አለ ሕግ
16.1K subscribers
3.29K photos
34 videos
1.93K files
3.72K links
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
Download Telegram
የደቦ ፍርድ ከጎዳና እስከ ዲጂታል አደባባይ ለሕግ የበላይነት የፈጠረው ስጋት✍️✍️✍️

በሀገራችን እየተለመደ የመጣው #የደቦ_ፍርድ (Mob Justice) ከጎዳና እስከ ዲጂታል መድረኮች ፍትሕን ከችሎት አውጥቶ አደባባይ ላይ በመጣል የሀገርን ገጽታና የዜጎችን ደኅንነት ከፍተኛ አደጋ ላይ ጥሎ ይገኛል፡፡ በማንኛውም ሥልጡን ማኅበረሰብ ውስጥ ፍትሕ የሚሰጠው በሕግ በተቋቋሙ የፍርድ አካላት እንጂ በቲክቶክ የዲጂታል ፍረጃ ወይም በጎዳና ስሜታዊ ስብስብ አይደለም፡፡
አለሕግ ስንል፤ አወ ሕግ ስላለ ነው፡፡ ሕግ ባለበት ሀገር ደግሞ ፍትሕ የማግኘት መብት የሁሉም ሰው ነው፡፡ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37 መሠረት፣ የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤት እንጂ የቲክቶክ መንደር ወይም የሰፈር ቡድን አይደለም፡፡
ችሎት ማለት ዝም ብሎ አዳራሽ ወይም ወንበር አይደለም፤ ችሎት የሥልጣን፣ የጥበብ እና የውሳኔ መፍለቂያ ነው። በሕግ ቋንቋ ችሎት ማለት፡-
1. ክርክር የሚሰማበትና የሚደመጥበት፣
2. ማስረጃ የሚመዘንበትና እውነታው የሚመረመርበት፣
3. በዳኞች አማካኝነት የመጨረሻ ሕጋዊ ውሳኔ የሚሰጥበት የተቀደሰ ሥርዓት ነው፡፡
በሕገ-መንግሥታችን አንቀጽ 20 መሠረት፣ ማንኛውም ሰው ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ የመቆጠር መብት አለው፡፡ ሆኖም ዛሬ ወንጀለኛን ማጋለጥ በሚል ሰበብ፤ የግል ቂም በቀልንና ጥላቻን ለመወጣት የሚደረጉ የዲጂታል ስም ማጥፋት ዘመቻዎች ንጹሕ ዜጎችን ለከፋ ሥነልቦናዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እየዳረጉ ነው፡፡ በተለይ በቲክቶክ እና መሰል መድረኮች ላይ ፎሎወር እና ላይክ ለማግኘት ብቻ ፖሊስ ምርመራ ሳይጀምር ሰዎችን ማዋረድና እንደወንጀለኛ መቁጠር እንዲሁም ለጥቃት ማጋለጥ በራሱ ከባድ ወንጀል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡
ብዙዎች በቡድን ስንሆን አንጠየቅም ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፤ ይህ ግን ትልቅ የሕግ ስህተት ነው፡፡ በወንጀል ሕጋችን መሠረት በቡድን/በደቦ ነው የፈጸምኩት የሚል ምክንያት ከቅጣት አያድንም፡፡
• የጸጥታ አካላት ተጠርጣሪዎችን ሲይዙ የሚያሳዩት ከሥነምግባር ውጭ የሆነ አያያዝ ማኅበረሰቡ ሕግን በእጁ እንዲያጠናቅቅ በዝምታ የሚሰጥ ግብዣ ይመስላል፡፡ ሕግ የሚከበረው ሕግን አክብሮ በማስከበር ነው፡፡
• ወንጀለኛን ለሕግ አሳልፎ መስጠት እንጂ፣ በእራሳችን እርምጃ መውሰድ እና ራስን እንደ ዳኛ አድርጎ መቁጠር ሌላ የከፋ ወንጀል ነው፡፡ ዛሬ በሌላው ላይ የሚፈረደው የደቦ ፍርድ፣ ነገ የእኛንም በር ማንኳኳቱ አይቀርም፡፡
መደብደብ፤ መግደል፤ ማኅበራዊ ሚዲያዎች/በዲጂታል ስም ማጥፋት እና ለአሉታዊ ነገር ግለሰቦችን ማነሳሳት በቡድን/በደቦ በዘመቻ ስለተፈፀመ ተጠያቂነትን አያስቀርም
1. በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 15 ፤20 ፤ 24 እና 37 መሰረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገ በስተቀር ሕይወቱን አያጣም፡፡ ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ ይቆጠራል፡፡ ክብሩና መልካም ስሙ የመከበር መብት አለው፡፡ ክርክሩ ወይም ጉዳይ ለፍርድ ቤት ቀርቦ ለማስወሰን መብት አለው፡፡
2. በወንጀል ህጋችን አንቀጽ 538 እና ተከታዮቹ መሰረት በሰው ሕይወትና አካል ላይ የሚፈጸሙ በቡድን የታገዙ ጥቃቶች ከባድ ቅጣት ያስከትላሉ፡፡
3. የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ 958/2008 መሰረት በዲጂታል መድረክ የሰውን ስም ማጥፋትና የሐሰት መረጃ ማሰራጨት በጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡
4. የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ አዋጅ 1185/2012 መሰረት በማስረጃ ያልተደገፈ ማንኛውም ሰው ወንጀለኛ እያሉ መሰየም ዘመቻ ከባድ የወንጀል ተጠያቂነት አለው፡፡
ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም! የፍርድ ቤት መዶሻን በእጃችን ከመያዝ እንቆጠብ። መንግሥት የሕግ ማስከበር ቁርጠኝነቱን በተግባር ሊያሳይ፣ ማኅበረሰቡም ለሕግ ተገዥነቱን ሊያረጋግጥ ይገባል፡፡
በዚህች ምድር ስንኖር ያለ ሕግ ፍትሕ የለም፤ ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም!
በእውነት ዓምድ እንቁም!
ሚኪያስ መላክ
በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤት
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
አለሕግ alehig.com አለ ሕግ
0920666595
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
https://t.me/AleHig
14👏3
የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ጸደቀ
----------------------
(ዜና ፓርላማ ) ሚያዚያ 13፣ 2018 ዓ.ም፤ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል የስፖርት ልማት እና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጽድቋል፡፡

የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ወርቀሰሙ ማሞ ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ ሪፖርትና ውሳኔ ሀሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

የፌደራል ስፖርት ልማትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ በስፖርቱ ዘርፍ አካታች፣ አሳታፊ፣ ዘመናዊና አስተዳደራዊ የአሰራር ሥርዓት ለመዘርጋት ምቹ መደላድል ይፈጥራል ተብሏል።

በዘርፉ የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚፈታና የስፖርት መሠረተ ልማትንና ማሰልጠኛ ተቋማትን በመገንባትና የስፖርት ግብዓት አምራቾችን እንደሚያበረታታም ተገልጿል።

አዋጁ ለሃገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት የራሱን ድርሻ ሊያበረክት የሚችል፤ በዜጎች መካከል ማህበራዊ ትስስርን የሚያጎለብት እንዲሁም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን የሚያጠናክር፤ ስፖርት ነክ ወንጀሎችን በመከላከል ስፖርትን ማስፋፋት የሚያስችል ስለመሆኑም የተከበሩ ወርቀሰሙ አብራርተዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው የአዋጁን አስፈላጊት በሚመለከት አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን አፈፃፀም ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ያሏቸውን ሀሳብ አቅርበዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብረት ሸዊት ሻንካ በምክር ቤቱ አባላት ለተነሱት ሃሳቦች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

‎ስፖርት የኢትዮጵያዊያን የኩራት ምንጭ እንዲሆን ዘርፉን የያዙትን ማነቆዎች በአሰራርና ስርዓት መፍታት ያስፈልጋል ሲሉ የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት ጠቁመዋል።

‎የስፖርቱ ዘርፍ ዘመናዊ የአሰራር ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን በማድረግ በዘርፉ ለሚስተዋሉ ማነቆዎች ምላሽ የሚሰጥና ሃገሪቱ ከዘርፉ ማግኘት ያለባትን ጥቅም እንድታገኝ በማድረጉ ረገድ ጉልህ ሚና እንዳለውም ወ/ሮ ሸዊት ገልፀዋል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 1413/2018 አድርጎ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፡፡

(በ አበባው ዮሴፍ)
4
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ አቭዬሽን ሴኩዩሪቲ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ
-------------------------
(ዜና ፓርላማ) ሚያዚያ 13፣ 2018 ዓ.ም፤ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ፡፡ 

በምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡

የማሻሻያ አዋጁ በሚዘረጋቸው አሠራሮችና ቴክኖሎጂዎች መሠረት ያሉትን የደህንነት ስጋቶች የሚፈታ ስለመሆኑ በውሳኔ ሀሳቡ ተገልጿል፡፡

በዓለም አቀፍ የሲቪል አቭዬሽን ስታንዳርድና መለኪያ መሠረት የተሻለ የአቭዬሽን ሴኩዩሪቲ መገንባት የሚያስችል እንዲሁም፤ እንደ ሀገር ከዚህ በፊት የነበረውን መልካም ገጽታ ለማስቀጠል የሚያስችል ማሻሻያ አዋጅ ስለመሆኑም የተከበሩ ፈትሂ (ዶ/ር) አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ እንደ ሀገር ሲያስመዘግብ የነበረውን ከፍተኛ ውጤት ለማስቀጠል ወቅቱን የዋጀ የሕግ ማዕቀፍ በማበጀት ለዓለም ማህበረሰብ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ በቴክኖሎጂ የታገዘ አስተማማኝና ቀልጣፋ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችልም ተብራርቷል፡፡

ነባሩ አዋጅ 432/1997 ከ20 ዓመታት በላይ ያለማሻሻያ የቆየ በመሆኑ ዘመኑ ያመጣቸውን ውስብስብ ሕገ ወጥ ጣልቃ ገብ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ስለመሆኑም ተገልጿል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት በበኩላቸው የአዋጁን አስፈላጊት በሚመለከት አስተያየት ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀጣይ ገቢ አሰባሰብን ጨምሮ አፈፃፀም ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ያሏቸውን ሀሳብ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 1412/2018 አድርጎ በ 2 ተቃውሞ እና በ 2 ድምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ አጽድቋል፡፡

(በ አበባው ዮሴፍ)
www.hopr.gov.et
7🍾1
አለ ሕግ
ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ አቭዬሽን ሴኩዩሪቲ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ ------------------------- (ዜና ፓርላማ) ሚያዚያ 13፣ 2018 ዓ.ም፤ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 15ኛ መደበኛ ስብሰባ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አጸደቀ፡፡  በምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ…
አቭዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅን ማሻሻል ለምን አስፈለገ?
👇👇👇
በቀድሞ አዋጅ 432/1997 ያልተካተቱ ዓለም አቀፍ የሲቪል አቭዬሽን ድርጅት ያወጣውን የተቀጽላ 17 አስገዳጅ ስታንዳርዶችን ለማካተት

በዓለም አቀፍ ደረጃ ደህንነቱ የተጠበቀና አስተማማኝ አቭዬሽን ለመገንባት

በአየር ትራንስፖርት ስርዓቱ የሚቃጡ የሕገ ወጥ ጣልቃ ገብ ድርጊቶች፣ ባህሪያትና የአፈፃፀም ስልት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገና እየተወሳሰበ በመምጣቱ የአቭዬሽን ሴኩዩሪቲ ዘርፍ አቅምን በቴክኖሎጂ እንዲሁም በአሰራር ለማዘመን፤

ነባሩ አዋጅ ከሃያ ዓመታት በላይ ያለማሻሻያ የቆየ፤ ዘመን ያመጣቸውን ውስብስብ ህገ ወጥ ጣልቃ ገብ ድርጊቶችን ለመቆጣጠር፤

የአቭዬሽን ኢንዱስትሪውን ደህንነት ለመጠበቅ እና ለማስጠበቅ በአዋጅ 432/1997 ኃላፊነት የተሰጣቸው ባለድርሻ አካላት የስያሜ ለውጥ ያደረጉ በመሆኑ፤

የኢንዱስትሪውን ደህንነት የበለጠ አስተማማኝ ለማድረግ ሌሎች ተጨማሪ የባለድርሻ አካላት በማካተት ሥልጣንና ተግባራቸውን በህግ መደንገግ በማስፈለጉ፤ 

በዓለም አቀፍ የሲቪል አቭዬሽን ድርጅት በተደረጉ የአቪዬሽን ሴኩሪቲ ኦዲት የተለዩ የህግ ክፍተቶችን ለማሻሻል፤
(በ አበባው ዮሴፍ)
www.hopr.gov.et
4
👉 ቃብድ ✍️
ቃብድ ማለት ተዋዋይ ወገኖች ውላቸው እንዲጸናላቸው ያላቸውን ፍላጎት ለማሳየት እና ሽያጩን ለማረጋገጥ አንዱ ወገን ለሌላኛው የሚሰጠው የማስያዣ ገንዘብ ነው።

በኢትዮጵያ የውል ሕግ ሥርዓት ውስጥ ቃብድ ከመደበኛ የውል አፈጻጸም ለየት ያሉ የሕግ ውጤቶች አሉት።

1. የቃብድ የሕግ ውጤት በፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1885
እንደ ፍትሐ ብሔር ሕግ ቁጥር 1885(1) እና (2) ድንጋጌ፣ በቃብድ የታሰረ የሽያጭ ውል ከሌሎች ውሎች የሚለየው በሚከተሉት ነጥቦች ነው፦

ተቃራኒ ስምምነት እስካልተደረገ ድረስ፣ ቃብድ የሰጠው ወገን የሰጠውን ቃብድ በመተው፣ ቃብድ የተቀበለው ወገን ደግሞ የተቀበለውን ቃብድ እጥፍ አድርጎ በመመለስ ውሉን በፈቃዳቸው ማፍረስ ይችላሉ።

በቃብድ የታሰረ ውል እንደ ሌሎች መደበኛ ውሎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1776 መሠረት በግዴታ እንዲፈጸም በሕግ አይገደድም።
ይልቁንም ተዋዋዮቹ ቃብዱን በመተው ወይም እጥፍ በመመለስ ከውሉ የመውጣት የመውጫ ቀዳዳ ይሰጣቸዋል።

የቅድመ ክፍያ እና የቃብድ ልዩነት
👇👇👇✍️✍️✍️
ተከራካሪዎች የከፈሉት ገንዘብ ቃብድ ሳይሆን ለሽያጭ ዋጋው ማሟያ የተደረገ የቅድመ ክፍያ ከሆነ፣ የቃብድ ሕግ እጥፍ መመለስ ወይም ትቶ መቅረት ተፈጻሚ አይሆንም።

ቃብድ ለተዋዋይ ወገኖች ውሉን የመተው መብት የሚሰጥ ቢሆንም፣ የሚከፈለው ገንዘብ ቃብድ መሆኑንም ወይም የቅድመ ክፍያ መሆኑ በግልጽ መታወቅ አለበት።
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
ሚኪያስ መላክ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
7👏1
ለተከታታይ አምስት (5) ቀናት ከስራ የቀረ ሰራተኛ ያለማስጠንቀቂያ ከስራ ሊሰናበት ነው።

ከእረፍትና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ አንድ ሰራተኛ ለአምስት (5) ተከታታይ ቀናትና ከዚያ በላይ ከስራ የቀረ ሰራተኛን ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውልን ማቋረጥ የሚያስችል አዲስ የህግ ትርጉም ተሰጥቷል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከዚህ በፊት በሰበር መዝገብ ቁጥር 249795 ላይ አንድ ሰራተኛ በተከታታይ ከአምስት (5) ቀናት በላይ ከሥራ ከቀረ አሰሪው ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ የሥራ ውልን ማቋረጥ እንደማይችል ጠቅሶ የሕግ ትርጉም ሰጥቶ ነበር።

ሆኖም ሰበር ሰሚ ችሎቱ አሁን ላይ አሰሪው ለእያንዳንዱ ቀን ማስጠንቀቂያ ሳይሰጥ ከስራ ማሰናበት የለበትም የሚለውን የሕግ ትርጉም ሽሮታል።

በምትኩ ከእረፍቶችና ልዩ ልዩ ፍቃዶች ውጭ አንድ ሰራተኛ ለአምስት ተከታታይ የሥራ ቀናትና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ከሥራ ከቀረ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ መስጠት ሳያስፈልግ የሥራ ውሉን ማቋረጥ ይቻላል በሚል ትርጉም ተሰጥቷል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።

ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ/ም

@tikvahethiopia
12😱1
ለታክስ ከፋይነት መመዝገብ ያለባቸው እነማን ናቸው?

ማንኛውም ሰው ማንኛውንም የንግድ ሥራ ከመጀመሩ በፊት ቀደም ብሎ በታክስ ከፋይነት መመዝገብ ይኖርበታል። ለዚህም አስቀድሞ የተመዘገበ ካልሆነ በስተቀር በታክስ ሕግ መሠረት ታክስ የመክፈል ኃላፊነት ያለበት ሰው በባለሥልጣኑ ዘንድ ለመመዝገብ ማመልከት አለበት፡፡

• ለታክስ ከፋይነት መመዝገብ ያለባቸው …

 በንግድ ወይም በሙያ ሥራ (መቀጠርን ሳይጨምር) የተሰማራ ግለሰብ፣
 ቤት በማከራየት ገቢ የሚያገኝ ግለሰብ፣
 ተቀጣሪ፣
 የመንግሥት የልማት ድርጅት፣
 የመንግሥት ባለበጀት መሥሪያ ቤት፣
 መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣
 የሃይማኖት ተቋማት፣
 የንግድ ማህበር፣
 በኢትዮጵያ ነዋሪ ባልሆነ ኩባንያ በቋሚነት የሚሠራ ድርጅት፣
 የወጪ መጋራት ተጠቃሚዎች፣
 በጋራ ሃብትነት ያልተመዘገበ ሃብት ያላቸው ሰዎች፣
 ባለ ልዩ መብት፣
 በመንግሥታት መካከል የሚደረግ ስምምነት በጽሕፈት ቤት ማቋቋሚያ ስምምነት የሚቋቋም ድርጅት እንዲሁም
 የኩባንያ አክሲዮን ባለድርሻ ናቸው።
በመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ተካሄደ
‎--------------------
‎(ዜና ፓርላማ) ሚያዝያ 19፣ 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በመረጃ  ነጻነት አዋጅ ላይ ከአስረጅዎች ጋር ተወያይቷል።

የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ  ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ በውይይቱ መክፈቻ እንዳሉት በመረጃ ነጻነት ረቂቅ አዋጅ ግልጽ ያልሆኑ ሐሳቦችን በጥያቄ ተነስተው በኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ የሚሰጥበት መሆኑን አመላክተው ውይይቱን በይፋ መጀመሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ወይዘሮ ስመኝ ውቤም የአዋጁን አስፈላጊነት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገ መንግሥትና በዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች መሠረት መረጃን ሕዝቡ እንዲያገኝ ታስቦ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅ መሆኑን ገልጸዋል። 

‎በውይይቱም የቋሚ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አዝመራ አንዴሞ፣ የቋሚ ኮሚቴው አባላት፣ የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ዋና ዕንባ ጠባቂ ወይዘሮ ስመኝ ውቤ እና ሌሎች የዕንባ ጠባቂው የሥራ ኃላፊዎች ተግኝተዋል።

(በ ጋሹ ይግዛው)
www.hopr.gov.et
#የደቦ #ፍርድ ከጎዳና እስከ ዲጂታል አደባባይ #ለሕግ የበላይነት የፈጠረው ስጋት
በሀገራችን እየተለመደ የመጣው #የደቦ_ፍርድ (Mob Justice) ከጎዳና እስከ ዲጂታል መድረኮች ፍትሕን ከችሎት አውጥቶ አደባባይ ላይ በመጣል የሀገርን ገጽታና የዜጎችን ደኅንነት ከፍተኛ አደጋ ላይ ጥሎ ይገኛል፡፡ በማንኛውም ሥልጡን ማኅበረሰብ ውስጥ ፍትሕ የሚሰጠው በሕግ በተቋቋሙ የፍርድ አካላት እንጂ በቲክቶክ የዲጂታል ፍረጃ ወይም በጎዳና ስሜታዊ ስብስብ አይደለም፡፡
አለሕግ ስንል፤ አወ ሕግ ስላለ ነው፡፡ ሕግ ባለበት ሀገር ደግሞ ፍትሕ የማግኘት መብት የሁሉም ሰው ነው፡፡ በኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37 መሠረት፣ የዳኝነት ሥልጣን የፍርድ ቤት እንጂ የቲክቶክ መንደር ወይም የሰፈር ቡድን አይደለም፡፡
ችሎት ማለት ዝም ብሎ አዳራሽ ወይም ወንበር አይደለም፤ ችሎት የሥልጣን፣ የጥበብ እና የውሳኔ መፍለቂያ ነው። በሕግ ቋንቋ ችሎት ማለት፡-
1. ክርክር የሚሰማበትና የሚደመጥበት፣
2. ማስረጃ የሚመዘንበትና እውነታው የሚመረመርበት፣
3. በዳኞች አማካኝነት የመጨረሻ ሕጋዊ ውሳኔ የሚሰጥበት የተቀደሰ ሥርዓት ነው፡፡
በሕገ-መንግሥታችን አንቀጽ 20 መሠረት፣ ማንኛውም ሰው ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ የመቆጠር መብት አለው፡፡ ሆኖም ዛሬ ወንጀለኛን ማጋለጥ በሚል ሰበብ፤ የግል ቂም በቀልንና ጥላቻን ለመወጣት የሚደረጉ የዲጂታል ስም ማጥፋት ዘመቻዎች ንጹሕ ዜጎችን ለከፋ ሥነልቦናዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ እየዳረጉ ነው፡፡ በተለይ በቲክቶክ እና መሰል መድረኮች ላይ ፎሎወር እና ላይክ ለማግኘት ብቻ ፖሊስ ምርመራ ሳይጀምር ሰዎችን ማዋረድና እንደወንጀለኛ መቁጠር እንዲሁም ለጥቃት ማጋለጥ በራሱ ከባድ ወንጀል መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡
ብዙዎች በቡድን ስንሆን አንጠየቅም ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፤ ይህ ግን ትልቅ የሕግ ስህተት ነው፡፡ በወንጀል ሕጋችን መሠረት በቡድን/በደቦ ነው የፈጸምኩት የሚል ምክንያት ከቅጣት አያድንም፡፡
• የጸጥታ አካላት ተጠርጣሪዎችን ሲይዙ የሚያሳዩት ከሥነምግባር ውጭ የሆነ አያያዝ ማኅበረሰቡ ሕግን በእጁ እንዲያጠናቅቅ በዝምታ የሚሰጥ ግብዣ ይመስላል፡፡ ሕግ የሚከበረው ሕግን አክብሮ በማስከበር ነው፡፡
• ወንጀለኛን ለሕግ አሳልፎ መስጠት እንጂ፣ በእራሳችን እርምጃ መውሰድ እና ራስን እንደ ዳኛ አድርጎ መቁጠር ሌላ የከፋ ወንጀል ነው፡፡ ዛሬ በሌላው ላይ የሚፈረደው የደቦ ፍርድ፣ ነገ የእኛንም በር ማንኳኳቱ አይቀርም፡፡
መደብደብ፤ መግደል፤ ማኅበራዊ ሚዲያዎች/በዲጂታል ስም ማጥፋት እና ለአሉታዊ ነገር ግለሰቦችን ማነሳሳት በቡድን/በደቦ በዘመቻ ስለተፈፀመ ተጠያቂነትን አያስቀርም
1. በኢፌዴሪ ሕገመንግሥት አንቀጽ 15 ፤20 ፤ 24 እና 37 መሰረት ማንኛውም ሰው በሕግ ካልተደነገገ በስተቀር ሕይወቱን አያጣም፡፡ ጥፋተኛነቱ በሕግ እስካልተረጋገጠ ድረስ እንደ ንጹሕ ይቆጠራል፡፡ ክብሩና መልካም ስሙ የመከበር መብት አለው፡፡ ክርክሩ ወይም ጉዳይ ለፍርድ ቤት ቀርቦ ለማስወሰን መብት አለው፡፡
2. በወንጀል ህጋችን አንቀጽ 538 እና ተከታዮቹ መሰረት በሰው ሕይወትና አካል ላይ የሚፈጸሙ በቡድን የታገዙ ጥቃቶች ከባድ ቅጣት ያስከትላሉ፡፡
3. የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅ 958/2008 መሰረት በዲጂታል መድረክ የሰውን ስም ማጥፋትና የሐሰት መረጃ ማሰራጨት በጽኑ እስራት ያስቀጣል፡፡
4. የጥላቻ ንግግርና የሐሰት መረጃ አዋጅ 1185/2012 መሰረት በማስረጃ ያልተደገፈ ማንኛውም ሰው ወንጀለኛ እያሉ መሰየም ዘመቻ ከባድ የወንጀል ተጠያቂነት አለው፡፡
ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም! የፍርድ ቤት መዶሻን በእጃችን ከመያዝ እንቆጠብ። መንግሥት የሕግ ማስከበር ቁርጠኝነቱን በተግባር ሊያሳይ፣ ማኅበረሰቡም ለሕግ ተገዥነቱን ሊያረጋግጥ ይገባል፡፡
በዚህች ምድር ስንኖር ያለ ሕግ ፍትሕ የለም፤ ያለ ሕግ የበላይነት ፍትሕ የለም፤ ያለ ፍትሕ ደግሞ ሰላም የለም!
በእውነት ዓምድ እንቁም!
ሚኪያስ መላክ
በፌዴራል ማናቸውም ፍርድ ቤት
ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ
አለሕግ alehig.com አለ ሕግ
0920666595
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
https://t.me/AleHig
9
6🤔3