🕊 💖 🕊
🕊 💖 እንኳን አደረሳችሁ 💖 🕊
❝ ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት ! ❞
════════════════
❝ ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤ ደግሞም። ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን [በገዛ ሥልጣኑ ተነሥቷል ብለን] በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።
ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤ ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ። ❞ [ ፩ቆሮ.፲፭፥፲፬ ]
🕊
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
▸ አግአዞ ለአዳም
ሰላም
▸ እምይእዜሰ
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም
❝ ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ❞
🕊
❝ ሞት ሆይ ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል ፥ መቃብርም ሆይ ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡ ❞ [ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
🕊 💖 እንኳን አደረሳችሁ 💖 🕊
❝ ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት ! ❞
════════════════
❝ ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤ ደግሞም። ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን [በገዛ ሥልጣኑ ተነሥቷል ብለን] በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።
ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤ ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ። ❞ [ ፩ቆሮ.፲፭፥፲፬ ]
🕊
ክርስቶስ ተንስአ እሙታን
▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን
አሰሮ ለሰይጣን
▸ አግአዞ ለአዳም
ሰላም
▸ እምይእዜሰ
ኮነ
▸ ፍስሐ ወሰላም
❝ ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ። ❞
🕊
❝ ሞት ሆይ ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል ፥ መቃብርም ሆይ ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡ ❞ [ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
🕊
[ † እንኳን አምላካችን እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ ላረፈባት የመጀመሪያዋ ዕለተ ሰንበትና ለቅዱስ ሕዝቅኤል ነቢይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
† አምላካችን እግዚአብሔር በ፮ [6] ቱ ቀናት ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ በ፯ [7] ኛዋ ዕለት ደክሞት ያይደለ ለእኛ ያስተምረንና ሰንበትን ይቀድስልን ዘንድ አረፈ::
ዕለተ ሰንበት ማለት አንዳንድ ልባቸውን ያሳወሩ ሰዎች እንደሚያወሩት የሥራ መፍቻ ቀን ሳትሆን :-
፩. ከሥጋዊ ተግባራችን ታቅበን መንፈሳዊ ተግባራትን [፮ [6] ቱ ቃላተ ወንጌልን] የምንፈጽምባት:
፪. ለጊዜውም ቢሆን ጥቂት እርፍ ብለን አማናዊቷን ዕረፍተ መንግስተ ሰማያት የምናስብባት ዕለት ናት::
እንደ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትም ለሰንበተ ክርስቲያን ቀዳሚውን ቦታ ሰጥተን ቀዳሚት ሰንበትንም እንደሚገባ ልንጠቀምባት ይገባል::
† የሰንበት ጌታዋ: የምሕረትም አባቷ ጌታችን እግዚአብሔር ለዕረፍተ መንግስቱ የተዘጋጀን ያድርገን::
🕊 † ቅዱስ ሕዝቅኤል ነቢይ † 🕊
† ነቢዩ ቅዱስ ሕዝቅኤል የነበረው ቅ/ል/ክርስቶስ በ፭፻ [500] ዓመት አካባቢ ሲሆን የጼዋዌ [ምርኮ] አባልም ነበር:: እሥራኤልና ይሁዳ ወደ ባቢሎን በምርኮ ሲወርዱ አብሮ ወርዷል:: ቅዱሱ ከ፬ [4]ቱ ዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ሐረገ ትንቢቱም በ፵፰ [48] ምዕራፎች የተዋቀረ ነው::
በዘመኑ ሁሉ ቅድስናን ያዘወተረው ቅዱሱ ከደግነቱ የተነሳ በጸጋማይ [ግራ] ጐኑ ተኝቶ ቢጸልይ ፮፻ [600] ሙታንን አስነስቷል:: ወገኖቹ እሥራኤልንም ያለ መታከት አስተምሯል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህች ዕለት ታላቁን ራዕይ እንዳየ ታስተምራለች:: ነቢዩ በፈለገ ኮቦር ካያቸው ምሥጢራት እነዚህን ያነሷል :-
፩. እግዚአብሔርን በዘባነ ኪሩብ ተቀምጦ ሲሠለስና ሲቀደስ አይቶታል:: የኪሩቤልንም ገጸ መልክእ በጉልህ ተመልክቷል:: [ሕዝ.፩፥፩]
፪. በመጨረሻው ቀን ትንሳኤ ሙታን : ትንሳኤ ዘጉባኤ እንደሚደረግም ተመልክቷል:: [ሕዝ.፴፩፥፩]
፫. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ኆኅት ኅትምት/ኆኅተ ምሥራቅ [የምሥራቅ ደጅ] ሁና አይቷታል::
ይሕ የምሥራቅ ደጅ [በር] ለዘለዓለም እንደታተመ ይኖራል:: የኃያላን ጌታ ሳይከፍት ገብቶ: ሳይከፍት ወጥቷልና:: [ሕዝ.፵፬፥፩] በመጨረሻ ሕይወቱ እሥራኤል ለክፋት አይቦዝኑምና ነቢዩን አሰቃይተው ገድለውታል::
† ከነቢዩ በረከት አምላኩ ያድለን::
🕊
[ † ሚያዝያ ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ በዓላት ]
፩. እግዚአብሔር ሰንበትን ቀደሰ
፪. ቅዱስ ሕዝቅኤል ነቢይ
፫. ቅዱስ ዲዮስቆሮስ [ክፉ ላለመናገር ድንጋይ ጐርሶ የኖረ አባት]
፬. ቅድስት ታኦድራ
፭. ቅዱስ አርሳኒ
፮. ቅዱስ ያሬድ ካህን [ልደቱ]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
፫. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ [አባ ገብረ ሕይወት]
፬. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
፭. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
† " እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ: ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ: ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና :- በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ:: የማይጠፋም የዘለዓለም ስም እሰጣቸዋለሁ:: " † [ኢሳ.፶፮፥፬-፭]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን አምላካችን እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ ላረፈባት የመጀመሪያዋ ዕለተ ሰንበትና ለቅዱስ ሕዝቅኤል ነቢይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
† አምላካችን እግዚአብሔር በ፮ [6] ቱ ቀናት ፳፪ [22] ቱን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ በ፯ [7] ኛዋ ዕለት ደክሞት ያይደለ ለእኛ ያስተምረንና ሰንበትን ይቀድስልን ዘንድ አረፈ::
ዕለተ ሰንበት ማለት አንዳንድ ልባቸውን ያሳወሩ ሰዎች እንደሚያወሩት የሥራ መፍቻ ቀን ሳትሆን :-
፩. ከሥጋዊ ተግባራችን ታቅበን መንፈሳዊ ተግባራትን [፮ [6] ቱ ቃላተ ወንጌልን] የምንፈጽምባት:
፪. ለጊዜውም ቢሆን ጥቂት እርፍ ብለን አማናዊቷን ዕረፍተ መንግስተ ሰማያት የምናስብባት ዕለት ናት::
እንደ ቤተ ክርስቲያን ስርዓትም ለሰንበተ ክርስቲያን ቀዳሚውን ቦታ ሰጥተን ቀዳሚት ሰንበትንም እንደሚገባ ልንጠቀምባት ይገባል::
† የሰንበት ጌታዋ: የምሕረትም አባቷ ጌታችን እግዚአብሔር ለዕረፍተ መንግስቱ የተዘጋጀን ያድርገን::
🕊 † ቅዱስ ሕዝቅኤል ነቢይ † 🕊
† ነቢዩ ቅዱስ ሕዝቅኤል የነበረው ቅ/ል/ክርስቶስ በ፭፻ [500] ዓመት አካባቢ ሲሆን የጼዋዌ [ምርኮ] አባልም ነበር:: እሥራኤልና ይሁዳ ወደ ባቢሎን በምርኮ ሲወርዱ አብሮ ወርዷል:: ቅዱሱ ከ፬ [4]ቱ ዐበይት ነቢያት አንዱ ሲሆን ሐረገ ትንቢቱም በ፵፰ [48] ምዕራፎች የተዋቀረ ነው::
በዘመኑ ሁሉ ቅድስናን ያዘወተረው ቅዱሱ ከደግነቱ የተነሳ በጸጋማይ [ግራ] ጐኑ ተኝቶ ቢጸልይ ፮፻ [600] ሙታንን አስነስቷል:: ወገኖቹ እሥራኤልንም ያለ መታከት አስተምሯል:: ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህች ዕለት ታላቁን ራዕይ እንዳየ ታስተምራለች:: ነቢዩ በፈለገ ኮቦር ካያቸው ምሥጢራት እነዚህን ያነሷል :-
፩. እግዚአብሔርን በዘባነ ኪሩብ ተቀምጦ ሲሠለስና ሲቀደስ አይቶታል:: የኪሩቤልንም ገጸ መልክእ በጉልህ ተመልክቷል:: [ሕዝ.፩፥፩]
፪. በመጨረሻው ቀን ትንሳኤ ሙታን : ትንሳኤ ዘጉባኤ እንደሚደረግም ተመልክቷል:: [ሕዝ.፴፩፥፩]
፫. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ኆኅት ኅትምት/ኆኅተ ምሥራቅ [የምሥራቅ ደጅ] ሁና አይቷታል::
ይሕ የምሥራቅ ደጅ [በር] ለዘለዓለም እንደታተመ ይኖራል:: የኃያላን ጌታ ሳይከፍት ገብቶ: ሳይከፍት ወጥቷልና:: [ሕዝ.፵፬፥፩] በመጨረሻ ሕይወቱ እሥራኤል ለክፋት አይቦዝኑምና ነቢዩን አሰቃይተው ገድለውታል::
† ከነቢዩ በረከት አምላኩ ያድለን::
🕊
[ † ሚያዝያ ፭ [ 5 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ በዓላት ]
፩. እግዚአብሔር ሰንበትን ቀደሰ
፪. ቅዱስ ሕዝቅኤል ነቢይ
፫. ቅዱስ ዲዮስቆሮስ [ክፉ ላለመናገር ድንጋይ ጐርሶ የኖረ አባት]
፬. ቅድስት ታኦድራ
፭. ቅዱስ አርሳኒ
፮. ቅዱስ ያሬድ ካህን [ልደቱ]
[ † ወርሐዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፪. ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
፫. አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጻድቅ [አባ ገብረ ሕይወት]
፬. ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
፭. ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ
† " እግዚአብሔር ሰንበቴን ስለሚጠብቁ: ደስ የሚያሰኘኝንም ነገር ስለሚመርጡ: ቃል ኪዳኔንም ስለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላልና :- በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ:: የማይጠፋም የዘለዓለም ስም እሰጣቸዋለሁ:: " † [ኢሳ.፶፮፥፬-፭]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
ማዕዶት
በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ከትንሳኤ እሁድ ቀጥሎ ያለው ሰኞ "ማዕዶት" ይባላል። ማዕዶት ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም መሻገር ማለት ነው። እንግዲህ በጥንተ ታሪክ እስራኤላውያን የፋሲካን በግ አርደው ደሙን በራፋቸው ላይ በመቀባት ከግብፅ የባርነት ምድር ወደ ከነዓን [ተስፋይቱ ምድር] የተሻገሩበትን ታሪክ ያስታውሰናል ማዕዶትን ስናስብ።
ለእኛም በክርስቶስ ኢየሱስ ላለን ከሞት ወደ ህይወት በክርስቶስ ትንሳኤ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ዘላለም ሕይወት መሻገራችንን የምናበስርበት ዕለት ነው። የድል አዋጃችንን በዚህ ሳምንት መቃብር ፈርሶ፣ ሞት ተሸንፎ የሰው ልጅ የቀድሞ ክብሩን መመለሱን የምስራች የምንልበትም ቀን ነው።
በዚህ ሳምንትም፤ የክርስቶስ ትንሳኤ ለሰው ልጅ ሁሉ የተሰጠ የነፃነት ስጦታ መሆኑ ይታወጃል፣ በቤተክርስቲያን ሥርዓት ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶልናል እየተባለ በደስታ ይዘመራል።እንዲሁ ከትንሳኤ እስከ ዳግም ትንሳኤ ያሉት 8 ቀናት እንደ አንድ ዕለት (እንደ እሁድ) ስለሚቆጠሩ፣ ረቡዕና አርብን ጨምሮ ጾም አይጾምባቸውም።
ማዕዶት መሻገር እንደመሆኑ እኛም ከክፋት ወደ በጎነት፣ ከጥል ወደ ፍቅር፣ ከጭንቀት ወደ ተስፋ የምንሻገርበት ይሁንልን!
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፥ በአማን ተንሥአ!
🕊 💖 🕊
፩. ሰኞ [ ማዕዶት ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
ማዕዶት ማለት [ ዐደወ-ተሻገረ ] ከሚል የግእዝ ግስ የተወረሰ ሲሆን በጥሬው "መሻገር" ማለት ነው:: ይሕም በደመ ክርስቶስ ተቀድሰን: በትንሳኤውም ድኅነት ተደርጐልን መከራን: መርገምን: የኃጢአትን ባሕር: አንድም ባሕረ እሳትን መሻገራችንን ያመለክታል::
- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ
- ከባርነት ወደ ነጻነት
- ከጨለማ ወደ ብርሃን
- ከሞት ወደ ሕይወት
- ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
- ከሲዖል ወደ ገነት
- ከገሐነመ እሳት ወደ መንግስተ ሰማያት
አዳምንና እኛን ልጆቹን አሸጋግሮናል::
አባታችን አዳምና ልጆቹ ከሲዖል የወጡት በዕለተ ዐርብ በሠርክ ቢሆንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሕ ዕለት እዲታሰብ ታዛለች::
ጌታችን ምርኮን ማርኮ: ጥጦስ መንገድ ጠራጊ ሆኖለት ወደ ገነት ሲያስገባቸው ለድንግል ማርያም አሳይቷታል:: እመ አምላክም በፍጹም ልቧ ደስ ተሰኝታለች:: አዳምና ልጆቹ እመቤታችንን ከላይ ሆነው እጅ ነስተዋታል:: እርሷ የድኅነታቸው ምክንያት ናትና::
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
፩. ሰኞ [ ማዕዶት ]
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
ማዕዶት ማለት [ ዐደወ-ተሻገረ ] ከሚል የግእዝ ግስ የተወረሰ ሲሆን በጥሬው "መሻገር" ማለት ነው:: ይሕም በደመ ክርስቶስ ተቀድሰን: በትንሳኤውም ድኅነት ተደርጐልን መከራን: መርገምን: የኃጢአትን ባሕር: አንድም ባሕረ እሳትን መሻገራችንን ያመለክታል::
- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ደሙ
- ከባርነት ወደ ነጻነት
- ከጨለማ ወደ ብርሃን
- ከሞት ወደ ሕይወት
- ከኃጢአት ወደ ጽድቅ
- ከሲዖል ወደ ገነት
- ከገሐነመ እሳት ወደ መንግስተ ሰማያት
አዳምንና እኛን ልጆቹን አሸጋግሮናል::
አባታችን አዳምና ልጆቹ ከሲዖል የወጡት በዕለተ ዐርብ በሠርክ ቢሆንም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚሕ ዕለት እዲታሰብ ታዛለች::
ጌታችን ምርኮን ማርኮ: ጥጦስ መንገድ ጠራጊ ሆኖለት ወደ ገነት ሲያስገባቸው ለድንግል ማርያም አሳይቷታል:: እመ አምላክም በፍጹም ልቧ ደስ ተሰኝታለች:: አዳምና ልጆቹ እመቤታችንን ከላይ ሆነው እጅ ነስተዋታል:: እርሷ የድኅነታቸው ምክንያት ናትና::
════════════════
†††
✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟
🕊 💖 🕊
❤1