ለተወደዳችሁ የፌደራል ጠበቆች በሙሉ:-
በከሳሽ 7ቱ ጠበቆች እና በተከሳሽ ገንዘብ ሚ/ር መካከል በከፍተኛ ፍ/ቤት በፍ/መ/ቁ. 344295 ባለው የተጨማሪ እሴት ታክስ መመሪያ ቁጥር 1104/2017 ክለሳ ክርክር ፍ/ቤቱ መመሪያው በ7ቱ ጠበቆች ላይ ሳይፈጸም ታግዶ እንዲቆይ ኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም ትእዛዝ መስጠቱ ይታወቃል::🧓🏾
ገንዘብ ሚ/ር በዚህ ትእዛዝ ቅር ተሰኝቻለሁ በማለት ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ አቅርቦ የነበረ ሲሆን ጠቅላይ ፍ/ቤቱም በፍ/መ/ቁ. 294176 ጥር 08 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የከፍተኛ ፍ/ቤቱን ትእዛዝ በማጽናት የመመሪያው አፈጻጸም 7ቱን ጠበቆች አስመልክቶ ታግዶ እንዲቆይ ወስኖአል::
ጠበቃ ሀይሉ ሀሰና
በከሳሽ 7ቱ ጠበቆች እና በተከሳሽ ገንዘብ ሚ/ር መካከል በከፍተኛ ፍ/ቤት በፍ/መ/ቁ. 344295 ባለው የተጨማሪ እሴት ታክስ መመሪያ ቁጥር 1104/2017 ክለሳ ክርክር ፍ/ቤቱ መመሪያው በ7ቱ ጠበቆች ላይ ሳይፈጸም ታግዶ እንዲቆይ ኅዳር 15 ቀን 2018 ዓ.ም ትእዛዝ መስጠቱ ይታወቃል::🧓🏾
ገንዘብ ሚ/ር በዚህ ትእዛዝ ቅር ተሰኝቻለሁ በማለት ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ አቅርቦ የነበረ ሲሆን ጠቅላይ ፍ/ቤቱም በፍ/መ/ቁ. 294176 ጥር 08 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት የከፍተኛ ፍ/ቤቱን ትእዛዝ በማጽናት የመመሪያው አፈጻጸም 7ቱን ጠበቆች አስመልክቶ ታግዶ እንዲቆይ ወስኖአል::
ጠበቃ ሀይሉ ሀሰና
👍29❤7🥰5😁2🤔2
ሁሉም ሊያውቀው የሚገባ ደንብ!!
➤በግሌ የአደጋ ምላሽ ፈንደ መኖሩ ተገቢ ነው!! በተጠቃሚ ላይ ብቻ ያተኮረ ክፍያ ሆነ!ነዳጅ፣ ቴሌኮም አገልግሎት፤ የባንክ ብድር፤ ተጠቃሚዎች ላይ ያተኮሩ ሆኑ! ያው የሚቀየር ነገር ባይኖርም ማወቁ አይከፋም።
🦜ይህ ደንብ መሆን ነበረበት ወይስ አዋጅ?
➤የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ
👉የትሌኮም አገልግሎት ለድምፅና ዳታ ከማጠቀው 5% በጣም ብዙ ነው!
👉አክሲዮን ትርፍ( Dividend ) 15% ታክስ ይደረግ ተብሎ አሁን ደግሞ 1% ይክፈሉ ተብሏል::
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው አዲስ ደንብ ቁጥር 576/2018 መሰረት የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ጽህፈት ቤት በይፋ ተቋቁሟል።
በፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ በወጣው ዝርዝር መሰረት የሚከተሉት አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ተጥሏል፡
1. የባንክ ብድር፡ ከሚሰጠው የብድር መጠን ላይ 1%
2. የኢንሹራንስ አረቦን (Premium)፦ከሚሰበሰበው ክፍያ ላይ 1%
3. ዲጂታል የባንክ አገልግሎት፦ ደንበኞች ከሚከፍሉት የአገልግሎት ክፍያ ላይ 5%
4. የአየር መንገድ ትኬት (የሀገር ውስጥ)፦ በእያንዳንዱ ትኬት ላይ 100 ብር
5. የነዳጅ ሽያጭ፦ በአንድ ሊትር ነዳጅ ላይ 1 ብር
6. የቴሌኮም አገልግሎት (ድምጽና ዳታ)፦ ከሚገዛው የአየር ሰዓት ወይም የአገልግሎት ዋጋ ላይ 5%
7. ፓስፖርትና ቪዛ፦ ለእያንዳንዱ አገልግሎት 200 ብር
8. የንግድ ፈቃድ (ማውጣትና ማደስ)፦ በእያንዳንዱ አገልግሎት 200 ብር
9. የአክሲዮን ትርፍ (Dividend)፦ ከሚያገኘው የትርፍ ድርሻ ላይ 1%
10. ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ፦ ከአገልግሎት ክፍያው ላይ 5%
መንግስት ይህንን ፈንድ ያቋቋመው እንደ ድርቅ፣ ጎርፍ እና መሰል አደጋዎች ሲከሰቱ ከውጭ እርዳታ ጥገኝነት ለመውጣት እና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ይገልጻል። አተገባበሩ ግን በዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባለው ማህበረሰብ ላይ የኢኮኖሚ ጫና ማሳረፉ አይቀሬ ነው።
Via #Menur_Reshid #አለሕግ
➤በግሌ የአደጋ ምላሽ ፈንደ መኖሩ ተገቢ ነው!! በተጠቃሚ ላይ ብቻ ያተኮረ ክፍያ ሆነ!ነዳጅ፣ ቴሌኮም አገልግሎት፤ የባንክ ብድር፤ ተጠቃሚዎች ላይ ያተኮሩ ሆኑ! ያው የሚቀየር ነገር ባይኖርም ማወቁ አይከፋም።
🦜ይህ ደንብ መሆን ነበረበት ወይስ አዋጅ?
➤የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ
👉የትሌኮም አገልግሎት ለድምፅና ዳታ ከማጠቀው 5% በጣም ብዙ ነው!
👉አክሲዮን ትርፍ( Dividend ) 15% ታክስ ይደረግ ተብሎ አሁን ደግሞ 1% ይክፈሉ ተብሏል::
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው አዲስ ደንብ ቁጥር 576/2018 መሰረት የአደጋ ስጋት ምላሽ ፈንድ ጽህፈት ቤት በይፋ ተቋቁሟል።
በፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ በወጣው ዝርዝር መሰረት የሚከተሉት አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ተጥሏል፡
1. የባንክ ብድር፡ ከሚሰጠው የብድር መጠን ላይ 1%
2. የኢንሹራንስ አረቦን (Premium)፦ከሚሰበሰበው ክፍያ ላይ 1%
3. ዲጂታል የባንክ አገልግሎት፦ ደንበኞች ከሚከፍሉት የአገልግሎት ክፍያ ላይ 5%
4. የአየር መንገድ ትኬት (የሀገር ውስጥ)፦ በእያንዳንዱ ትኬት ላይ 100 ብር
5. የነዳጅ ሽያጭ፦ በአንድ ሊትር ነዳጅ ላይ 1 ብር
6. የቴሌኮም አገልግሎት (ድምጽና ዳታ)፦ ከሚገዛው የአየር ሰዓት ወይም የአገልግሎት ዋጋ ላይ 5%
7. ፓስፖርትና ቪዛ፦ ለእያንዳንዱ አገልግሎት 200 ብር
8. የንግድ ፈቃድ (ማውጣትና ማደስ)፦ በእያንዳንዱ አገልግሎት 200 ብር
9. የአክሲዮን ትርፍ (Dividend)፦ ከሚያገኘው የትርፍ ድርሻ ላይ 1%
10. ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ፦ ከአገልግሎት ክፍያው ላይ 5%
መንግስት ይህንን ፈንድ ያቋቋመው እንደ ድርቅ፣ ጎርፍ እና መሰል አደጋዎች ሲከሰቱ ከውጭ እርዳታ ጥገኝነት ለመውጣት እና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ይገልጻል። አተገባበሩ ግን በዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባለው ማህበረሰብ ላይ የኢኮኖሚ ጫና ማሳረፉ አይቀሬ ነው።
Via #Menur_Reshid #አለሕግ
👍11❤9👎1🍾1
ማስታወቂያ
ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህግ ጉዳዮች ጸሃፊ I እና የህግ ጉዳዮች ጸሃፊ II የፅሁፍ ፈተና ወስዳችሁ ለቃል ፈተና የተመረጣችሁ ስማችሁ በዚህ ዝርዝር የተጠቀሰው ለህግ ጉዳዮች ጸሃፊ I ጠዋት 2:30 እንዲሁም ለህግ ጉዳዮች ጸሃፊ II ከሰዓት 7:30 ማክሰኞ ቀን 26/05/2018 ዓ.ም ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ ለቃል ፈተና በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግቢ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህግ ጉዳዮች ጸሃፊ I እና የህግ ጉዳዮች ጸሃፊ II የፅሁፍ ፈተና ወስዳችሁ ለቃል ፈተና የተመረጣችሁ ስማችሁ በዚህ ዝርዝር የተጠቀሰው ለህግ ጉዳዮች ጸሃፊ I ጠዋት 2:30 እንዲሁም ለህግ ጉዳዮች ጸሃፊ II ከሰዓት 7:30 ማክሰኞ ቀን 26/05/2018 ዓ.ም ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ ለቃል ፈተና በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግቢ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
❤8
EFAA INVITATION FOR EXPRESSION OF INTEREST.docx
21.7 KB
EFAA Invitation for Expression of Interest – Baseline Financial & Compliance Audit
The Ethiopian Federal Advocates Association (EFAA) invites qualified and licensed audit firms to submit their Expression of Interest to conduct a Baseline Financial and Compliance Audit of the Association.
📅 Submission Deadline: February 8, 2026 (5:30 PM)
📧 Submission Email: info@efaa.et
🔗 Full details available in the attached Invitation Document.
EFAA encourages eligible firms to apply.
The Ethiopian Federal Advocates Association (EFAA) invites qualified and licensed audit firms to submit their Expression of Interest to conduct a Baseline Financial and Compliance Audit of the Association.
📅 Submission Deadline: February 8, 2026 (5:30 PM)
📧 Submission Email: info@efaa.et
🔗 Full details available in the attached Invitation Document.
EFAA encourages eligible firms to apply.
❤8
#በሰበር መዝገብ ቁጥር 236212 የፍ/ስ/ስ/ህ/ቁ. 358 በተመለከተ በሰበር ችሎት የተሰጠ አስገዳጅ የህግ ትርጉም
#ሰበር መዝገብ ቁጥር፦ 236212
#ቀን፦ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ/ም
#ዳኞች፦ ቴዎድሮስ ምህረት፣ ብርሃኑ አመነው፣ ገበየሁ ፈለቀ፣ ተሾመ ሽፈራው፣ ደረጀ አያና፣ ደጀኔ አያንሳ እና ብርቅነሽ እሱባለው (ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ሙሉ ችሎት)
#አመልካቾች፦ 1ኛ. ወ/ሮ ዘምዘም መሐመድ፣ 2ኛ. አቶ ፍቃዱ ዳባ
#ተጠሪዎች፦ 1ኛ. አቶ ሙሉጌታ ደጀኑ፣ 2ኛ. ወ/ሮ እህተማሪያም በዛብህ
የጉዳዩ አመጣጥ
የክርክሩ መነሻ በቀድሞው ወረዳ 23 ቀበሌ 15 ውስጥ የሚገኝ ቁጥሩ 033 የሆነ ቤት ነው። ጉዳዩ በተለያዩ መዛግብት ላይ የተካሄዱ ክርክሮችን ውጤት የሚመለከት ነው፦
#በመ/ቁ. 00867 ላይ በተደረገ ክርክር ቤቱ ለተጠሪዎች እንዲረከቡ ተወስኖ ነበር።
#በሌላ በኩል፣ በመ/ቁ. 68979 ላይ በተደረገ ክርክር 2ኛ አመልካች ቤቱን እንዲረከብ ተወስኖ በአፈጻጸም ተረክቧል።
#ተጠሪዎች 2ኛ አመልካች ቤቱን የተረከበበት የውሳኔ መዝገብ (መ/ቁ. 68979) እንዲሰረዝላቸው አዲስ ክስ አቅርበዋል።
#የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መጀመሪያ ላይ "በሌላ መዝገብ ላይ የተሰጠ ውሳኔ እንዲሰረዝ የሚቀርብ ክስ ተቀባይነት የለውም" በማለት ውድቅ ቢያደርገውም፣ ጉዳዩ በሰበር መዝገብ ቁጥር 104920 ታይቶ ወደ ስር ፍርድ ቤት እንዲመለስ ተደርጓል።
#በመጨረሻም የስር ፍርድ ቤት ተጠሪዎች በመ/ቁ. 00867 መብታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ፣ አመልካቾች ቤቱን እንዲያስረክቡ ወስኗል። ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ይህንን ውሳኔ ቢሽረውም፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግን የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አጽንቷል።
#የሰበር ችሎት አስገዳጅ የህግ ትርጉም
"አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ በማቅረብ መብቱን ማስከበር የሚችለው፣ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም በቂ እና አሳማኝ በሆነ ሁኔታ ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት መብቱን የሚነካ ውሳኔ ስለመኖሩ ማወቅ ባለመቻሉ የመቃወም አቤቱታ (በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት) ማቅረብ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።"
ይህ የሕግ ትርጉም የሚከተሉትን ዝርዝር ነጥቦች ያካትታል፦
1. ሶስተኛ ወገን መብቱን ለመከላከል ያለው ዋናው መንገድ ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት የመቃወም አቤቱታ ማቅረብ ነው።
2. ውሳኔው መብቱን እንደሚነካ እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው በቸልተኝነት ሳይጠቀምበት ቀርቶ፣ ውሳኔው ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ አይቻልም።
3. አዲስ ክስ ለማቅረብ ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት መቃወሚያውን ለማቅረብ ያልቻለበትን "አሳማኝ ምክንያት" ወይም "ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ" የማስረዳት ግዴታ አለበት።
ችሎቱ ይህንን የሕግ ትርጉም ለመስጠት የተገደደው ቀደም ብለው በሰበር ሰሚ ችሎት ይሰጡ በነበሩ ውሳኔዎች መካከል የነበረውን ግልጽ ቅራኔ ለመፍታት ነው።
#የቀድሞው የመጀመሪያ አቋም (ሰ/መ/ቁ. 50835)፦ አንድ ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላም ቢሆን በውሳኔው መብቱ የተነካበት ሦስተኛ ወገን በሌላ መዝገብ አዲስ ክስ አቅርቦ መብቱን ማስከበር ይችላል የሚል ነበር።
#የቀድሞው ሁለተኛ አቋም (ሰ/መ/ቁ. 67127)፦ አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ መኖሩን ሲያውቅ በዚያው መዝገብ ላይ የመቃወም አቤቱታ (በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት) ማቅረብ ከሚችል በቀር፣ ውሳኔው በአፈጻጸም ከተጠናቀቀ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ አይችልም የሚል ነበር።
#ችሎቱ መሠረት ያደረጋቸው የሕግ መርሆዎች
ችሎቱ መፍትሔ የሰጠው መሰረታዊ ጭብጥ "በአንድ መዝገብ በተሰጠ ውሳኔ መብቴ ተነክቷል የሚል ሦስተኛ ወገን፣ ውሳኔው ከተፈጸመ በኋላ በሌላ መዝገብ አዲስ ክስ ማቅረብ ይችላል ወይ?" የሚለውን ነው። ችሎቱ ለውሳኔው የሚከተሉትን ነጥቦች በምክንያትነት ጠቅሷል፦
#የውሳኔዎች አስገዳጅነት ወሰን
እንደ አጠቃላይ መርህ፣ ፍርድ ውጤት የሚኖረው በተከራካሪ ወገኖች ላይ ብቻ ነው (Res inter alios judicata)። በኢትዮጵያ ሕግም በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 5 መሠረት አንድ ውሳኔ መቃወሚያ የሚሆነው ተከራካሪዎቹ አንድ ሲሆኑ ነው።
#ፍትሕ የማግኘት መብት እና ሥነ ሥርዓታዊ ውጤታማነት
ችሎቱ በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 37(1) የተደነገገውን ፍትሕ የማግኘት መብት እና የሥነ ሥርዓት ሕጉን ወጪና ጊዜ ቆጣቢነት መርሆዎችን አገናዝቧል። ሰዎች በቂ ማስታወቂያ ሳይሰጣቸው እና ሳይሰሙ በመብታቸው ላይ የተሰጠ ውሳኔ እንዲገደዱ ማድረግ ፍትሐዊ አይደለም።
#የሕጉ ክፍተት እና አማራጭ መፍትሔዎች
የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 ሦስተኛ ወገን ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት የመቃወም አቤቱታ እንዲያቀርብ ቢፈቅድም፣ ውሳኔው ከተፈጸመ በኋላ ያለውን ሁኔታ በግልጽ አይደነግግም።
#አዲስ ክስ የማቅረቢያ ቅድመ ሁኔታ
አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ ስለመኖሩ በቸልተኝነት ሳይሆን ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም በቂ በሆነ ሁኔታ ሳያውቅ ቀርቶ ውሳኔው ከተፈጸመ፣ አዲስ ክስ ማቅረብን መከልከል ፍትሕ የማግኘት መብትን ይጥሳል። ሆኖም ይህ መብት ያልተገደበ ሳይሆን በበቂ ምክንያት ውሳኔውን ማወቅ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ የሚፈቀድ ነው።
#የችሎቱ ውሳኔ
#በሰ/መ/ቁጥር 50835 እና በሰ/መ/ቁጥር 67127 ላይ የተሰጡት ተቃራኒ አስገዳጅ የሕግ ትርጉሞች ተሻሽለዋል።
#አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ የሚችለው፣ ከአቅም በላይ በሆነ ወይም በቂ በሆነ ምክንያት ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት መብቱን የሚነካ ውሳኔ መኖሩን ማወቅ ባለመቻሉ የመቃወም አቤቱታ (በቁጥር 358 መሠረት) ማቅረብ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
#ጉዳዩን በመሰረታዊነት እንዲወስን መዝገቡ አምስት ዳኞች ወደሚሰየሙበት ችሎት ተመልሷል።
#የተጠቀሱ የሕግ ድንጋጌዎች እና የሰበር ውሳኔዎች
#የሕግ ድንጋጌዎች
የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 37(1)፤ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 5፣ 5(4)፣ 36፣ 40(2)፣ 41፣ 43፣ 358፣ 360(2)፣ 418፣ 421፣ 455፤ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 27(1/2)።
#የተሻሻሉ/የተለወጡ የቀድሞ የሰበር ውሳኔዎች፦
#ሰ/መ/ቁ. 50835 (ቅጽ 12)፦ "ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላም ሦስተኛ ወገን አዲስ ክስ ማቅረብ ይችላል" የሚል አቋም የነበረው።
#ሰ/መ/ቁ. 67127 (ቅጽ 13)፦ "ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ አይቻልም" የሚል አቋም የነበረው።
#ሌሎች የተጠቀሱ መዛግብት፦ ሰ/መ/ቁ. 122926፣ 104920፣ 56795፣ 40229፣ 93998፣ 181236፣ 210077፣ 53607
በጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አብርሀም ዮሀንስ
#ሰበር መዝገብ ቁጥር፦ 236212
#ቀን፦ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ/ም
#ዳኞች፦ ቴዎድሮስ ምህረት፣ ብርሃኑ አመነው፣ ገበየሁ ፈለቀ፣ ተሾመ ሽፈራው፣ ደረጀ አያና፣ ደጀኔ አያንሳ እና ብርቅነሽ እሱባለው (ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ሙሉ ችሎት)
#አመልካቾች፦ 1ኛ. ወ/ሮ ዘምዘም መሐመድ፣ 2ኛ. አቶ ፍቃዱ ዳባ
#ተጠሪዎች፦ 1ኛ. አቶ ሙሉጌታ ደጀኑ፣ 2ኛ. ወ/ሮ እህተማሪያም በዛብህ
የጉዳዩ አመጣጥ
የክርክሩ መነሻ በቀድሞው ወረዳ 23 ቀበሌ 15 ውስጥ የሚገኝ ቁጥሩ 033 የሆነ ቤት ነው። ጉዳዩ በተለያዩ መዛግብት ላይ የተካሄዱ ክርክሮችን ውጤት የሚመለከት ነው፦
#በመ/ቁ. 00867 ላይ በተደረገ ክርክር ቤቱ ለተጠሪዎች እንዲረከቡ ተወስኖ ነበር።
#በሌላ በኩል፣ በመ/ቁ. 68979 ላይ በተደረገ ክርክር 2ኛ አመልካች ቤቱን እንዲረከብ ተወስኖ በአፈጻጸም ተረክቧል።
#ተጠሪዎች 2ኛ አመልካች ቤቱን የተረከበበት የውሳኔ መዝገብ (መ/ቁ. 68979) እንዲሰረዝላቸው አዲስ ክስ አቅርበዋል።
#የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት መጀመሪያ ላይ "በሌላ መዝገብ ላይ የተሰጠ ውሳኔ እንዲሰረዝ የሚቀርብ ክስ ተቀባይነት የለውም" በማለት ውድቅ ቢያደርገውም፣ ጉዳዩ በሰበር መዝገብ ቁጥር 104920 ታይቶ ወደ ስር ፍርድ ቤት እንዲመለስ ተደርጓል።
#በመጨረሻም የስር ፍርድ ቤት ተጠሪዎች በመ/ቁ. 00867 መብታቸው የተረጋገጠ በመሆኑ፣ አመልካቾች ቤቱን እንዲያስረክቡ ወስኗል። ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ይህንን ውሳኔ ቢሽረውም፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ግን የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አጽንቷል።
#የሰበር ችሎት አስገዳጅ የህግ ትርጉም
"አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ በማቅረብ መብቱን ማስከበር የሚችለው፣ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም በቂ እና አሳማኝ በሆነ ሁኔታ ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት መብቱን የሚነካ ውሳኔ ስለመኖሩ ማወቅ ባለመቻሉ የመቃወም አቤቱታ (በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት) ማቅረብ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።"
ይህ የሕግ ትርጉም የሚከተሉትን ዝርዝር ነጥቦች ያካትታል፦
1. ሶስተኛ ወገን መብቱን ለመከላከል ያለው ዋናው መንገድ ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት የመቃወም አቤቱታ ማቅረብ ነው።
2. ውሳኔው መብቱን እንደሚነካ እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው በቸልተኝነት ሳይጠቀምበት ቀርቶ፣ ውሳኔው ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ አይቻልም።
3. አዲስ ክስ ለማቅረብ ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት መቃወሚያውን ለማቅረብ ያልቻለበትን "አሳማኝ ምክንያት" ወይም "ከአቅም በላይ የሆነ ሁኔታ" የማስረዳት ግዴታ አለበት።
ችሎቱ ይህንን የሕግ ትርጉም ለመስጠት የተገደደው ቀደም ብለው በሰበር ሰሚ ችሎት ይሰጡ በነበሩ ውሳኔዎች መካከል የነበረውን ግልጽ ቅራኔ ለመፍታት ነው።
#የቀድሞው የመጀመሪያ አቋም (ሰ/መ/ቁ. 50835)፦ አንድ ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላም ቢሆን በውሳኔው መብቱ የተነካበት ሦስተኛ ወገን በሌላ መዝገብ አዲስ ክስ አቅርቦ መብቱን ማስከበር ይችላል የሚል ነበር።
#የቀድሞው ሁለተኛ አቋም (ሰ/መ/ቁ. 67127)፦ አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ መኖሩን ሲያውቅ በዚያው መዝገብ ላይ የመቃወም አቤቱታ (በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 መሠረት) ማቅረብ ከሚችል በቀር፣ ውሳኔው በአፈጻጸም ከተጠናቀቀ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ አይችልም የሚል ነበር።
#ችሎቱ መሠረት ያደረጋቸው የሕግ መርሆዎች
ችሎቱ መፍትሔ የሰጠው መሰረታዊ ጭብጥ "በአንድ መዝገብ በተሰጠ ውሳኔ መብቴ ተነክቷል የሚል ሦስተኛ ወገን፣ ውሳኔው ከተፈጸመ በኋላ በሌላ መዝገብ አዲስ ክስ ማቅረብ ይችላል ወይ?" የሚለውን ነው። ችሎቱ ለውሳኔው የሚከተሉትን ነጥቦች በምክንያትነት ጠቅሷል፦
#የውሳኔዎች አስገዳጅነት ወሰን
እንደ አጠቃላይ መርህ፣ ፍርድ ውጤት የሚኖረው በተከራካሪ ወገኖች ላይ ብቻ ነው (Res inter alios judicata)። በኢትዮጵያ ሕግም በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 5 መሠረት አንድ ውሳኔ መቃወሚያ የሚሆነው ተከራካሪዎቹ አንድ ሲሆኑ ነው።
#ፍትሕ የማግኘት መብት እና ሥነ ሥርዓታዊ ውጤታማነት
ችሎቱ በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 37(1) የተደነገገውን ፍትሕ የማግኘት መብት እና የሥነ ሥርዓት ሕጉን ወጪና ጊዜ ቆጣቢነት መርሆዎችን አገናዝቧል። ሰዎች በቂ ማስታወቂያ ሳይሰጣቸው እና ሳይሰሙ በመብታቸው ላይ የተሰጠ ውሳኔ እንዲገደዱ ማድረግ ፍትሐዊ አይደለም።
#የሕጉ ክፍተት እና አማራጭ መፍትሔዎች
የፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ. 358 ሦስተኛ ወገን ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት የመቃወም አቤቱታ እንዲያቀርብ ቢፈቅድም፣ ውሳኔው ከተፈጸመ በኋላ ያለውን ሁኔታ በግልጽ አይደነግግም።
#አዲስ ክስ የማቅረቢያ ቅድመ ሁኔታ
አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ ስለመኖሩ በቸልተኝነት ሳይሆን ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ወይም በቂ በሆነ ሁኔታ ሳያውቅ ቀርቶ ውሳኔው ከተፈጸመ፣ አዲስ ክስ ማቅረብን መከልከል ፍትሕ የማግኘት መብትን ይጥሳል። ሆኖም ይህ መብት ያልተገደበ ሳይሆን በበቂ ምክንያት ውሳኔውን ማወቅ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ የሚፈቀድ ነው።
#የችሎቱ ውሳኔ
#በሰ/መ/ቁጥር 50835 እና በሰ/መ/ቁጥር 67127 ላይ የተሰጡት ተቃራኒ አስገዳጅ የሕግ ትርጉሞች ተሻሽለዋል።
#አንድ ሰው መብቱን የሚነካ ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ የሚችለው፣ ከአቅም በላይ በሆነ ወይም በቂ በሆነ ምክንያት ውሳኔው ከመፈጸሙ በፊት መብቱን የሚነካ ውሳኔ መኖሩን ማወቅ ባለመቻሉ የመቃወም አቤቱታ (በቁጥር 358 መሠረት) ማቅረብ ያልቻለ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ነው።
#ጉዳዩን በመሰረታዊነት እንዲወስን መዝገቡ አምስት ዳኞች ወደሚሰየሙበት ችሎት ተመልሷል።
#የተጠቀሱ የሕግ ድንጋጌዎች እና የሰበር ውሳኔዎች
#የሕግ ድንጋጌዎች
የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 37(1)፤ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 5፣ 5(4)፣ 36፣ 40(2)፣ 41፣ 43፣ 358፣ 360(2)፣ 418፣ 421፣ 455፤ አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 27(1/2)።
#የተሻሻሉ/የተለወጡ የቀድሞ የሰበር ውሳኔዎች፦
#ሰ/መ/ቁ. 50835 (ቅጽ 12)፦ "ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላም ሦስተኛ ወገን አዲስ ክስ ማቅረብ ይችላል" የሚል አቋም የነበረው።
#ሰ/መ/ቁ. 67127 (ቅጽ 13)፦ "ውሳኔ ከተፈጸመ በኋላ አዲስ ክስ ማቅረብ አይቻልም" የሚል አቋም የነበረው።
#ሌሎች የተጠቀሱ መዛግብት፦ ሰ/መ/ቁ. 122926፣ 104920፣ 56795፣ 40229፣ 93998፣ 181236፣ 210077፣ 53607
በጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አብርሀም ዮሀንስ
❤30