Alage ATVT College PR and Communication
1.83K subscribers
1.69K photos
14 videos
1 file
270 links
የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን
Download Telegram
በየደረጃው ያሉ የኮሌጁ አመራሮች በኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ እየለማ ያለ የአትክልትና ፍራፍሬ ማሳን ተዘዋውረው ምልከታ አደረጉ።
"""""""""""""""""""""""
በኮሌጁ ዲን ረ/ፕ መርክነህ መሰኔ የተመራ የአመራሮች ቡድን በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ የሙዝና የፓፓያ ማሳን ተንቀሳቅሶ ጎብኝቷል።

ይህ የኢንተርፕራይዝ ልማት ዘርፍ ቀደም ሲል የሙዝ ምርቱን ለኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ለኢት ፍሩት ድርጅት እና ለአካባቢ ማህበረሰብ በሽያጭ ሲያቀርብ ቆይቷል።

የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ዘርፍ የኮሌጁን የውስጥ የገቢ አቅም ለማጎልበት በአመራሩ ትኩረት ተሰጥቶ ከሚሰራባቸው የኢንተርፕራይዝ ዘርፎች ውስጥ አንዱ አካል ተደርጎ እንደሚወሰድም በመስክ ምልከታው ወቅት ተመላክቷል።

በዕለቱ-የዘርፉን የሥራ እንቅስቃሴ አስመልክቶ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ቡድን መሪ አቶ አዲሴ ኤርገኖ ለአመራሩ አጭር ገለፃ አድርገዋል።

በየደረጃው ያለ የኮሌጁ አመራር እየለማ ያለን የሙዝና ፓፓያ ማሳ ያለበትን ደረጃ ተዘዋውሮ ምልከታ ካደረገ በኃላ ለተሻለ የጋራ ስኬት በሚል ሁሉም በየዘርፍ ድጋፍና ክትትል እንዲያደርግ የኮሌጁ ዲን ረ/ፕ መርክነህ መሰኔ የሥራ ክፍፍል መመሪያ ሰጥተዋል።

የአላጌ ግ/ቴ/ሙ/ሥ/ኮሌጅ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም
Telegram :👇
https://t.me/Alageprandcommunication
Facebook :👇
https://facebook.com/alageprandcommunication
Tiktok:👇
http://tiktok.com/@alage.atvt.college
WhatsApp:👇
https://whatsapp.com/channel/0029VbC7wgXF6smvri9Klb3n
Twitter /X:👇
https://x.com/2018Alage43959
👍2