አለ ሕግ
16K subscribers
3.3K photos
34 videos
1.94K files
3.72K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
በየሶስት ወሩ የሚከፈል ታክስ መክፈያ እና ማሳወቂያ ጊዜ


በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ 1395/2017 አንቀጽ 89 እንደተደነገገው በየሶስት ወሩ የሚከፈለው ግብር ግብር ከፋዩ የሂሳብ ሪፖርት በሚያቀርብበት ወር መጨረሻ ጀምሮ ካለው ሶስት ወር ጊዜ በኋላ ባለው 30 ቀናት ውስጥ ይሆናል፡፡ በዚሁ መሰረት የሂሳብ ሪፖርታቸውን ጥቅምት/2018 ዓ.ም ያጠናቀቁ ግብር ከፋዮች የመጀመሪያውን የካቲት/2018፣ ሁለተኛውን ግንቦት/2018፣ ሶስተኛውን ነሀሴ/2018ዓ.ም ይከፍሉና አራተኛውን እና የማጠቃለያ የሂሳብ ሪፖርታቸውን እስከ ጥቅምት/2019 ዓ.ም የሚያጠናቅቁ ይሆናል፡፡
የሂሳብ ሪፖርታቸውን እ.ኤ.አ በኤፕሪል/2025 የዘጉ ድርጅቶች የመጀመሪያውን ኦገስት/2025፣ ኖቬምበር/2025 እና ፌብርዋሪ/2026 ይከፍሉና አራተኛውን እና የማጠቃለያ የሂሳብ ሪፖርታቸውን እስከ ኤፕሪል/2026 ዓ.ም የሚያጠናቅቁ ይሆናል፡፡

በየሶስት ወሩ የሚከፈለው የአመታዊ ግብሩ 25% ወይም 1/4ኘኛ ሲሆን፣ በሶስት ወር ውስጥ ከገቢያችን ላይ የተቀነሰ የቅድመ ግብር (withholding tax) ካለ ከምንከፍለው ክፍያ ላይ ተቀናሽ እናደርጋለን፡፡

ለምሳሌ፡ X PLC የሂሳብ ሪፐርቱን ያቀረበው ጥቅምት 2018ዓ.ም ቢሆን እና የከፈለው ታክስ 1,500,000 ቢሆን፤
የካቲት/2018ዓ.ም ላይ 375,000
ግንቦት/2018ዓ.ም ላይ 375,000
ሶስተኛውን ነሀሴ/2018ዓ.ም 375,000
አራተኛውን እና የመጨረሻውን ጥቅምት/2019ዓ.ም የሂሳብ ሪፖርት ያሰራ እና መከፈል ያለበት ግብር ከ2018 በጀት ከፍ ያለ ከሆነ 375,000ብር ላይ ልዩነቱን ጨምሮ፣ ከ2018 በጀት ዝቅ ያለ ከሆነ ደግሞ ከ375,000ብር ቀንሶ ልዩነቱን ብቻ ይከፍላል፡፡
መጋቢት እና ሚያዚያ ወር ላይ ዊዝሆልድ የተደረገ 150,000ብር ቢኖረው ግንቦት ላይ ከሚከፍለው ታክስ ላይ ተቀናሽ ማድረግ አለበት፡፡
ይህ ማለት 375,000 - 150,000 = 225,000ብር ይሆናል ማለት ነው፡፡
https://t.me/AleHig
3🔥1
#ከፍቺ_በኋላ_የተደረገ የንብረት ስምምነት- በፍርድ ቤት መጽደቅ አላስፈላጊነት

ከ “የቤተሰብ ህግ፥ በሰበር ችሎት” የተወሰደ
#ተጋቢዎች በትዳር ውስጥ እያሉ የሚያደርጓቸው የንብረት ስምምነቶች ወይም የጋብቻ ውል ማሻሻያዎች በሕግ ፊት ተቀባይነት እንዲኖራቸው በፍርድ ቤት መጽደቅ አስፈላጊነት ጋብቻው በፍቺ ከፈረሰ በኋላ ተጋቢዎቹ የሚያደርጓቸውን የንብረት ስምምነቶች የሚመለከት አለመሆኑን የሰበር ውሳኔዎች በዝርዝር ያስረዳሉ። ከፍቺ በኋላ የሚደረግ የንብረት ስምምነት ተጋቢዎቹ እንደገና ታርቀው ጋብቻቸውን ለመቀጠል በሚያደርጉት ጥረት ውስጥ ሊከሰት የሚችል ሲሆን እንዲህ ዓይነቱ ስምምነት በፍርድ ቤት እንዲጸድቅ ሕጉ በግልጽ አያስገድድም።

#ይህንን መርህ በተመለከተ በሰበር መዝገብ ቁጥር 181543 ላይ ግልጽ የሆነ የሕግ ትርጉም ተሰጥቶበታል። በዚህ ጉዳይ ላይ ተጋቢዎቹ ቀደም ብለው በፍቺ ከተለያዩ በኋላ እርቅ አድርገው ጋብቻቸውን ለመቀጠል ሲስማሙ አንደኛው ወገን ከጋብቻ በፊት በውርስ ያገኘው ቤት የጋራ ንብረት እንዲሆን በውል ተስማምተዋል። የበታች ፍርድ ቤቶች ይህ ስምምነት በፍርድ ቤት ስላልጸደቀ ዋጋ የለውም በማለት ውድቅ ቢያደርጉትም የሰበር ሰሚ ችሎቱ ግን ውሳኔውን ሽሮታል። ችሎቱ በሰጠው አስገዳጅ ትርጉም የፌዴራል የቤተሰብ ሕግ አዋጅ አንቀጽ 47 እና 73 የሚያስገድዱት የጋብቻ ውልን የማሻሻል ወይም በጋብቻ ውስጥ የመዋዋል ግዴታ በፍርድ ቤት እንዲጸድቅ ሲሆን ይህ ድንጋጌ ተጋቢዎች ጋብቻቸው በሕግ ከፈረሰ በኋላ የሚያደርጉትን ስምምነት አይመለከትም። በመሆኑም ጋብቻው ከፈረሰ በኋላ የተደረገው የእርቅና የንብረት ስምምነት በፍርድ ቤት ሳይጸድቅም የጸና ሕጋዊ ውጤት ይኖረዋል።

#በተመሳሳይ ሁኔታ በአማራ ክልል የቤተሰብ ሕግ አተገባበር ላይም ተመሳሳይ አቋም በሰበር መዝገብ ቁጥር 148204 ላይ ተንጸባርቋል። ተጋቢዎች በፍርድ ቤት ከተፋቱ በኋላ ከፍርድ ቤት ውጭ ጋብቻ የማደስ ስምምነት ያደረጉ ሲሆን በዚህ ስምምነት ወቅት ወፍጮን ጨምሮ የተለያዩ ንብረቶችን ተከፋፍለዋል። የክልሉ የቤተሰብ ሕግ አንቀጽ 84 ተጋቢዎች በትዳር ውስጥ እያሉ የሚያደርጉት ውል በፍትሕ አካል መጽደቅ እንዳለበት ቢደነግግም ስምምነቱ የተደረገው ጋብቻው በፍርድ ቤት ከፈረሰ በኋላ እስከሆነ ድረስ ይህ አንቀጽ ተፈጻሚነት እንደሌለው ችሎቱ ወስኗል።

#ከፍቺ በኋላ የሚደረጉ የንብረት ስምምነቶች በአፈፃፀም ሂደት ላይም ያላቸው ተጽዕኖ ከፍተኛ ነው። ተጋቢዎች ከፍቺ በኋላ በሽማግሌዎች ወይም በራሳቸው ስምምነት አድርገው ንብረት ከተረካከቡና ይህንኑም በአፈፃፀም ችሎት ቀርበው ካረጋገጡ ስምምነቱ በፍርድ ቤት አልጸደቀም በሚል ምክንያት እንደገና አዲስ ክርክር ሊነሳበት አይችልም። የአፈፃፀም ትዕዛዝ የመጨረሻነት ባህሪ ስላለውና ግራ ቀኙ በስምምነቱ መሠረት ንብረት መረካከባቸውን ካረጋገጡ በኋላ ስምምነቱን መካድ አይቻልም። በተጨማሪም እንዲህ ያሉ ስምምነቶች በሰው ምስክር ሊረጋገጡ የሚችሉ ሲሆን በተለይም የሁለቱም ወገን ምስክሮች ስለ ስምምነቱ መኖርና ስለ ንብረት ክፍፍሉ ከመሰከሩ ስምምነቱ ጸንቶ ይቆያል።

#ከላይ በተጠቀሱት ሁለት መዝገቦች ከፍቺ በኋላ የሚደረግ የንብረት ስምምነት በሕግ ፊት ተቀባይነት እንዲኖረው በፍርድ ቤት መጽደቅ እንደ ቅድመ ሁኔታ እንዳልተቀመጠ የሰበር ችሎት ድምዳሜ ላይ ደርሷል። ችሎቱ አክሎ ኣንዳለው የሕጉ ጥበቃ በትዳር ውስጥ ለሚደረጉ ውሎች ብቻ የተገደበው ተጋቢዎች በትዳር ውስጥ ባላቸው ልዩ ግንኙነት ምክንያት አንደኛው በሌላው ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል በሚል ስጋት ሲሆን ጋብቻው ከፈረሰ በኋላ ግን ተዋዋዮቹ እንደ ማንኛውም ነጻ ግለሰብ ስለሚቆጠሩ ስምምነታቸው በውል ሕግ መሠረት ተፈጻሚነት ይኖረዋል። ሁለቱም ውሳኔዎች የተሰጡት ፍቺ በፍርድ ቤት ከተወሰነ በኋላ ተጋቢዎች “ጋብቻውን ማደስ” በሚል እርቅ በፈጸሙበት ሁኔታ ነው። በችሎቱ ሀተታ ላይ እንደሰፈረው ተጋቢዎች ከፍቺ በኋላ ጋብቻቸውን ለማደስ በሚያደርጉት የእርቅ ስምምነት ውስጥ የግል ንብረትን የጋራ ለማድረግ ወይም ንብረት ለመከፋፈል ቢስማሙ ይህ ስምምነታቸው በፍርድ ቤት ባይጸድቅም በመካከላቸው አስገዳጅ የሆነ ሕጋዊ ውጤት ያስከትላል።

#ምንም እንኳን በሁለቱም የሰበር ውሳኔዎች ላይ የንብረት ስምምነት የተደረገው በ “ጋብቻ ማደስ” ዐውድ ቢሆንም “የጋብቻ ማደሱ” የክርክሩ ጭብጥ አልነበረም። ዳግም ጋብቻ ተመስርቷልም አልተባለም። ስለሆነም “ተጋቢዎች ጋብቻቸው በፍርድ ቤት ከፈረሰ በኋላ በሕግ ከተመለከቱት የጋብቻ አፈጻጸም ሥርዓቶች (በክብር መዝገብ ሹም፣ በሃይማኖት ወይም በባህል) ውጭ አዲስ የጋብቻ ሥርዓት ሳይፈጽሙ አብረው መኖራቸው ብቻውን ጋብቻው እንደቀጠለ ያስቆጥራል የሚለው የሰበር ትርጓሜ” በፌዴሬሽን ምክር ቤት መሻሩ በውሳኔዎቹ ይዘት ላይ የሚያስከትለው ለውጥ የለም። ምክንያቱም ከችሎቱ ሀተታ እንደሚነበበው የህግ አተረጓጎሙ መነሻ ያደረገው የጋብቻ አለመኖር እንጂ መኖሩ አይደለም። በተለይም “የሕጉ ጥበቃ በትዳር ውስጥ ለሚደረጉ ውሎች ብቻ የተገደበው ተጋቢዎች በትዳር ውስጥ ባላቸው ልዩ ግንኙነት ምክንያት አንደኛው በሌላው ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር ይችላል በሚል ስጋት” እንደሆነ የተገለጸው አመክንዮ የችሎቱ አቋም በ “ጋብቻ ማደስ” ተጽዕኖ ስር እንዳልወደቀ አስረጂ ነው።

#እዚህ ላይ መነሳት ያለበት መሰረታዊ ጥያቄ ይህ የሰበር ችሎቱ የህግ ትርጉም ችሎቱ በሌሎች መዝገቦች ላይ “የፍቺ ውጤቶች ስምምነት” በፍርድ ቤት መጽደቅ እንዳለባቸው ከያዘው ጠንካራ አቋም ጋር እንዴት ይታረቃል? የሚለው ነው። ምናልት ይሄኛው ህጋዊ ውጤት ይኑረውም አይኑረውም ተጋቢዎች ከተፋቱ በኋላ አንድ ላይ ለመኖር ታርቀው የሚያደርጉት የንብረት ስምምነት ሲሆን ኋለኛው ግን የፍቺ ውጤት ስምምነት ነው ቢባል የችሎቱን አቋም ያስታርቀው ይሆን? ይሁን እንጂ በዚህ መልኩ ድምዳሜ ላይ መድረስ አንድን ህንጻ ፊት እና ከኋላ አይቶ “ሁለት የተለያዩ ህንጻዎች ናቸው” ስለመሆናቸው እርግጠኛ የመሆን ያክል የማያስኬድ ነው።
አብርሀም ዮሀንስ
https://t.me/AleHig
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
11
የቤተሰብ ህግ በሰበር ችሎት

📢 አዲስ የህግ መጽሐፍ የቅድመ-ትዕዛዝ ጥሪ!

"የቤተሰብ ህግ በሰበር ውሳኔዎች" — በአቀራረቡ ለየት ያለና በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ላይ ያተኮረ አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለህትመት ይበቃል።

በአሁኑ ወቅት የህትመት ዋጋ መናር ስራዎችን ለህዝብ ለማድረስ ፈታኝ ቢሆንም፣ ይህ እውቀት ለባለሙያውና ለአንባቢው እንዲደርስ ለማድረግ በጣም ውስን ኮፒዎችን (ከ300-500 ብቻ) ለተመዝጋቢዎች ለማቅረብ ተዘጋጅተናል።

🎯 የምዝገባ አማራጮች እና ልዩ ጥቅሞች
መጽሐፉን በሁለት መንገድ መመዝገብ ይችላሉ፦

1. ቅድሚያ ገዢ (Early Bird):
ቅድሚያ ክፍያ በመፈጸም መጽሐፉ እስኪወጣ ለሚጠብቁ ደንበኞች የሚከተሉት ልዩ የቴክኖሎጂ ጥቅሞች ለተወሰነ ጊዜ በነጻ ይሰጣሉ፦

* Desktop Application: ከቅፅ 1-28 ያሉ፣ የ7 ዳኞች ትርጉም፣ የህፃናትና ሴቶች ጉዳይን ጨምሮ ከ 10,000 በላይ የሰበር ውሳኔዎች ማጠቃለያ የያዘ። እያንዳንዱ ማጠቃለያ የክርክሩን አመጣጥ፣ ቁልፍ የህግ ትርጉም እና የፍርዱን አመክንዮ በዝርዝር የያዘ ሲሆን፤ ፈጣንና ዘመናዊ መፈለጊያ (Search) ተገጥሞለታል።


* Mobile Application: ከ10 ሺህ በላይ ውሳኔዎችን "የአንድ መስመር" ማውጫ የያዘ መተግበሪያ።
2. ኋላ ገዢ (Standard):
መጽሐፉ ሲታተም ክፍያ ፈጽመው መጽሐፉን ብቻ በአድራሻቸው የሚረከቡ።

📘 የመጽሐፉ መረጃ
* ርዕስ፦ የቤተሰብ ህግ
* የገጽ ብዛት፦ 350
* ዋጋ፦ 1,000 ብር (Delivery/ማድረሻን ጨምሮ)

📝 እንዴት ይመዘገባሉ?
ኮፒው በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ስምዎትንና አድራሻዎትን በሚከተለው ስልክ ቁጥር ይላኩ፦

📞 ስልክ፦ 0915735560 (በText, Telegram ወይም WhatsApp)
ሲመዘገቡ የሚከተለውን መረጃ ያካትቱ፦
* ሙሉ ስም
* ስልክ ቁጥር
* አድራሻ (መጽሐፉ እንዲደርሶ የሚፈልጉበት)

* የምዝገባ አይነት፦ "ቅድሚያ ገዢ" ወይም "ኋላ ገዢ" በማለት ይጥቀሱ።

> ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉ ለተመዝጋቢዎች ብቻ የሚሸጥ ሲሆን፣ ርክክቡም ባለዎት አድራሻ ላይ በመመስረት በቤትዎ ወይም በቢሮዎ ድረስ በነጻ ይከናወናል።
>
ይህንን መልዕክት ለሌሎች የህግ ባለሙያዎች በማጋራት ይተባበሩ!


(ከታች ምስል mobile app screenshots)
6😁1
የቤተሰብ ህግ በሰበር ችሎት ✍️

📢 አዲስ የህግ መጽሐፍ የቅድመ-ትዕዛዝ ጥሪ!

"የቤተሰብ ህግ በሰበር ውሳኔዎች" — በአቀራረቡ ለየት ያለና በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔዎች ላይ ያተኮረ አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለህትመት ይበቃል።

በአሁኑ ወቅት የህትመት ዋጋ መናር ስራዎችን ለህዝብ ለማድረስ ፈታኝ ቢሆንም፣ ይህ እውቀት ለባለሙያውና ለአንባቢው እንዲደርስ ለማድረግ በጣም ውስን ኮፒዎችን (ከ300-500 ብቻ) ለተመዝጋቢዎች ለማቅረብ ተዘጋጅተናል።

🎯 የምዝገባ አማራጮች እና ልዩ ጥቅሞች
መጽሐፉን በሁለት መንገድ መመዝገብ ይችላሉ፦

1. ቅድሚያ ገዢ (Early Bird):
ቅድሚያ ክፍያ በመፈጸም መጽሐፉ እስኪወጣ ለሚጠብቁ ደንበኞች የሚከተሉት ልዩ የቴክኖሎጂ ጥቅሞች ለተወሰነ ጊዜ በነጻ ይሰጣሉ፦

* Desktop Application: ከቅፅ 1-28 ያሉ፣ የ7 ዳኞች ትርጉም፣ የህፃናትና ሴቶች ጉዳይን ጨምሮ ከ 10,000 በላይ የሰበር ውሳኔዎች ማጠቃለያ የያዘ። እያንዳንዱ ማጠቃለያ የክርክሩን አመጣጥ፣ ቁልፍ የህግ ትርጉም እና የፍርዱን አመክንዮ በዝርዝር የያዘ ሲሆን፤ ፈጣንና ዘመናዊ መፈለጊያ (Search) ተገጥሞለታል።


* Mobile Application: ከ10 ሺህ በላይ ውሳኔዎችን "የአንድ መስመር" ማውጫ የያዘ መተግበሪያ።
2. ኋላ ገዢ (Standard):
መጽሐፉ ሲታተም ክፍያ ፈጽመው መጽሐፉን ብቻ በአድራሻቸው የሚረከቡ።

📘 የመጽሐፉ መረጃ
* ርዕስ፦ የቤተሰብ ህግ
* የገጽ ብዛት፦ 350
* ዋጋ፦ 1,000 ብር (Delivery/ማድረሻን ጨምሮ)

📝 እንዴት ይመዘገባሉ?
ኮፒው በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ስምዎትንና አድራሻዎትን በሚከተለው ስልክ ቁጥር ይላኩ፦

📞 ስልክ፦ 0915735560 (በText, Telegram ወይም WhatsApp)
ሲመዘገቡ የሚከተለውን መረጃ ያካትቱ፦
* ሙሉ ስም
* ስልክ ቁጥር
* አድራሻ (መጽሐፉ እንዲደርሶ የሚፈልጉበት)

* የምዝገባ አይነት፦ "ቅድሚያ ገዢ" ወይም "ኋላ ገዢ" በማለት ይጥቀሱ።

> ማሳሰቢያ፦ መጽሐፉ ለተመዝጋቢዎች ብቻ የሚሸጥ ሲሆን፣ ርክክቡም ባለዎት አድራሻ ላይ በመመስረት በቤትዎ ወይም በቢሮዎ ድረስ በነጻ ይከናወናል።
>
ይህንን መልዕክት ለሌሎች የህግ ባለሙያዎች በማጋራት ይተባበሩ!


(ከላይ ምስል mobile app screenshots)
11
👉#ሰበር #መረጃ
👉 ሰበር #ውሳኔ
👉 ሰበር #ትዕዛዝ
👉 ሰበር #መግለጫ
👉 ሰበር #ምርመራ

👉ሰበር ዝውውር
👉 ሰበር #ውጤት
👉ሰበር #ቅሌት
👉ሰበር #ሹመት

👉ሰበር የዋጋ ተመን
👉 ሰበር ስምምነት
👉 ሰበር #ቅናሽ

👉 ሰበር #እውነታ
👉ሰበር #ምስል
👉 #ሰበር_ጥቆማ
#አለሕግ #AleHig
6
የፍትሐ ብሔር ሥነ-ሥርዓት ሕግ ቁጥር 418፣ ሦስተኛ ወገኖች ንብረቱ በሚታገድበት ወቅት ሕጋዊ ጥቅም ወይም ይዞታ እንዳላቸው ማረጋገጥ ከቻሉ፣ በንብረት እገዳው ላይ ተቃውሞ እንዲያቀርቡ ይፈቅዳል። ይህ ሥነ-ሥርዓታዊ ጥበቃ የንጹሐን ሦስተኛ ወገኖች ንብረት የሌሎችን ዕዳ ለመክፈያነት እንዳይውል ይከላከላል፤ ሆኖም ይህ ሂደት የአፈጻጸም ፍርድ ቤቱ ከአፈጻጸሙ ወሰን ውጭ ውሎችን እንዲሰርዝ ወይም አዲስ የባለቤትነት መብት እንዲሰጥ ስልጣን አይሰጠውም።
👍135
ሰበር ን በአንድ ዓረፍተ ነገር
thank you all በመጀመሪያ ታላቅ ምሴጋናዬን እያቀረብኩኝ

For Pre-Order ተመዝጋቢዎች በገባሁት ቃል መሠረት ሁለት application available አደርጋለው።
እስከዛው beta version የጫናችሁ ጠቃሚ ሆኖ እንዳገኛችሁት ምላሻችሁን ስለሰጣችሁኝ ከልብ አመሠግናለው።
ስለዚህኛው Cassation Key Rules app
ጥቂት ልበል።
አፕሊኬሽኑ የሰበርን ውሳኔ በአንድ ዓረፍተ ነገር የሚያጠቃልል ማውጫ ነው። ማውጫውን አይታችሁ ዋናውን ውሳኔ ማንበብ አትርሱ። ከዚህ በታች ቅንጭብ ቀርቧል።

#​የሰበር_ውሳኔዎች_ማጠቃለያ

#​የሰበር መዝገብ ቁጥር 197368፦ በአንድ ዓይነት ጉዳይ ላይ በሌላ ፍርድ ቤት ክርክር እየተካሄደ ነው (Pending Suit) የሚለው መቃወሚያ ተፈጻሚ የሚሆነው፣ ሁለቱ ክሶች ተመሳሳይ የውል መሠረት ያላቸው ሲሆን ብቻ ነው።

#​የሰበር መዝገብ ቁጥር 197405፦ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዓለም አቀፍ ድርጅቶች ላይ ያለው የስረ ነገር ሥልጣን የሚመነጨው ጉዳዩ ዓለም አቀፍ ሕግን ተፈጻሚ የሚያደርግ ሲሆን እንጂ፣ ተከራካሪው አካል ዓለም አቀፍ ድርጅት ስለሆነ ብቻ አይደለም።

#​የሰበር መዝገብ ቁጥር 197695፦ የሰበር ሰሚ ችሎት ሥልጣን መሠረታዊ የሕግ ስህተትን በማረም ላይ የተገደበ በመሆኑ፣ የበታች ፍርድ ቤቶች ማስረጃን መዝነው የደረሱበትን የፍሬ ነገር ድምዳሜ የመመርመር ሥልጣን የለውም።

#​የሰበር መዝገብ ቁጥር 197736፦ ፍርድ ቤቶች ዳኝነት መስጠት ያለባቸው በተጠየቀው ዳኝነት አግባብ ቢሆንም፣ በክርክር ሂደት በማስረጃ የተረጋገጠን ዝርዝር ፍሬ ነገር (ለምሳሌ የመንገድ ስፋት) መወሰን ባልተጠየቀ ዳኝነት መወሰን ተብሎ አይቆጠርም።

#​የሰበር መዝገብ ቁጥር 197790፦ በፍትሐብሔር ክርክር ውስጥ የወጥነት እና የተገማችነት መርህ ወሳኝ በመሆኑ፣ ቀደም ሲል በሌላ መዝገብ ላይ ተወስኖ የጸና ጭብጥ (ለምሳሌ የውል መቋረጥ ጥፋት) በድጋሚ ሊመረመር አይገባም።

#​የሰበር መዝገብ ቁጥር 199060፦ የከፍተኛ ፍርድ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያን (ለምሳሌ ይርጋን) በተመለከተ የበታች ፍርድ ቤት የሰጠውን ብይን ሽሮ ውሳኔ ከሰጠ፣ ይግባኙ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት መቅረብ አለበት።
በጠበቃ አብርሀም ዮሀንስ
18👍1
ምን አይነት የፕላስቲክ ማሸጊያዎች ተፈቅደዋል ?

የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፥ " በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 መሰረት የፕላስቲክ ማሸጊያ ማለት እቃዎችን ከብክለት ለመከላከል ወይንም ከሌላ ነገር ጋር እንዳይቀላቀል ለማድረግ በእቃው አምራች ጥቅም ላይ የሚውል ከፕላስቲክ የሚዘጋጅ መጠቅለያ ወይም መያዣ ነው የሚል ትርጉም ተሰጥቶታል " ብሏል።

በዚህም መሰረት ፦
- የምግብ፣
- የባልትና ውጤቶችን፣
- ለላውንደሪ አገልግሎት እና ሌሎች ምርቶችን ለማሸግ የሚውሉ የፕላስቲክ ማሸጊያዎች በአዋጁ የተፈቀዱ መሆኑን ገልጿል።

የእነዚህ ማሸጊያዎች የቆሻሻ አያያዝ በአዋጁ እና አዋጁን ተከትለው በሚወጡ የማስፈፀሚያ ህጎች እንደሚተገበር አመልክቷል።

(የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
የካቲት 18 ቀን 2018

@tikvahethiopia
9👍3
2👍2
የቀዳሚነት መብት ጨረታ ጊዜ እና የጋራ ባለሀብት በተመለከተ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰበር መዝገብ ቁጥር መ/ቁ 215842፣ ቅጽ 28፣ የፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1126(1)፣ 1386-1409 እና የፍ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 430(1)፣ 443 መሰረት ተደርጐ በአብላጫ ድምፅ የህግ ትርጉም ተሰጥቷል

🏠በጨረታ በሚሸጠው ንብረት ላይ የጋራ ባለሀብት በመሆኑ ምክንያት በሕግ የቀዳሚነት መብት የተጠበቀለት ወገን ንብረቱን ለመግዛት በጨረታ ተወዳዳሪ ሆኖ ካልቀረበ በቀር ጨረታው ተከናውኖ አሸናፊው ከታወቀ በኋላ የጨረታውን ውጤት አውቆ የሚያቀርበው የቀዳሚነት መብት ጥያቄ በጨረታው አሸናፊ መብት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ስለሚኖረው አቤቱታው ተቀባይነት የሌለውም።
ዋና ዋና ነጥቦች (Key Legal Points)
#የቅድመ-ሁኔታ ግዴታ፦ የቀዳሚነት መብት ያለው ሰው መብቱን ለመጠቀም የግድ በጨረታው ሂደት ውስጥ እንደ ተወዳዳሪ መሳተፍ አለበት።
#የጊዜ ገደብ፦ ጨረታው ተጠናቆ አሸናፊ ከተለየ በኋላ የሚቀርብ የ"እኔ እገዛለሁ" ጥያቄ በሕግ ተቀባይነት የለውም።
#የሦስተኛ ወገን መብት፦ ሕጉ የጨረታውን አሸናፊ (የገዢውን) መብትና ጥቅም ለመጠበቅ ሲል ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኋላ የሚመጡ ጥያቄዎችን ውድቅ ያደርጋል።
Fiker Getachew
10👍5