ ዲስትሪክት እና ወደ አራት ቅርንጫፎች ማሳደግ በመቻሉ ከፍተኛ የሆነ የብድር ጥያቄ እየቀረበ መሆኑን ነው ስራ አስኪያጁ አቶ ወንድወሰን የተናገሩት፡፡
ከሚቀርቡ ጥያቄዎች መካከል በአዋጭነታቸው የተለዩ 53 ኢንተርፕራይዞች መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ወንድወሰን ከነዚህም ውስጥ 17 ወደ ስራ ገብተው ማምረት የጀመሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ቀሪዎቹም በተከላ እና በግዥ ሂደት ላይ የሚገኙ መሆኑን የተናገሩት አቶ ወንድወሰን 15ቱ በመጽደቅ ሂደት ላይ የሚገኙ ናቸው ብለዋል፡፡
ለነዚህ ፕሮጄክቶች የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከ1.2 ቢሊዮን ብር ብር በላይ ፋይናንስ ማድረጉን ነው የባንኩ የጂግጂጋ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድወሰን ተመስገን የተናገሩት፡፡
እነዚህ የሊዝ ፋይናንስ ፕሮጄክቶች በሶማሌ ክልል ያለውን ከፍተኛ የገበያ ፍላጎትን ታሳቢ ያደረጉ ፤ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚያስቀሩ እና ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የሚያስገኙ ሲሆን የአካባቢውን ኢኮኖሚ ከንግድና አርብቶ አደርነት ወደ አምራችና ግብርና እንዲሰማሩ የሚያደርጉ መሆናቸውንም ነው የገለጹት፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሪፎርም ከማካሄዱ በፊት ባንኩ በሶማሌ ክልል ብዙም የማይታወቅ እንደነበር ያስታወሱት ስራ አስኪያጁ አሁን ላይ ዲስትሪክት እና አራት ቅርንጫፎችን ከፍቶ እየተንቀሳቀሰ በመሆኑ ማህበረሰቡ ደስታውን እየገለጸ እና ከባንኩ ጋር አብሮ ለመስራት ጥያቅዎችን እያቀረበ ይገኛል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የጂግጂጋ ዲስትሪክት በስሩ የጂግጂጋ ፤ ቀብሪደሃር፡ ደጋሃቡር እና ጎዴ ቅርንጫፎችን ከፍቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የጂግጂጋ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድወሰን ተመስገን እንዳሉት ባንኩ ዲስትሪክቱን በክልሉ መክፈቱ ቀደም ሲል የነበረውን ከፍያለ የደንበኞች ቁጥር እና የሚቀርበውን የብድር ጥያቄ በእጅጉ አሳድጎታል፡፡
ቀደም ሲል በሁለት ቅርንጫፎች ብቻ በክልሉ ይሰጥ የነበረውን አገልግሎት የባንኩን ሪፎርም ተከትሎ በአሁኑ ወቅት ወደ አንድ ዲስትሪክት እና ወደ አራት ቅርንጫፎች ማሳደግ በመቻሉ ከፍተኛ የሆነ የብድር ጥያቄ እየቀረበ መሆኑን ነው ስራ አስኪያጁ አቶ ወንድወሰን የተናገሩት፡፡
ከሚቀርቡ ጥያቄዎች መካከል በአዋጭነታቸው የተለዩ 53 ኢንተርፕራይዞች መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ወንድወሰን ከነዚህም ውስጥ 17 ወደ ስራ ገብተው ማምረት የጀመሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ቀሪዎቹም በተከላ እና በግዥ ሂደት ላይ የሚገኙ መሆኑን የተናገሩት አቶ ወንድወሰን 15ቱ በመጽደቅ ሂደት ላይ የሚገኙ ናቸው ብለዋል፡፡
ለነዚህ ፕሮጄክቶች የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከ1.2 ቢሊዮን ብር ብር በላይ ፋይናንስ ማድረጉን ነው የባንኩ የጂግጂጋ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ወንድወሰን ተመስገን የተናገሩት፡፡
እነዚህ የሊዝ ፋይናንስ ፕሮጄክቶች በሶማሌ ክልል ያለውን ከፍተኛ የገበያ ፍላጎትን ታሳቢ ያደረጉ ፤ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን የሚያስቀሩ እና ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል የሚያስገኙ ሲሆን የአካባቢውን ኢኮኖሚ ከንግድና አርብቶ አደርነት ወደ አምራችና ግብርና እንዲሰማሩ የሚያደርጉ መሆናቸውንም ነው የገለጹት፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሪፎርም ከማካሄዱ በፊት ባንኩ በሶማሌ ክልል ብዙም የማይታወቅ እንደነበር ያስታወሱት ስራ አስኪያጁ አሁን ላይ ዲስትሪክት እና አራት ቅርንጫፎችን ከፍቶ እየተንቀሳቀሰ በመሆኑ ማህበረሰቡ ደስታውን እየገለጸ እና ከባንኩ ጋር አብሮ ለመስራት ጥያቅዎችን እያቀረበ ይገኛል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ የጂግጂጋ ዲስትሪክት በስሩ የጂግጂጋ ፤ ቀብሪደሃር፡ ደጋሃቡር እና ጎዴ ቅርንጫፎችን ከፍቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
👍47👏2❤1🤝1
የግብርና ሚኒስቴር የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ የህብረተሰቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል ብሎም የግብርናውን ዘርፍ ለሀገራዊ ኢኮኖሚው ዕድገት የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ከፍ ለማድረግ ከክልሎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
የግብርና ግብዓት አቅርቦትና ምርት ግብይት ኤክስፖ 2015 በሚል ርዕስ ኤግዚቢሽንና ባዛር እንዲሁም ንዑስ ዘርፉን የሚያመለክቱ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚቀርቡበት ሲምፖዚየም በአዲስ አበባ ከሰሞኑ ተከፍቷል፡፡
ኤክስፖው ከመጋቢት 26 እስከ ሚያዝያ 5 የሚቆይ ሲሆን የሰብልና የእንስሳት ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችንና የተመረጡ የግብርና ምርቶች ለዕይታ ቀርበውበታል፡፡
ምርቶችን ለገበያ ለማስተዋወቅ እና ደንበኞችንና አምራቾችን ለማገናኜት መልካም አጋጣሚን እንደፈጠረም ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡
አንዱ-በኤክስፖው ላይ ከሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች የተለዩ ዋና ዋና ግብዓት አምራቾች፣ በአቅራቢነት የተሰማሩ ድርጅቶች፣ የሕብረት ስራ ማህበራት፣ የግብርና ምርት አምራቾች እና ፣ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
የግብርናው ዘርፍ እንዲያድግ በትኩረት የሚደግፈው የኢትዮጵያ ልማት ባንክም የግብርና ሚኒስቴር ያዘጋጀውን ኤክስፖ ስፖንሰር በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል፡፡
የግብርና ግብዓት አቅርቦትና ምርት ግብይት ኤክስፖ 2015 በሚል ርዕስ ኤግዚቢሽንና ባዛር እንዲሁም ንዑስ ዘርፉን የሚያመለክቱ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚቀርቡበት ሲምፖዚየም በአዲስ አበባ ከሰሞኑ ተከፍቷል፡፡
ኤክስፖው ከመጋቢት 26 እስከ ሚያዝያ 5 የሚቆይ ሲሆን የሰብልና የእንስሳት ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችንና የተመረጡ የግብርና ምርቶች ለዕይታ ቀርበውበታል፡፡
ምርቶችን ለገበያ ለማስተዋወቅ እና ደንበኞችንና አምራቾችን ለማገናኜት መልካም አጋጣሚን እንደፈጠረም ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡
አንዱ-በኤክስፖው ላይ ከሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች የተለዩ ዋና ዋና ግብዓት አምራቾች፣ በአቅራቢነት የተሰማሩ ድርጅቶች፣ የሕብረት ስራ ማህበራት፣ የግብርና ምርት አምራቾች እና ፣ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
የግብርናው ዘርፍ እንዲያድግ በትኩረት የሚደግፈው የኢትዮጵያ ልማት ባንክም የግብርና ሚኒስቴር ያዘጋጀውን ኤክስፖ ስፖንሰር በማድረግ አጋርነቱን አሳይቷል፡፡
👍64❤14👏2
በአክሲዮን ማኅበር የመሥራት ምቹ ሁኔታ
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እያንዳንዱ ሠልጣኝ በሥልጠናው ከሚያገኘው የቢዝነሥ ሥራውን ለመሥራት ክህሎት ከማግኘት በተጨማሪ ለሥራ ማስኬጃ (መዋጮ) የሚጠየቁትን 20 በመቶ ካፒታል ለሌላቸውና ወደ ቢዝነስ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ አማራጭ አዘጋጅቷል፡፡ በመሆኑም ባለፉት ሦስት ዙሮች ሥልጠና ወስደው ብቁ ሆነው የምስክር ወረቀት የተቀበሉ በአክሲዮን ማኅበር ወደ ቢዝነስ እንዲገቡ በባንካችን ተፈቅዷል፡፡ ባንኩ በአክሲዮን አደራጅቶ ፋይናንስ በማድረግ ለበርካቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ልማትን ለማፋጠን እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ ለዚህም እያንዳንዱ ሼር 1000 ብር ዋጋ ያለው ሆኖ ዝቅተኛው የሚሸጥ የሼር መጠን አምስት ወይም 5000 ብር ይሆናል፡፡ በአክሲዮን ለመሥራት ሠልጣኞች ራሳቸውንና ሌሎች አብረዋቸው ሊሠሩ የተዘጋጁ የአክሲዮን አባላቶቻቸውን በማስመዝገብ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ተዘርግቷል፡፡
በሚፈጠረው የአክሲዮን ማኅበር ውስጥ ዋነኛ (አስተባባሪ) የሚሆኑት ሥልጠና ወስደው ምስክር ወረቀት ያገኙ አባላቱ ቁጥር አንድ ወይም ከዚያ በላይ መሆን የሚገባቸው ሲሆን፣ የሚያስመዘግቧቸው ሌሎች አባላት ግን ሥልጠናውን ያልወሰዱ ከሆነ በቀጣይ በሚኖሩ የሥልጠና ዙሮች መሠልጠን ይገባቸዋል፡፡ በአክሲዮን ማኅበር ለመሥራት የሚመዘገቡ የአክሲዮን ባለቤቶች አብረው ለመሥራት ተስማምተው የቆዩ፣ ሕጋዊ ለመሆን በሂደት ላይ ያሉና በጋራ የሚጠሩበት ስም ካላቸው ማስመዝገብ ይችላሉ፡፡ በአዲስ መልክ የሚቋቋም ከሆነ ግን በሚመዘገቡበት ቀን የባንኩ ቅርንጫፍ ለጊዜው በሚሰጣቸው መለያ ስም ወይም ቁጥር ይመዘገባሉ፡፡ ተመዝጋቢዎች ኢንቨስት ማድረግ የሚፈልጉበትን ቦታና የኢኮኖሚ ዘርፍ እንዲሁም ንዑስ ዘርፍ መምረጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በግላቸው ለመሥራት አቅሙ ያላቸውና የተዘጋጁ ሠልጣኞች በዚህ መንገድ ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እያንዳንዱ ሠልጣኝ በሥልጠናው ከሚያገኘው የቢዝነሥ ሥራውን ለመሥራት ክህሎት ከማግኘት በተጨማሪ ለሥራ ማስኬጃ (መዋጮ) የሚጠየቁትን 20 በመቶ ካፒታል ለሌላቸውና ወደ ቢዝነስ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ አማራጭ አዘጋጅቷል፡፡ በመሆኑም ባለፉት ሦስት ዙሮች ሥልጠና ወስደው ብቁ ሆነው የምስክር ወረቀት የተቀበሉ በአክሲዮን ማኅበር ወደ ቢዝነስ እንዲገቡ በባንካችን ተፈቅዷል፡፡ ባንኩ በአክሲዮን አደራጅቶ ፋይናንስ በማድረግ ለበርካቶች የሥራ ዕድል በመፍጠር ልማትን ለማፋጠን እንቅስቃሴ ጀምሯል፡፡ ለዚህም እያንዳንዱ ሼር 1000 ብር ዋጋ ያለው ሆኖ ዝቅተኛው የሚሸጥ የሼር መጠን አምስት ወይም 5000 ብር ይሆናል፡፡ በአክሲዮን ለመሥራት ሠልጣኞች ራሳቸውንና ሌሎች አብረዋቸው ሊሠሩ የተዘጋጁ የአክሲዮን አባላቶቻቸውን በማስመዝገብ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታ ተዘርግቷል፡፡
በሚፈጠረው የአክሲዮን ማኅበር ውስጥ ዋነኛ (አስተባባሪ) የሚሆኑት ሥልጠና ወስደው ምስክር ወረቀት ያገኙ አባላቱ ቁጥር አንድ ወይም ከዚያ በላይ መሆን የሚገባቸው ሲሆን፣ የሚያስመዘግቧቸው ሌሎች አባላት ግን ሥልጠናውን ያልወሰዱ ከሆነ በቀጣይ በሚኖሩ የሥልጠና ዙሮች መሠልጠን ይገባቸዋል፡፡ በአክሲዮን ማኅበር ለመሥራት የሚመዘገቡ የአክሲዮን ባለቤቶች አብረው ለመሥራት ተስማምተው የቆዩ፣ ሕጋዊ ለመሆን በሂደት ላይ ያሉና በጋራ የሚጠሩበት ስም ካላቸው ማስመዝገብ ይችላሉ፡፡ በአዲስ መልክ የሚቋቋም ከሆነ ግን በሚመዘገቡበት ቀን የባንኩ ቅርንጫፍ ለጊዜው በሚሰጣቸው መለያ ስም ወይም ቁጥር ይመዘገባሉ፡፡ ተመዝጋቢዎች ኢንቨስት ማድረግ የሚፈልጉበትን ቦታና የኢኮኖሚ ዘርፍ እንዲሁም ንዑስ ዘርፍ መምረጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በግላቸው ለመሥራት አቅሙ ያላቸውና የተዘጋጁ ሠልጣኞች በዚህ መንገድ ለመሥራት መዘጋጀታቸውን ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍139❤17👏7
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከጀርመን ልማት ባንክ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ በወረታ ኢንተርናሽናል ቢዝነስ የቀረቡ 17 የእርሻ ትራክተሮች ለሊዝ ፋይናንስ ደንበኞቹ አስረክቧል፡፡
ዘመናዊ ግብርና ማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መሰረት ነው፡፡ በመሆኑም ግብርናን በማዘመን ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን 20 በመቶ የስራ ማስኬጃ በመክፈል 80 በመቶውን በአምስት ዓመታት ተከፍሎ የሚያልቅ የሊዝ ፋይናንስ ብድር አሰጣጥ ስርዓትን በመዘርጋት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለግብርና ሜካናይዜሽን ስራ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
ዘመናዊ ግብርና ማስፋፋት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ መሰረት ነው፡፡ በመሆኑም ግብርናን በማዘመን ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን 20 በመቶ የስራ ማስኬጃ በመክፈል 80 በመቶውን በአምስት ዓመታት ተከፍሎ የሚያልቅ የሊዝ ፋይናንስ ብድር አሰጣጥ ስርዓትን በመዘርጋት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለግብርና ሜካናይዜሽን ስራ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍86👏5🤝3❤1
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት መሰረታዊ ምክነያት ኢንተርፕራይዞች በረዥም ጊዜ በአገር እድገት ውስጥ የሚፈጥሩትን በጎ ተጽእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥሩ ከመሆናቸው ባሻገር ለትላልቅ ኢንዲስትሪዎች ግብዓት የሚያቀርቡ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕከል የሚሆኑ ናቸው፡፡
የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የአገርን ኢኮኖሚ አስተማማኝ በሆነ መሰረት ላይ በመገንባት በኩል ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን የአለም ተሞክሮ ያስገነዝበናል፡፡ ተወዳዳሪ እና የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም የሚችል መሰረተ ሰፊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ድርሻ የላቀ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ በማለፈ የዳበረ ኢኮኖሚ መገንባት ጃፓን እና ቻይናን ጨምሮ አሜሪካ እና ጀርመን ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ለአገራችን ከሚሰጡት የላቀ ፋይዳ በመነሳት ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ የሚያስችል ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ኢንተርፕራይዞቼ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ የቴክኖሎጂ ችግሮችን በመቅረፍ እና የማሽነሪ አቅርቦት ከነድጋፉ በማዘጋጀት፣ የክህሎት ክፈተታቸውን መሙላት የሚያስችል ስልጠና በመስጠት እና በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማገዝ በኩል ባንኩ ተጨባጭ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የአገርን ኢኮኖሚ አስተማማኝ በሆነ መሰረት ላይ በመገንባት በኩል ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን የአለም ተሞክሮ ያስገነዝበናል፡፡ ተወዳዳሪ እና የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም የሚችል መሰረተ ሰፊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ድርሻ የላቀ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ በማለፈ የዳበረ ኢኮኖሚ መገንባት ጃፓን እና ቻይናን ጨምሮ አሜሪካ እና ጀርመን ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ለአገራችን ከሚሰጡት የላቀ ፋይዳ በመነሳት ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ የሚያስችል ስራ እየሰራ ይገኛል፡፡ ኢንተርፕራይዞቼ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ የቴክኖሎጂ ችግሮችን በመቅረፍ እና የማሽነሪ አቅርቦት ከነድጋፉ በማዘጋጀት፣ የክህሎት ክፈተታቸውን መሙላት የሚያስችል ስልጠና በመስጠት እና በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማገዝ በኩል ባንኩ ተጨባጭ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
የልማት አጋርዎ!
👍77❤15
የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የአገር ልማት መሠረቶች!
በ ዜማ ያሬድ
በሌሎች ሀገራት አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የአገርን ኢኮኖሚ አስተማማኝ በሆነ መሠረት ላይ በመገንባት በኩል ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን የሀገራት ተሞክሮ ያስገነዝበናል፡፡ ተወዳዳሪ እና የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም የሚችል መሠረተ ሰፊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ድርሻ የላቀ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ኢንተርፕራይዞች ለልማት ተጠቅሞ በማለፍ ረገድ ዛሬ ላይ የዳበረ ኢኮኖሚ መገንባት የቻሉት ጃፓን፣ ቻይና፣ አሜሪካ እና ጀርመን ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ለአገራችን ከሚሰጡት የላቀ ፋይዳ በመነሣት ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ የሚያስችል ሥራ እየሠራ ይገኛል፡፡ ባንኩ ኢንተርፕራይዞቼ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ የቴክኖሎጂ ችግሮችን በመቅረፍ እና የማሽነሪ አቅርቦት ከነድጋፉ በማዘጋጀት፣ የክህሎት ክፍተታቸውን መሙላት የሚያስችል ስልጠና በመስጠት እና በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማገዝ በኩል ተጨባጭ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት መሰረታዊ ምክንያት ኢንተርፕራይዞች በረዥም ጊዜ በአገር ልማት ውስጥ የሚፈጥሩትን በጎ ተጽእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥሩ ከመሆናቸው ባሻገር ለትላልቅ ኢንዲስትሪዎች ግብዓት የሚያቀርቡ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕከል ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው፡፡
ኢንተርፕራይዞች የገበያ ክፍተት ከመሙላት አንጻር ያላቸው ሚናም ቁልፍ ነው፡፡ በኢኮኖሚ ውስጥ የገበያ ክፍተት የምርት አቅርቦት ከሸማቹ ፍላጎት ጋር ባለመመጣጠኑ እና ገበያ ላይ ያለው ምርት ከሸማቹ ፍላጎት ያነሰ በመሆኑ በአቅርቦት እና በፍላጎት አለመጣጣም የሚፈጠር የገበያ መዛባትን የሚያመላክት ነው፡፡ ታዲያ በገበያ ውስጥ ያለውን የምርት አቅርቦት በማሳደግ የገበያ ክፈተትን መሙላት ጤናማ የሆነ የግብይት ስርዓት ለመገንባት እና በአቅርቦት እና በፍላጎት አለመጣጣም የሚከሰት የገበያ መናርን ለማርገብ ወሳኝ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ኢንዱስትሪዎችን ማስፋት፣ የውጭ ምንዛሬ የሚጠይቁ ምርቶችን በአገር ውስጥ በመተካት አንድም የመግዛት አቅምን ማሳደግ እና በሌላ በኩል ደግሞ በገበያው የምርት መትረፍረፍ እንዲፈጠር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
እንደሚታወቀው በአገራችን ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የአገራችን ሕዝብ የኑሮ መሰረት ግብርና እና ከግብርና ጋር የተያያዘ ሥራ ነው፡፡ ግብርና እና ከግብርና ጋር የተያያዘ ሥራ የአገራችንም የኢኮኖሚ መሰረት ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ስሩ ግብርና መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ተናቦ እና አንዱ ሌላውን እየመገበ እንዲሄድ በማድረግ የኢንዲስትሪ መሰረቱን አስተማማኝ ማድረግ ይቻላል፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት የሚገባው አንድም በአገራችን ዘላቂ እና አስተማማኝ ኢንዱስትሪ ለመገንባት፤ በሌላ መልኩም ሰፊ የሰው ጉልበት የሚይዝና የአገራችንን የግብርና ምርት ግብአቶችን በመጠቀም እሴት ጨምሮ የዓለም ገበያን ጭምር ለመቆጣጠር ሰፊ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ነው፡፡
የብዙ አገራት ተሞክሮ የሚያሳየውም ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ተመጋግቦ የሚሄድ ነው፤ አንዱ ለሌላው ዘርፍ ማደግ እንደ እርሾ የሚያገልግል ነው፡፡ በአገራችን ነባራዊ ሁኔታም የምንገነባው ኢንዱስትሪ የግብርና ምርቶቻችንን እንደ ግብዓት መጠቀሙ በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪነት ከመጨመሩ ባሻገር ለአገር ውስጥ ገበያ ጉድለትን በመሙላት የተረጋጋ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር የሚያስችል ነው፡፡
ከዚህ አንጻር በየአካባቢው የሚፈጠሩ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች እንደ አገር ማምጣት ለምንፈልገው የኢንዱስትሪ ሽግግር መሰረት ናቸው፡፡ በተለይ በአገራችን ያለውን ሰፊ የሰው ሀብት በመያዝ፣ አነስተኛ ካፒታል እና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ረገድ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ተመራጭ ናቸው፡፡
በአገራችን ካለው ከፍተኛ የስራ አጥ ቁጥር አንጻር በቂ የስራ እድል በመፍጠር በኩል አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የላቀ ፋይዳ አላቸው፡፡ በበለጸጉ አገራት ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ግብዓት በማቅረብ እና ሰፊ የስራ እድል መሰረት በመሆን በኩል አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የጎላ ድርሻ አላቸው፡፡
የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅማቸውን በማሳደግ፣ ስልታዊ በሆነ መንገድ የገበያ ክፍተቱን ሊሞላ በሚችል ዘርፍ ላይ እንዲሰማሩ በማሠልጠንና የክህሎት እና የፋይናንስ ችግራቸውን መቅረፍ ቢቻል ከአገራችን አልፎ በጎሮቤት ሀገራት ያለውን ገበያ ሰብረው መግባት የሚችሉበትን እድል ጭምር ማስፋት ይቻላል፡፡
የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቁ ምርቶችን በአገር ውስጥ መተካት የሚቻለውም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በአገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸውን ድርሻ በማስፋት ነው፡፡ ከተለያዩ አገራት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እየተገዙ የሚገቡት የኢንዱስትሪ ምርቶች በአገር ውስጥ በመተካት የገበያ ጉድለቱን መሙላት የሚቻለው የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን ተሳትፎ ማሳደግ ሲቻል ነው፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያደርገውን ስልጠና አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ ኢንተርፕራይዞቹ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ያላቸውን የተሳትፎ ድርሻ በማሳደግ የአገር ኢኮኖሚን ማሳደግ የሚያስችል አቅም እንዲፈጥሩ ማገዝ ይጠበቃል፡፡
በ ዜማ ያሬድ
በሌሎች ሀገራት አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የአገርን ኢኮኖሚ አስተማማኝ በሆነ መሠረት ላይ በመገንባት በኩል ያላቸው ሚና የላቀ መሆኑን የሀገራት ተሞክሮ ያስገነዝበናል፡፡ ተወዳዳሪ እና የውስጥ አቅምን አሟጦ መጠቀም የሚችል መሠረተ ሰፊ ኢኮኖሚ ለመገንባት የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ድርሻ የላቀ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ኢንተርፕራይዞች ለልማት ተጠቅሞ በማለፍ ረገድ ዛሬ ላይ የዳበረ ኢኮኖሚ መገንባት የቻሉት ጃፓን፣ ቻይና፣ አሜሪካ እና ጀርመን ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ለአገራችን ከሚሰጡት የላቀ ፋይዳ በመነሣት ያሉባቸውን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ የሚያስችል ሥራ እየሠራ ይገኛል፡፡ ባንኩ ኢንተርፕራይዞቼ ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ የቴክኖሎጂ ችግሮችን በመቅረፍ እና የማሽነሪ አቅርቦት ከነድጋፉ በማዘጋጀት፣ የክህሎት ክፍተታቸውን መሙላት የሚያስችል ስልጠና በመስጠት እና በተለይ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ተሳትፏቸውን እንዲያሳድጉ በማገዝ በኩል ተጨባጭ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራበት መሰረታዊ ምክንያት ኢንተርፕራይዞች በረዥም ጊዜ በአገር ልማት ውስጥ የሚፈጥሩትን በጎ ተጽእኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥሩ ከመሆናቸው ባሻገር ለትላልቅ ኢንዲስትሪዎች ግብዓት የሚያቀርቡ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕከል ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው፡፡
ኢንተርፕራይዞች የገበያ ክፍተት ከመሙላት አንጻር ያላቸው ሚናም ቁልፍ ነው፡፡ በኢኮኖሚ ውስጥ የገበያ ክፍተት የምርት አቅርቦት ከሸማቹ ፍላጎት ጋር ባለመመጣጠኑ እና ገበያ ላይ ያለው ምርት ከሸማቹ ፍላጎት ያነሰ በመሆኑ በአቅርቦት እና በፍላጎት አለመጣጣም የሚፈጠር የገበያ መዛባትን የሚያመላክት ነው፡፡ ታዲያ በገበያ ውስጥ ያለውን የምርት አቅርቦት በማሳደግ የገበያ ክፈተትን መሙላት ጤናማ የሆነ የግብይት ስርዓት ለመገንባት እና በአቅርቦት እና በፍላጎት አለመጣጣም የሚከሰት የገበያ መናርን ለማርገብ ወሳኝ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ኢንዱስትሪዎችን ማስፋት፣ የውጭ ምንዛሬ የሚጠይቁ ምርቶችን በአገር ውስጥ በመተካት አንድም የመግዛት አቅምን ማሳደግ እና በሌላ በኩል ደግሞ በገበያው የምርት መትረፍረፍ እንዲፈጠር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
እንደሚታወቀው በአገራችን ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የአገራችን ሕዝብ የኑሮ መሰረት ግብርና እና ከግብርና ጋር የተያያዘ ሥራ ነው፡፡ ግብርና እና ከግብርና ጋር የተያያዘ ሥራ የአገራችንም የኢኮኖሚ መሰረት ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት ስሩ ግብርና መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ተናቦ እና አንዱ ሌላውን እየመገበ እንዲሄድ በማድረግ የኢንዲስትሪ መሰረቱን አስተማማኝ ማድረግ ይቻላል፡፡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት የሚገባው አንድም በአገራችን ዘላቂ እና አስተማማኝ ኢንዱስትሪ ለመገንባት፤ በሌላ መልኩም ሰፊ የሰው ጉልበት የሚይዝና የአገራችንን የግብርና ምርት ግብአቶችን በመጠቀም እሴት ጨምሮ የዓለም ገበያን ጭምር ለመቆጣጠር ሰፊ ዕድል የሚሰጥ በመሆኑ ነው፡፡
የብዙ አገራት ተሞክሮ የሚያሳየውም ግብርና ከኢንዱስትሪ ጋር ተመጋግቦ የሚሄድ ነው፤ አንዱ ለሌላው ዘርፍ ማደግ እንደ እርሾ የሚያገልግል ነው፡፡ በአገራችን ነባራዊ ሁኔታም የምንገነባው ኢንዱስትሪ የግብርና ምርቶቻችንን እንደ ግብዓት መጠቀሙ በዓለም ገበያ ላይ ተወዳዳሪነት ከመጨመሩ ባሻገር ለአገር ውስጥ ገበያ ጉድለትን በመሙላት የተረጋጋ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር የሚያስችል ነው፡፡
ከዚህ አንጻር በየአካባቢው የሚፈጠሩ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች እንደ አገር ማምጣት ለምንፈልገው የኢንዱስትሪ ሽግግር መሰረት ናቸው፡፡ በተለይ በአገራችን ያለውን ሰፊ የሰው ሀብት በመያዝ፣ አነስተኛ ካፒታል እና ቴክኖሎጂን በመጠቀም ረገድ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች ተመራጭ ናቸው፡፡
በአገራችን ካለው ከፍተኛ የስራ አጥ ቁጥር አንጻር በቂ የስራ እድል በመፍጠር በኩል አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የላቀ ፋይዳ አላቸው፡፡ በበለጸጉ አገራት ለትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ግብዓት በማቅረብ እና ሰፊ የስራ እድል መሰረት በመሆን በኩል አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች የጎላ ድርሻ አላቸው፡፡
የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅማቸውን በማሳደግ፣ ስልታዊ በሆነ መንገድ የገበያ ክፍተቱን ሊሞላ በሚችል ዘርፍ ላይ እንዲሰማሩ በማሠልጠንና የክህሎት እና የፋይናንስ ችግራቸውን መቅረፍ ቢቻል ከአገራችን አልፎ በጎሮቤት ሀገራት ያለውን ገበያ ሰብረው መግባት የሚችሉበትን እድል ጭምር ማስፋት ይቻላል፡፡
የውጭ ምንዛሪ የሚጠይቁ ምርቶችን በአገር ውስጥ መተካት የሚቻለውም የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በአገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸውን ድርሻ በማስፋት ነው፡፡ ከተለያዩ አገራት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እየተገዙ የሚገቡት የኢንዱስትሪ ምርቶች በአገር ውስጥ በመተካት የገበያ ጉድለቱን መሙላት የሚቻለው የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎችን ተሳትፎ ማሳደግ ሲቻል ነው፡፡ በመሆኑም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያደርገውን ስልጠና አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ ኢንተርፕራይዞቹ በአምራች ኢንዱስትሪ ላይ ያላቸውን የተሳትፎ ድርሻ በማሳደግ የአገር ኢኮኖሚን ማሳደግ የሚያስችል አቅም እንዲፈጥሩ ማገዝ ይጠበቃል፡፡
👍81❤17👏7🤝5
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በ115 ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ አገራዊ ፋይዳቸው ላቅ ያለ ፕሮጀክቶችን የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ በሁለት እግራቸው እንዲቆሙ አስተዋጽዖ አድርጓል፡፡ በግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪ፣ በአግሮ ፐሮሰሲንግ እና በሌሎች የኢንቨስትመንት መስኮች መሰማራት ለሚፈልጉ ሁሉ የቢዝነስ አዋጭነት ፕሮፖዛላቸውን በመገምገም እና ስልጠና በመስጠት ለበርካታ ኢንዱስትሪዎች ለውጥ ምክነያት እየሆነ ነው፡፡
በአገራችን ላሉ ግዙፍ የቡናና የአትክልት እርሻ ልማቶች፣ ቆዳና ሌጦ ፋብሪካዎች፣ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች ከስኬቶቻቸው ፊት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አበርክቶት የጎላ ነው፡፡ በባንኩ የሚሰጣቸውን የብድር እና የክህሎት ድጋፍ አገልግሎት በአግባቡ የተጠቀሙ ታሪካቸው ተቀይሮ የአገር ተስፋ መሆን ጀምረዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እስካሁን በሶስት ዙር ካሰለጠናቸው 33 ሺህ የሚሆኑ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች አዋጪ የሆነ የስራ ሃሳባቸውን በማቅረብ፤ ባንካችን ያስቀመጠውን የብድር መስፈርት አሟልተው የቀረቡ ኢንተርፕራይዞች 20 ቢሊዮን ብር የሚሆነ ብድር በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡ እንደሚታወቀው ባንካችን በአራተኛ ዙር 112 ሺህ የሚሆኑ ተሳታፊዎችን ሲያሰለጥን አንድም ዙሪያቸውን በመመልክት በአቅራቢያቸው የሚገኙ አማራጮችን እንዲመለከቱ ማድረግ የተቻለበት ሲሆን፣ ባንካችን የሚሰጠውን የብድር አገልግሎት ከመጠቀም ባሻገር በቢዝነስ ላይ ያለቸውን የግል ምልከታ እየቀየረና በአነስተኛ ካፒታል አዋጭ የሆነ የስራ ሃሳብ በአጭር ጊዜ ውጤታማ ማድረግ እንደሚችል ማስገንዘብ የተቻለበት ነው፡፡
በአገራችን ላሉ ግዙፍ የቡናና የአትክልት እርሻ ልማቶች፣ ቆዳና ሌጦ ፋብሪካዎች፣ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች ከስኬቶቻቸው ፊት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አበርክቶት የጎላ ነው፡፡ በባንኩ የሚሰጣቸውን የብድር እና የክህሎት ድጋፍ አገልግሎት በአግባቡ የተጠቀሙ ታሪካቸው ተቀይሮ የአገር ተስፋ መሆን ጀምረዋል፡፡
ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እስካሁን በሶስት ዙር ካሰለጠናቸው 33 ሺህ የሚሆኑ የአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች አዋጪ የሆነ የስራ ሃሳባቸውን በማቅረብ፤ ባንካችን ያስቀመጠውን የብድር መስፈርት አሟልተው የቀረቡ ኢንተርፕራይዞች 20 ቢሊዮን ብር የሚሆነ ብድር በሊዝ ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል፡፡ እንደሚታወቀው ባንካችን በአራተኛ ዙር 112 ሺህ የሚሆኑ ተሳታፊዎችን ሲያሰለጥን አንድም ዙሪያቸውን በመመልክት በአቅራቢያቸው የሚገኙ አማራጮችን እንዲመለከቱ ማድረግ የተቻለበት ሲሆን፣ ባንካችን የሚሰጠውን የብድር አገልግሎት ከመጠቀም ባሻገር በቢዝነስ ላይ ያለቸውን የግል ምልከታ እየቀየረና በአነስተኛ ካፒታል አዋጭ የሆነ የስራ ሃሳብ በአጭር ጊዜ ውጤታማ ማድረግ እንደሚችል ማስገንዘብ የተቻለበት ነው፡፡
👍61❤49👏9
በ ዓለም አቀፍ ደረጃ ለ 134 ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ ለሚከበረው ዓለም አቀፍ የሰራተኞች ቀን እንኳን አደረሳችሁ።
የዘንድሮው የሰራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) በዓል "ለሰራተኞች መሰረታዊ ጥያቄዎች አፋጣኝ መፍትሔ" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። Instagram
https://www.instagram.com/dbe_ethiopia/
Twitter
https://twitter.com/DBE_Ethiopia
You tube
https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
Facebook
https://www.facebook.com/dbethiopia
የዘንድሮው የሰራተኞች ቀን (ሜይ ዴይ) በዓል "ለሰራተኞች መሰረታዊ ጥያቄዎች አፋጣኝ መፍትሔ" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። Instagram
https://www.instagram.com/dbe_ethiopia/
https://twitter.com/DBE_Ethiopia
You tube
https://www.youtube.com/@developmentbankofethiopia
https://www.facebook.com/dbethiopia
👍39❤6🤝4
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባዘጋጀው የኢቢሲ ቤተሰብ የወዳጅነት የእግር ኳስ ውድድር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ወደግማሽ ፍጻሜ አለፈ፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን አዲሱን የሚዲያ ኮምፕሌክስ ግንባታ መጠናቀቅ ተከትሎ ለግንባታው መጠናቀቅ በአጋርነት አብረው የሰሩ 8 ያህል ተቆማትን ያሳተፈ የወዳጅነት ውድድር እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በውድድሩ እየተሳተፉና አጋርነታቸውን ሲያሳዩ ከቆዩት ከተቋማቱ መካከል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አንዱ መሆኑን የጠቀሱት የኢቢሲ ስፖርት ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግርማ በቀለ ተቋማቱን እውቅና ለመስጠት ውድድሩ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡
የኢቢሲ አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌ አሁን ለደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ የኢትዮጵያ ልማት ባንክም የራሱን አስተዋጾ በማድረጉ ያመሰገኑት አቶ ግርማ የእግር ኳስ የወዳጅነት ውድድሩ በቀጣይ በተቋማቱ መካከል ያለውን የስራ ግንኙነት እና ወዳጅነት/ አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠነክረው ገልጸዋል፡፡
በውድድሩ ተሳታፊ የነበሩት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የኮርፖሬት ባንኪንግ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው በላይ ባንካችን ኢትዮ ቴሌኮምን አሸንፎ ወደግማሽ ፍጻሜ መግባቱን ጠቅሰው ውድድሩ በሰራተኛው መካከል ያለውን ቅርርብ ይበልጥ እንደሚያጠናክረው አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሰራተኞች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ዮሴፍ ተስፋዬ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከዚህ ቀደም ዋንጫ ማንሳቱን አውስተው በዚህ ውድድር በማሸነፍ ባንካችንን እናስጠራለን ብለዋል፡፡
የፍጻሜ ውድድሩ የኢቢሲ የሚዲያ ኮምፕሌክስ የምርቃት ስነስርአት በሚከናወንበት ማግስት እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን አዲሱን የሚዲያ ኮምፕሌክስ ግንባታ መጠናቀቅ ተከትሎ ለግንባታው መጠናቀቅ በአጋርነት አብረው የሰሩ 8 ያህል ተቆማትን ያሳተፈ የወዳጅነት ውድድር እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በውድድሩ እየተሳተፉና አጋርነታቸውን ሲያሳዩ ከቆዩት ከተቋማቱ መካከል የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አንዱ መሆኑን የጠቀሱት የኢቢሲ ስፖርት ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግርማ በቀለ ተቋማቱን እውቅና ለመስጠት ውድድሩ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡
የኢቢሲ አዲሱ የሚዲያ ኮምፕሌ አሁን ለደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ የኢትዮጵያ ልማት ባንክም የራሱን አስተዋጾ በማድረጉ ያመሰገኑት አቶ ግርማ የእግር ኳስ የወዳጅነት ውድድሩ በቀጣይ በተቋማቱ መካከል ያለውን የስራ ግንኙነት እና ወዳጅነት/ አጋርነት ይበልጥ እንደሚያጠነክረው ገልጸዋል፡፡
በውድድሩ ተሳታፊ የነበሩት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የኮርፖሬት ባንኪንግ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው በላይ ባንካችን ኢትዮ ቴሌኮምን አሸንፎ ወደግማሽ ፍጻሜ መግባቱን ጠቅሰው ውድድሩ በሰራተኛው መካከል ያለውን ቅርርብ ይበልጥ እንደሚያጠናክረው አመላክተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የሰራተኞች ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ዮሴፍ ተስፋዬ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከዚህ ቀደም ዋንጫ ማንሳቱን አውስተው በዚህ ውድድር በማሸነፍ ባንካችንን እናስጠራለን ብለዋል፡፡
የፍጻሜ ውድድሩ የኢቢሲ የሚዲያ ኮምፕሌክስ የምርቃት ስነስርአት በሚከናወንበት ማግስት እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡
👍38❤16
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዲጂታል ዜና መጽሔት
ቁጥር 1
ሚያዚያ 2015 ዓ.ም
ቁጥር 1
ሚያዚያ 2015 ዓ.ም
👍40❤4👏4🤝3