Bank of Abyssinia
184K subscribers
2.63K photos
189 videos
51 files
831 links
Bank of Abyssinia – The Choice for All
Welcome to BoA’s official Telegram channel!

Use @BOA_ATM_bot to access:

ATM locators
Card services & support
Real-time updates
Download Telegram
2% ተጨማሪ ጉርሻ!

የውጭ ገንዘብ ምንዛሪ ተመን ( ጳጉሜ 02 ፣ 2018 ዓ.ም)

ከውጪ ሃገር በደሃብሺል፣ በዌስተርን ዩኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስ ፋስት፣ ቴራፔይ፣ ኢትዮ ዳሽ፣ ፋስትፔይ፣ ሪያና ሌሎች ገንዘብ አስተላላፊዎች በኩል የተላከልዎትን ገንዘብ በባንካችን በኩል ሲቀበሉ ወይም ሲመነዝሩ፤ በሁሉም ቅርንጫፎቻችን ከቀልጣፋ መስተንግዶ ጋር ተጨማሪ ጉርሻ እናበረክትልዎታለን!
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!

September 07, 2026 - Exchange rate at Bank of Abyssinia

Facebook
| Instagram | LinkedIn | Twitter | Website |TikTok | Telegram
20👍10
ባንካችን መጪውን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖች የ4 ሚሊዮን ብር የአይነት ድጋፍ አደረገ   

ባንካችን አቢሲንያ መጪውን የዘመን መለወጫ ምክንያት በማድረግ ዛሬ  ዿግሜ 2 ቀን 2018 ዓ.ም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖቻችን 4 ሚልዮን ብር የሚወጣ የአስቤዛ ድጋፍ አደረገ።  

ማህበራዊ ሃላፊነትን መወጣት ዋነኛ መገለጫው እና ቁልፍ ተቋማዊ ዕሴቱ የሆነው ባንካችን አቢሲንያ ይህን የአይነት ድጋፍ ያደረገው በከተማችን አዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ አረጋውያን፣ወላጆቻቸውን ላጡ ሕጻናትና ሴቶች ነው።

የባንካችን ቺፍ ፋይናንስ ኦፊሰር አቶ አብርሃም ገበየሁ እና ሌሎች የባንካችን የስራ ሃላፊዎች ድጋፉን ለገሀር በሚገኘው በትንሿ ስታዲየም ተገኝተው አስረክበዋል።

አቶ አብርሃም ድጋፉን ካስረከቡ በኋላ “ድጋፉ በመጪው የዘመን መለወጫ በዓል ባንካችን አቢሲንያ ከጎናችሁ እንደሆነና አጋርነቱን ለማሳየት ያደረገው ተግባር ነው” ሲሉ ተናግረዋል።   

በዝግጅቱ ላይ የለሚኩራ፣ የልደታ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም የተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ተወካዮች የተገኙ ሲሆን የቂርቆስ ክ/ከተማ የወረዳ 7 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ወ/ሮ ነኢማ ሎባ በበኩላቸው ባንካችን በየጊዜው ለተቸገሩ ወገኖቻችን የሚያደርገውን ድጋፍ በማድነቅ በወረዳቸው ስም አመስግነዋል፡፡

ድጋፉ በነገው ዕለትም በከተማችን አዲስ አበባና በቢሾፍቱ ለሚገኙ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ወገኖቻችንም የሚደረግ ይሆናል፡፡
42👍19👏6🤩1
2% ተጨማሪ ጉርሻ!

የውጭ ገንዘብ ምንዛሪ ተመን ( ጳጉሜ 03 ፣ 2018 ዓ.ም)

ከውጪ ሃገር በደሃብሺል፣ በዌስተርን ዩኒየን፣ መኒግራም፣ ትራንስ ፋስት፣ ቴራፔይ፣ ኢትዮ ዳሽ፣ ፋስትፔይ፣ ሪያና ሌሎች ገንዘብ አስተላላፊዎች በኩል የተላከልዎትን ገንዘብ በባንካችን በኩል ሲቀበሉ ወይም ሲመነዝሩ፤ በሁሉም ቅርንጫፎቻችን ከቀልጣፋ መስተንግዶ ጋር ተጨማሪ ጉርሻ እናበረክትልዎታለን!
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!

September 08, 2026 - Exchange rate at Bank of Abyssinia

Facebook
| Instagram | LinkedIn | Twitter | Website |TikTok | Telegram
18👍3
አዲስ ዓመት ደረሰ!  ለሚወዷቸው  በአቢሲንያ ሬሚት ደስታቸውን እጥፍ ድርብ ያድርጉ።
መተግበሪያውን ዛሬውኑ ያውርዱ፣ ይጠቀሙ እና 10% ጉርሻ ያግኙ! ዛሬውኑ ይመዝገቡ እና ይጀምሩ
16👏6👍4🤔3
የባንካችን የዘመን መለወጫ በዓል ድጋፍ ዛሬም በአ.አ.፣ በሸገር ሲቲ እና ቢሾፍቱ ቀጥሏል  

ትናንት በአ.አ. ትንሿ ስታዲየም የተጀመረው እና ባንካችን አቢሲንያ ለወገኖቻችን የሚያደርገው የዘመን መለወጫ የአስቤዛ ስጦታ ዛሬም በአዲስ አበባ፣ በሸገር ሲቲ እና በቢሾፍቱ ተከናውኗል።  

በዚህም መሠረት ባንካችን ዛሬ ጳጉሜን 3 ቀን 2018 ዓ.ም በከተማችን የሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት ግቢ ውስጥ በአርቲስት ሙናዬ መንበሩ ስም ለተቋቋመው የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ በሸገር ሲቲ መልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ አሸዋ ሜዳ አካባቢ በመልካ ኖኖ የአይነ ስውራን ማኅበር ለሚታገዙ ወገኖች እንዲሁም ቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኙ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ወገኖቻችን ስጦታውን አስረክቧል።

ስጦታው በተሰጠባቸው ቦታዎች የባንካችን የሥራ ኃላፊዎች እና የክፍለ ከተማ አመራሮች ተገኝተው ስጦታውን አበርክተዋል።

ስጦታው ባንካችን አቢሲንያ በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ለዘመን መለወጫ በዓል መዋያ ካዘጋጀው የብር 4 ሚሊዮን የዓይነት (የአስቤዛ) ድጋፍ አካል ነው።
45👏7👍6