Legal Aid
1.58K subscribers
657 photos
7 videos
57 files
182 links
⚖ Legal Aid: Your essential hub for legal professionals and students! Stay updated on new laws, landmark judgments, vacancies, and key insights. Join us to empower your legal journey and connect with the community! 📚✹"
Download Telegram
⚖ ወሳኝ ዹሰበር ዉሳኔ መ.ቁ 208644
‱ በወንጀል ጉዳይ ዹሚቀርበው ማሔሚጃ በማሔሚጃነቔ áŠ„áŠ•á‹łá‹­á‰€áˆ­á‰„ በህግ በልዩ ሁኔታ ካልተኚለኚለ በቀር ሔለ ዔርጊቱ á‰ á‰€áŒ„á‰łáˆ ሆነ በተዘዋዋáˆȘ ሊያሚጋግጄ ዚሚቜል ማናቾውም ማሔሚጃ ሊቀርቄ ይቻላል.
* አንዔን ዹቀሹበ ዹወንጀል ክሔ ለማሚጋገጄ ዚሚያሔቜሉቔን ማሔሚጃዎቜ ዚመለዚቔ ኄና ዹመወሰን áˆ”áˆáŒŁáŠ‘ ዚዓቃቀ ሕግ በመሆኑ ክሱን á‹«áˆšáŒ‹áŒáŒĄáˆáŠ›áˆ ያላ቞ውን ማሔሚጃዎቜ ኄሔካቀሚበ ዔሚሔ á‹šá‰€áˆšá‰Ąá‰” ማሔሚጃዎቜ በኄርግጄም ክሱን በህግ በተቀመጠው á‹šáˆ›áˆ”áˆšá‹łá‰” ደሹጃ á‹šáˆšá‹«áˆšáŒ‹áŒáŒĄ መሆን ያለመሆና቞ው ኹሚመዘን በቀር አንዔን ዚማሔሚጃ አይነቔ ለይቶ “ካላቀሚቄክ” ተቄሎ ዚሚገደዔበቔ ዹህግ áŠ áŒá‰Łá‰„ ዹለም.
*ቄዙ ጊዜ ፍርዔ ቀቶቜ ዹግል ተበዳይ በምሔክርነቔ ካልቀሚበ ኄንá‹Čሁም በአካል ላይ ለሚፈፀሙ ወንጀሎቜ ዹሕክምና ማሔሚጃ ካልቀሚበ ዹሚል ዹተሳሳተ አቋም በመያዝ ቔዕዛዝ ይሰጣሉ.

ዹ኱.ፌ .ዮ .áˆȘ ህገ መንግሔቔ አንቀፅ 19(5) ኄና ዹወንጀል ህግ ሄነሄርዓቔ ቁጄር133,134, 137,141,149
👍3❀1
ዚምሔራቜፊ ዚደብቄ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ክልል á‹šá‹łáŠžá‰œ አá‹Čሔ ዚጄቅማጄቅም መመáˆȘያ ጾደቀ!
####
​በደብቄ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ክልል ዹሚገኙ ዚፍቔህ አካላቔ áˆČáŒ á‰Łá‰ á‰á‰” ዹነበሹው ዚጄቅማጄቅም ማሻሻያ በይፋ ሔራ ላይ መዋሉ ተሹጋግጧል፱ ይህ መመáˆȘያ ኹክልል ኄሔኚ ወሹዳ ያሉ ዚፍርዔ ቀቔ ዚሔራ áŠƒáˆ‹áŠá‹Žá‰œáŠ•áŁ á‹łáŠžá‰œáŠ• ኄና á‰ áŒ‰á‰ŁáŠ€á‹ á‹šáˆšá‰°á‹łá‹°áˆ© á‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œáŠ• ሁሉ ዚሚያካቔቔ ነው፱
​ ዚካá‰Čቔ 16/2018 ዓ.ም በተካሄደው ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርዔ ቀቔ á‹łáŠáŠá‰” áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ ዋና áŒ‰á‰ŁáŠ€ 6ኛ ዙር 8ኛ መደበኛ áˆ”á‰„áˆ°á‰Łáą
​በጠቅላይ ፍርዔ ቀቱ ምክቔል á•áˆŹá‹á‹łáŠ•á‰” ክቡር አቶ አንዷለም አምባዬ áŠ á‰…áˆ«á‰ąáŠá‰” á‰ áŒ‰á‰ŁáŠ€á‹ ፀዔቋል
​መመáˆȘያው በዞን ኄና በáˆȘጂዼ ፖሊሔ ኚተሞቜ ለሚገኙ ሁሉም ዚፍቔህ አካላቔ á‰°áˆ°áˆ«áŒ­á‰·áˆáą
​ ዹክልሉ ጠቅላይ ፍርዔ ቀቔ በቀን 20/06/2018 ዓ.ም በጻፈው ደቄዳቀ áˆ˜áˆ°áˆšá‰”áŁ ክፍያው ኚዚካá‰Čቔ ወር መጀመáˆȘያ ጀምሼ á‰łáˆ”á‰Š ዹሚፈጾም ይሆናል፱
â€‹á‹šá‹łáŠžá‰œáŠ• ኄና á‹šá‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œáŠ• ዹኑሼ ሁኔታ á‰ áˆ›áˆ»áˆ»áˆáŁ ዚፍቔህ ሔርዓቱ በነጻነቔ ኄና በቄቃቔ ኄንá‹Čሰራ ለማገዝ á‰łáˆ”á‰Š ዹተዘጋጀ ነው፱
​"ፍቔህ በነጻነቔ ኄንዔቔሰፍን á‹šá‹łáŠžá‰œ ጄቅማጄቅም መኹበር መሰሹታዊ ኄርምጃ ነው!"
​#ደብቄ_áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« #ዚፍቔህ_ሔርዓቔ #á‹šá‹łáŠžá‰œ_ጄቅማጄቅም #áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« #SouthEthiopia #JudiciaryReform #EthiopiaNews
👍3❀1👏1
ውሳኔ ለመሔጠቔ በሚል ጉቩ በመቀበል ዚተጠሚጠሚቜ ዚፍርዔ ቀቔ ዳኛ ተኚሰሰቜ

አá‹Čሔ አበባ፣ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 10፣ 2018 (ኀፍ ኀም áˆČ) ዚፍቔህ ሚኒሔ቎ር ዚሙሔና áŒ‰á‹łá‹źá‰œ ዳáˆȘáŠ­á‰¶áˆŹá‰” ዐቃቀ ሕግ ዚፌዎራል ዹመጀመáˆȘያ ደሹጃ ፍርዔ ቀቔ ዳኛ ዚሆነቜውን ቎ዎቄሔቔያ ጌታቾው (ዚቀዔሞ ሔሟ ቃልáŠȘዳን) ላይ ዚሙሔና ወንጀል ክሔ መሰሹተ፱

ተኹሳሿ ዚሙሔና ወንጀሎቜን ለመደንገግ ዹወጣውን አዋጅ ቁጄር 881/2007 አንቀፅ 9 ንዑሔ ቁጄር 1 (ሀ) ኄና ቁጄር (2) ሔር ዹተመላኹተውን ዔንጋጌ መተላለፏን ጠቅሶ ዐቃቀ ሕግ ዝርዝር ክሔ አቅርቧል፱

á‰°áŠšáˆłáˆœ ዚፌደራል ዹመጀመáˆȘያ ደሹጃ ፍርዔ ቀቔ አá‹Čሔ ኹተማ ምዔቄ 1ኛ ዚቀተሰቄ ቜሎቔ ዳኛ ሆና ሔቔሰራ ተገቱ ያልሆነ ጄቅም ለማግኘቔ በማሰቄ በሔራ ኃላፊነቷ á‹šá‰°áˆ°áŒŁá‰”áŠ• áˆ„áˆáŒŁáŠ•áŠ“ á‹šá‰°áŒŁáˆˆá‰Łá‰”áŠ• አደራ ወደ ጎን በመተው ውሳኔ ለመሔጠቔ ጉቩ ጠይቃ ዚተቀበለቜውን ገንዘቄ áŠ„áŠ•á‹łáˆ”á‰€áˆ˜áŒ á‰œ ኄጅ ኹፍንጅ መያዟን በክሱ ዝርዝር ላይ ተገልጿል፱

በዚህ መሰሚቔ ተኹሳሿ á‹šáˆ›á‹­áŒˆá‰Łá‰”áŠ• ጄቅም ለማግኘቔ በማሰቄ በሁለቔ ተኚራካáˆȘ ግለሰቊቜ መካኚል በቜሎቔ በነበሹው ዹባልና ሚሔቔ ንቄሚቔ ክርክር ላይ አመልካቜ ንቄሚቱ በግሌ ያፈራሁቔ ነው በሚል ያቀሚበቜውን አቀቱታ ተጠáˆȘ ያመነ በመሆኑ ክሔ መሔማቔ áˆłá‹«áˆ”áˆáˆáŒ ውሳኔ ለመሔጠቔ በዚካá‰Čቔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሼ ይዛ áŠ„á‹«áˆˆáŁ በቀጠሼ ቀን አመልካቜ በቜሎቔ ሔቔቀርቄ á‰°áŠšáˆłáˆœ አመልካቜን "ዹአንá‰ș ጉዳይ በቱሼ ነው ዹሚታዹነው" በማለቔ በቱሼ ኄንዔቔቀርቄ ማዔሚጓ በክሱ ላይ á‰°áˆ˜áˆ‹áŠ­á‰·áˆáą

በዚህ መልኩ ተኹሳሿ በቱሼ ባለጉዳይዋን ኄንዔቔቀርቄ ካደሚገቜ በኋላ áŒ‰á‹łá‹© ላይ ውሳኔ ለማሔጠቔ 600 áˆșህ ቄር ኄንዔቔኚፍላቔ ዚጠዚቀቻቔ ኄና አመልካቜም ይህንን ያህል ገንዘቄ ዹመክፈል አቅም ኄንደሌለቔ ሔቔገልጜላቔ 'ኄሔበሜበቔ ነይ" በማለቔ በሚቀጄለው ቀን በቱሼ ኄንዔቔቀርቄ ዚቀጠሚቻቔ መሆኑ በክሔ ዝርዝሩ ላይ ሰፍሯል፱

በዚህም አመልካቜ áŒ‰á‹łá‹©áŠ• á‰Łáˆˆá‰€á‰· ለሆነው ግለሰቄ በማሳወቋ á‰Łáˆˆá‰€á‰·áˆ ምንም አይነቔ ገንዘቄ áŠ„áŠ•á‹łá‰”áŠšááˆ በመምክር አመልካቜ በቀጠሼ ቀን በዔጋሚ በቱሼ ሔቔቀርቄ á‰°áŠšáˆłáˆœ ዚጠዚቅቜውን ገንዘቄ áŠ áˆ˜áŒŁáˆœ ወይ ቄላ በመጠዹቅ አመልካቜም ገንዘቡን መክፈል ኄንደማቔቜል በምቔጠልጜበቔ ጊዜ á‰°áŠšáˆłáˆœ ዳኛ በመጚሚሻም 100 áˆșህ ቄር ኄንዔቔኚፍል በመጠዹቅና ዹተጠቀሰውን ገንዘቄ ለመቀበል በመሔማማቔ በዚካá‰Čቔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ዹግል ተበዳይ ገንዘቡን ይዛ áˆ”á‰”áˆ˜áŒŁ ውሳኔው áŠ„áŠ•á‹°áˆšáˆ°áŒŁá‰” መናገሯ á‰°áŒ á‰…áˆ·áˆáą

ኹዚህም በኋላ አመልካቜም አሔቀዔማ ለህግ áŠ áˆ”áŠšá‰ŁáˆȘ አካላቔ á‰Łáˆłá‹ˆá‰€á‰œá‹ መሰሚቔ á‰ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 01 ቀን 2018 ዓ.ም ዹተጠዹቀውን 100 áˆșህ ቄር áˆˆá‰°áŠšáˆłáˆœ በቱሼዋ በመሔጠቔ á‰°áŠšáˆłáˆœáˆ ገንዘቡን ተቀቄላ á‰Łáˆ”á‰€áˆ˜áŒ á‰œá‰ á‰” ቅጜበቔ ኄጅ ኹፍንጅ ዚተያዘቜ መሆኑን በመጄቀሔፀ ተኹሳሿ ያላቔን á‹šá‹łáŠáŠá‰” áˆ”áˆáŒŁáŠ• á‹«áˆˆáŠ áŒá‰Łá‰„ በመጠቀም áˆ”áˆáŒŁáŠ•áŠ• á‹«áˆˆáŠ áŠ áŒá‰Łá‰„ መገልገል ኚባዔ ዚሙሔና ወንጀል ፈጜማለቜ áˆČል ዐቃቀ ሕግ ክሱን አቅርቧል፱

በተጹማáˆȘም በወንጀለኛ መቅጫ ሔነ ሔርዓቔ ሕግ ቁጄር 113 ንዑሔ ቁጄር (1) መሰሚቔ በአማራጭነቔ ሌላኛውን ማለቔም ዚሙሔና ወንጀሎቜን ለመደንገግ ዹወጣውን አዋጅ ቁጄር 881/2007 አንቀፅ 11 ንዑሔ ቁጄር (2) ሔር ዹተመለኹተውን ዔንጋጌ ጠቅሶ ዹወንጀል ዔርጊቱን አካቔቶ ዝርዝር ክሔ አቅርቩባታል፱

á‰°áŠšáˆłáˆżá‰œ በፌደራል ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ልደታ ምዔቄ 5ኛ ወንጀል ቜሎቔ ቀርባ á‹šá‰°áˆ˜áˆ°áˆšá‰°á‰Łá‰” ዚክሔ ዝርዝር ኄንá‹Čá‹°áˆ­áˆłá‰” ተደርጓል፱

በታáˆȘክ አዱኛ
❀4
''ዹግል áˆ†áˆ”á’á‰łáˆŽá‰œ/ማህበራቔ ህዝባዊ ዔርጅቔ ሆነው በሙሔና አዋጅ 881/2007 ሔር ይገባሉ"!!

ዚጄያቄዎ ዋና ይዘቔ á‰ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ውሔጄ ዚሙሔና ወንጀል ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ቁጄሚሰ 881/2007 ወይም ተመሳሳይ አዋጅ) አንዔ ዔርጅቔ ህዝባዊ ዔርጅቔ (Public Organization) ሆኖ ይቆጠራል ወይሔ አይቆጠርም በሚለው ላይ ዚፌደራል ጠቅላይ ፍርዔ ቀቔ ሰበር ሰሚ ቜሎቔ ዹሰጠውን ዹሰበር ውሳኔ áˆ˜áˆšá‹łá‰” ነው፱

ይህ ጉዳይ በአዋጅ ቁጄር 881/2015 (ዚሙሔና ወንጀሎቜ አዋጅ) አንቀጜ 2(5) ላይ ዹተመሰሹተ ነው፱

አዋጁ ህዝባዊ ዔርጅቔን ኄንá‹Čህ á‹­áŒˆáˆáŒ»áˆáĄ-

áŠšáŠ á‰Łáˆ‹á‰” ወይም ኚህዝቄ በማንኛውም መንገዔ áŒˆáŠ•á‹˜á‰„áŁ ንቄሚቔ ወይም ሌላ ሃቄቔ ዚሚሰበሔቄና á‹šáˆšá‹«áˆ”á‰°á‹łá‹”áˆ­ ዹግል ዘርፍ አካል (ኩባንያ ወይም ዔርጅቔ)፱
ይህ ማለቔ ቄዙ ዹግል áŠ©á‰ŁáŠ•á‹«á‹Žá‰œáŁ áˆ›áˆ…á‰ áˆ«á‰”áŁ áŠźáŠŠá•áˆ«á‰Čቭሔ ወይም áˆ†áˆ”á’á‰łáˆŽá‰œ (በተለይ ኚህዝቄ ገንዘቄ á‹šáˆšáˆ°á‰ áˆ”á‰Ą) በዚህ ህግ ሔር ሊገቡ á‹­á‰œáˆ‹áˆ‰áą

ይህም በግል ዘርፍ ዹሚፈጾሙ ዚሙሔና ወንጀሎቜን (ቄልáˆč áŒáŠ•áŠ™áŠá‰”áŁ áˆ”áˆáŒŁáŠ• መጠቀም፣ ገንዘቄ መቀበል ወዘተ) ለመቆጣጠር ያለመ ነው፱

* ዹሰበር ውሳኔ áˆáˆłáˆŒá‹Žá‰œ ኄና አቀራሚቄ

ዚፌደራል ጠቅላይ ፍርዔ ቀቔ ሰበር ሰሚ ቜሎቔ በዚህ ጉዳይ ላይ በተለያዩ áŒ‰á‹łá‹źá‰œ ላይ ውሳኔ áˆ°áŒ„á‰·áˆáą በተለይ አንዳንዔ á‹áˆłáŠ”á‹Žá‰œ (በተለይ áˆ†áˆ”á’á‰łáˆ ወይም ተመሳሳይ ዔርጅቶቜን በተመለኹተ) በአቄላጫ ዔምጜ ዔርጅቱን ህዝባዊ ዔርጅቔ ቄሎ á‹­á‰†áŒ„áˆ«áˆáą

ይህም ማለቔ በዚህ ህግ ሔር ሰራተኞá‰č/áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹łáˆȘዎá‰č በሙሔና ወንጀል ሊጠዹቁ á‹­á‰œáˆ‹áˆ‰áą

* ዹውሳኔው ዋና ይዘቔ (ኹኩፊሮላዊ áˆ›áŒŁá‰€áˆ» á‰ áˆ˜á‹áŒŁá‰”)
- áŒ‰á‹łá‹©áĄ በሐሹር ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ዹጀመሹ ዹወንጀል ክርክር (ዚሙሔና ወንጀል ክሔ)፱ ተጠáˆȘዎቜ (ኄነ ቀተልሄም ጌቱ አለሙ ኄና ሌሎቜ) á‰ áˆ†áˆ”á’á‰łáˆ‰ áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ ውሔጄ ዚተሰማሩ áˆČሆኑ፣ ዚተኚሰሱቔ በአዋጅ 881/2015 መሰሚቔ ዚሙሔና ወንጀሎቜ (ኄምነቔ ማጉደል፣ ቄልáˆč ግንኙነቔ ወዘተ) ነው፱

- ዹሰበር ውሳኔ፡ በአቄላጫ ዔምጜ (majority) áˆ†áˆ”á’á‰łáˆ‰/ማህበሩ áŠšáŠ á‰Łáˆ‹á‰” ኄና ኚህዝቄ በተሰበሰበ ገንዘቄ/አክáˆČዼን ዹተቋቋመ በመሆኑ ህዝባዊ ዔርጅቔ ተቄሎ á‰°á‰†áŒ„áˆŻáˆáą ሔለዚህ áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹łáˆȘዎá‰č/ሠራተኞá‰č በዚህ አዋጅ ሔር በሙሔና ወንጀል ሊጠዹቁ á‹­á‰œáˆ‹áˆ‰áą

- ዚልዩነቔ áˆ€áˆłá‰„ (Dissenting Opinion)፡ አንዔ ዳኛ ተቃውሞ áˆ°áŒ„á‰·áˆáą አዋጁ በግል ዘርፍ ላይ á‰ąá‹«á‰°áŠ©áˆ­áˆáŁ ህዝባዊ ዔርጅቔ ለመሆን በምንጭ (source) ኄና ዓላማ (purpose) መሞኹር አለበቔ ቄሎ á‰°áŠšáˆ«áŠ­áˆŻáˆáą ሆኖም አቄላጫው ቜሎቔ ውሳኔውን á‰°á‰€á‰„áˆáˆáą
❀5
⚖ ​በሔርቆቔ ወንጀል አንዔ á‰°áŠšáˆłáˆœ "ሰርቋል" ለመባል ንቄሚቱን áˆ˜áŠ•áŠ«á‰”áŁ መቁሚጄ...ወዘተ ቄቻውን በቂ ነውን? ወይንሔ ንቄሚቱ ዚግዔ ወደ ተኹሳáˆč ይዞታ áˆ˜áŒá‰Łá‰” አለበቔ?
*

ዚፌደራል ጠቅላይ ፍርዔ ቀቔ ሰበር ሰሚ ቜሎቔ በመዝገቄ ቁጄር 230945 ለዚህ ጄያቄ ምላሜ áˆ°áŒ„á‰·áˆáą
​🔍 ዹይዞታ ለውጄ (Possession) ኄና ሔርቆቔ
​በወንጀል ህግ አንቀፅ 665 áˆ˜áˆ áˆšá‰”áŁ ሔርቆቔ ዹሚፈፀመው አንዔን ዕቃ አንሔቶ በመውሰዔ (Taking away) ኄና በራሔ ይዞታ ሔር በማዔሚግ ነው፱ ይህ ማለቔፊ
​ንቄሚቱ áŠšá‰Łáˆˆá‰€á‰± ቁጄጄር áˆ˜á‹áŒŁá‰” áŠ áˆˆá‰ á‰”áą ​ንቄሚቱ ወደ ወንጀል አዔራጊው ይዞታ áˆ˜áŒá‰Łá‰” áŠ áˆˆá‰ á‰”áą
​📍 ዚሰበሩ ክርክርና ውሳኔ
​በዚህ መዝገቄ ላይ ተኹሳáˆč ዚኀሌክቔáˆȘክ ፖል (ምሶሶ) ቄሚቔን በመጋዝ áˆČቆራርጄ ኄጅ ኹፈንጅ ተይዟል፱
â€‹á‹šá‰ á‰łá‰œ ፍርዔ ቀቶቜ áŠ„á‹­á‰łáŠ ቄሚቱን ለመሔሚቅ መቁሚጄ መጀመሩ "ፍፃሜ ያገኘ ሔርቆቔ" ነው በሚል ጄፋተኛ አዔርገውቔ ነበር፱
​ዹሰበር ሰሚ ቜሎቔ ቔርጉምፊ ተኹሳáˆč ቄሚቱን ኄዚቆሚጠ ኄንጂ አንሔቶ አልወሰደም፱ ንቄሚቱ ገና ኚምሶሶው ተለይቶ ወደ ተኹሳáˆč ቁጄጄር (ይዞታ) አልገባም፱
​💡 ዋናው ዹህግ ነጄቄ
​ዔርጊቱ በቆሹጣ ላይ ኄያለ መቋሹጡ፣ ዹይዞታ ለውጄ (Change of Possession) áŠ„áŠ•á‹łáˆá‰°áŠšáŠ“á‹ˆáŠ á‹«áˆłá‹«áˆáą በመሆኑም፩
​ንቄሚቱ ወደ ተኹሳáˆč ኄጅ áŠ«áˆáŒˆá‰Ł ዔርጊቱ "ዚሔርቆቔ ሙኚራ" (Attempt) ኄንጂ ፍፃሜ ያገኘ ወንጀል ሊባል áŠ á‹­á‰œáˆáˆáą
​በመሆኑም ተኹሳáˆč በወንጀል ህግ አንቀፅ 27(1) ኄና 669(1)(ለ) መሠሚቔ በሔርቆቔ ሙኚራ ቄቻ ሊቀጣ ይገባል áˆČል á‹ˆáˆ”áŠ—áˆáą

​📱 ማጠቃለያፊ አንዔን ንቄሚቔ ለመሔሚቅ áˆ˜áˆ°áŠ“á‹łá‰” ወይም ንቄሚቱን ለመውሰዔ ዚሚያሔቜል ተግባር ላይ ኄያሉ መያዝ (ለምሳሌ፡ áˆ˜á‰áˆšáŒ„áŁ áˆ˜áá‰łá‰”...) ነገር ግን ንቄሚቱን ሙሉ በሙሉ በቁጄጄር ሔር አውሎ አለመውሰዔ በህጉ በ"ሙኚራ" ደሹጃ á‹šáˆšá‹«áˆ”á‰€áŒŁ ተግባር ነው፱
❀6
ዹፊንቮክ áŠąáŠ•á‰šáˆ”á‰”áˆ˜áŠ•á‰” ሔራ አሔáŠȘያጅ ተኹሰሰ

አá‹Čሔ አበባ፣ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 18፣ 2018 (ኀፍ ኀም áˆČ) ተፅዕኖ ፈጣáˆȘዎቜን áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹« በማሔነገር ዚኀሌክቔáˆȘክ ተሜኚርካáˆȘዎቜ áŠ„áŠ“áˆ”áˆšáŠ­á‰ŁáˆˆáŠ• በማለቔ ኹ600 ሚሊዹን ቄር በላይ áŠšá‰°á‰ á‹łá‹źá‰œ ዹሰበሰበው ፊንቮክ áŠąáŠ•á‰šáˆ”á‰”áˆ˜áŠ•á‰” ሔራ አሔáŠȘያጅ ዹሆነው á‹łáŠ•áŠ€áˆ á‹źáˆáŠ•áˆ” ክሔ á‰°áˆ˜áˆ”áˆ­á‰¶á‰ á‰łáˆáą

á‰°áŠšáˆłáˆœ በ1996 ዓ.ም ዹወጣውን ዹወንጀል ህግ አንቀፅ 32 ቁጄር 1 ሀ ኄና ለ ኄንá‹Čሁም አንቀጜ 35፣ 38 ኄንá‹Čሁም ዹኼምፒውተር ወንጀል አዋጅ ቁጄር 958/2008 አንቀፅ 10 ቁጄር 1 ሔር ዹተደነገገውን በመተላለፍ ነው ክሔ á‹šá‰°áˆ˜áˆ°áˆšá‰°á‰ á‰”áą

á‰°áŠšáˆłáˆœ ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣáˆȘዎቜ ጋር በመሆን ኼምፒውተርን ወይም ዹኼምፒውተር ሔርዓቔን በመጠቀም áŠ áˆłáˆłá‰œ ዳታ á‰ áˆ›áˆ°áˆ«áŒšá‰”áŁ á‹šáˆ«áˆłá‰žá‹áŠ• በመሰወር ወይም መግለፅ ዹሚገባቾውን ነገር በመደበቅ ወይም ዹሌላውን ሰው ዹተሳሳተ ኄምነቔ በመጠቀም፣ ሌላውን ሰው አታልለው ዹተበዳይን ጄቅም ዹሚጎዳ ዔርጊቔ ኄንá‹Čፈፀም ለማዔሚግ በማሰቄ ወንጀል ለመፈፀም á‰Łá‹°áˆšáŒ‰á‰” ሔምምነቔ መሰሚቔ ዹወንጀል ዔርጊቔ መፈጾማቾውን ዐቃቀ ሕግ በክሔ ዝርዝሩ ላይ áŠ áˆ˜áˆáŠ­á‰·áˆáą

በዚህም á‰°áŠšáˆłáˆœ በ2013 ዓ.ም በመጀመáˆȘያ ሄሎ ታክáˆČ ኄና ሄሎ መáŠȘና á‹šá‰°á‰Łáˆ‰á‰”áŠ• ዔርጅቶቜ ካቋቋመ በኋላ ዔርጅቱ ዹታክáˆČ ሄራን ለማዘመን ዘመናዊ መáŠȘኖቜን ኹሀገር ውሔጄ áŠ á‰…áˆ«á‰ąá‹Žá‰œ ኄና ኹውጭ ሀገር á‰ áˆ›áˆ”áˆ˜áŒŁá‰” ኄንá‹Čሁም በመገጣጠም በመንገዔ ኄና ቔራንሔፖርቔ á‰Łáˆˆáˆ”áˆáŒŁáŠ• (ሚኒሔ቎ር) ባወጣው መመáˆȘያ መሰሚቔ አሁን ያለውን ዚቔራንሔፖርቔ ቜግር áˆˆáˆ˜áá‰łá‰” ለታክáˆČ ፈላጊዎቜ ዘመናዊ ታክáˆČ በዱቀ áŠ„áŠ“á‰€áˆ­á‰ŁáˆˆáŠ• በሚል áŠ áˆłáˆłá‰œ መሚጃዎቜን አሰራጭተዋል ቄሏል á‰ áŠ­áˆ±áą

በመሹጃው መሰሚቔ ኹ5 áˆșህ በላይ ዹሚሆኑ ግለሰቊቜ á‰°áŠšáˆłáˆœ ኄና á‹šá‰°áŠšáˆłáˆœ ዔርጅቔ በተለያዩ á‰ áˆ˜áŠ•áŒáˆ„á‰”áŁ በግል ኄና ማህበራዊ ሚá‹Čያዎቜ ዚተሰራጚውን áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á‹Žá‰œáŠ• በመመልኚቔ ወደ ዔርጅቱ ዚሄዱ ዹግል á‰°á‰ á‹łá‹źá‰œ በዱቀ áˆ°áˆ­á‰łá‰œáˆ ቔርፋማ ዚምቔሆኑበቔን ታክáˆČ ገንዘቡን በኚፈላቜሁቔ በ3 ወር ውሔጄ áŠ„áŠ“áˆ”áˆšáŠ­á‰Łá‰žá‹‹áˆˆáŠ• በማለቔ 60 áˆșህ ቄር áˆˆáˆ˜áˆ˜á‹áŒˆá‰ąá‹«áŁ ኹመáŠȘናው ጠቅላላ ዋጋ 25 በመቶ ወይም 247 áˆșህ 500 ቄር በዔርጅቱ አካውንቔ ላይ ገቱ ኄንá‹Čያደርጉ በማዔሚግ ዹግል á‰°á‰ á‹łá‹źá‰œ ኄምነቔ ኄንá‹ČáŒ„áˆ‰á‰Łá‰œá‹ ለማዔሚግ ኄና በሹቀቀ መንገዔ ወንጀሉን ለመፈፀም ኄንá‹Čያመቻ቞ው ውል በማርቀቅ ኄና በዔርጅቱ በተሹቀቀው ውል ላይ ኄንá‹Čፈርሙ ማዔሚግ ዹሚል በክሱ ላይ ተገልጿል፱

ኹዚህ በተጹማáˆȘ ዹመáŠȘኖቻቜውን ሻንáˆČ ኄና ሞተር ቁጄር áˆ”áˆˆáˆ˜áŒŁ ፈርማቜሁ ውሰዱ በማለቔ ኹሄሎ ታክáˆČ ኹሚል ዔርጅቔ ዹሞተር ኄና ሻንáˆČ ቁጄር ላይ ፈርመው ኄንá‹Čወሔዱ ካደሚገ በኋላ ኹ600 ሚሊዹን ቄር በላይ ተቀቄሎ መáŠȘናውን áˆłá‹«áˆ”áˆšáŠ­á‰„ ዔርጅቱን ዘግቶ መሰወር በክሱ ላይ ኚተነሱ áŒ‰á‹łá‹źá‰œ መካኚል ነው፱

ኄንá‹Čሁም á‰°áŠšáˆłáˆœ ግርማይ ገ/ሚካኀል ኹተባለው (አሔካል ዹተባለውን ዔርጅቔ በማቋቋም በዔርጅቱ ሔም በ2002 ዓ.ም በተካሄደው ዹዓለም ዋንጫ ጹዋታ ላይ á‰ áˆ­áŠ«á‰ł áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹«á‹á‹«áŠ• ኄንá‹Čታደሙ ወደ ደብቄ አፍáˆȘካ ኄልካ቞ዋለሁ በማለቔ ቄር በመቀበል ተሰውሼ በ኱ንተርፖል ዚተያዘ) ለጊዜው ካልተያዘው ግቄሚ-አበር ጋር በመሆን ኹዚህ በፊቔ ኹላይ ዚፈፀሙቔን ኄና ኹላይ ዹተገለፀውን ወንጀል በሰፊው ለመፈፀም በሕጋዊ፣ በንግዔ ኄና ውል ሜፋን ሔም በተለምዶ ዹነጭ ኼሌታ ሳይበር áŠ á‰łáˆ‹á‹źá‰œ ዚሚፈፅሙቔ ወንጀል ለመፈፀም ኄንá‹Čያመቻ቞ው ፊንቮክ áŠąáŠ•á‰šáˆ”á‰”áˆ˜áŠ•á‰” ኃ/ዹተ/ዹግ/ማህበር ዹተባለውን ዔርጅቔ በተሜካርኚáˆȘዎቜ አሔመáŒȘáŠá‰”áŁ በተሜካርኚáˆȘዎቜ መለዋወጫፀ መቆጣጠáˆȘያ መሳáˆȘያዎቜን ኄና áŒŒáŒŁáŒŒáŒŠá‰œ አሔመáŒȘነቔ ኄና ዚተሜካርኚáˆȘዎቜ ኚአካላቔ ኄና á‰°áˆłá‰ąá‹Žá‰œ አሔመáŒȘነቔ 7 ሚሊዹን ቄር áŠ«á’á‰łáˆ በማቋቋም ኹአá‹Čሔ አበባ ንግዔ ኄና áŠąáŠ•á‹±áˆ”á‰”áˆȘ ቱሼ በግንቊቔ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ዚንግዔ ፍቃዔ á‹«á‹ˆáŒĄ መሆኑፀ á‹”áˆ­áŒ…á‰łá‰œáŠ• ዚኀሌክቔáˆȘክ መáŠȘኖቜን á‰ á‰€áŒ„á‰ł ኚቻይና ቱዋይá‹Č ኩባንያ á‰ áˆ›áˆ”áˆ˜áŒŁá‰” በጠቅላላ ዋጋ 1 ሚሊዹን 900 áˆșህ ቄር ለደንበኞቜ በ50 በመቶ ወይም 950 áˆșህ ቄር ቅዔሚያ ክፍያ ኄና ቀáˆȘው ዹ50 በመቶ በዱቀ ሜያጭ ወደ ሀገር ውሔጄ á‰ áˆ›áˆ”áŒˆá‰Łá‰” ለደንበኞቜ በማሔሚኚቄ ላይ ይገኛልፀ ማንኛውም ተቋም ያላደሚገውን ቀáˆȘውን 950 áˆșህ ቄር 50 በመቶ ያለወለዔ በ5 ዓመቔ ውሔጄ ኹፍለው ዚሚጚርሱበቔ አሰራር በመዘርጋቔ ዹመáŠȘና á‰Łáˆˆá‰€á‰” ሊያደርጋቜሁ ተዘጋጅቷልፀ ሔለዚህ ተመዝግበው በ3 ወር ውሔጄ ዹመáŠȘና á‰Łáˆˆá‰€á‰” ይሁኑ ዹሚሉ áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á‹Žá‰œáŠ• á‰ áˆ›áˆ°áˆ«á‰”áą

á‰ áŠŠáˆźáˆšá‹« ባህል ማዕኹል፣ በሔካይ ላይቔ ሆቮል፣ በመሔቀል አደባባይ ኄና á‰ á‹ˆá‹łáŒ…áŠá‰” አደባባይ áŠ„áŠ•á‹łáˆ”áˆšáŠšá‰Ą á‹šáˆšá‹«áˆłá‹­ á‰Șዔዟ ኄና ፎቶ በመልቀቅ ኄና á‰ áˆ›áˆłá‹šá‰” ኄሔካሁን ኹ450 በላይ መáŠȘኖቜን áˆˆá‰°áˆ˜á‹áŒ‹á‰ąá‹Žá‰œ ያሔሚኚበ መሆኑንፀ አሁንም ለደንበኞቻቜን ለማሔሚኚቄ ወደ 400 መáŠȘኖቜን ወደ ሀገር ውሔጄ ኄያጓጓዝን ኄናገኛለንፀ ኑ ኄና ኹፍለው ቀáˆȘውን 950 áˆșህ ቄር ያለወለዔ ኄዚኚፈሉ ዹመáŠȘና á‰Łáˆˆá‰€á‰” ይሁኑፀ ለመáŠȘናው ለ5 ዓመቔ ዋሔቔና áŠ„áŠ•áˆ°áŒŁáˆˆáŠ•á€ á‹”áˆ­áŒ…á‰łá‰œáŠ• ኹፀሐይ ኱ንáˆčራንሔ ጋር ዹ኱ንáˆčራንሔ ውል áŒˆá‰„á‰·áˆáŁ ኹባንክ ጋር አገናኝተናል” በማለቔ ዚተለያዩ áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á‹Žá‰œáŠ• በታዋቂ áŒáˆˆáˆ°á‰Šá‰œáŁ ታዋቂ አርá‰Čáˆ”á‰¶á‰œáŠ•áŁ á‰ČáŠ­á‰¶áŠšáˆźá‰œáŠ•áŁ ዚመንግሄቔ ኄና ዹግል ሚá‹Čያዎቜን ኄንá‹Čሁም á‹šáˆ«áˆłá‰žá‹áŠ• ሚá‹Čያ ጹምሼ ዚተለያዩ ማህበራዊ ሚá‹Čያዎቜን በመጠቀም áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á‹áŠ• በማሰራጚቔ á‰ áˆ­áŠ«á‰ł ሰዎቜ á‰ á‰°áŠšáˆłáˆœ ኄና á‰ á‰°áŠšáˆłáˆœ ዔርጅቔ ዚተሰራጚውን ቔርፋማ ዚምቔሆኑበቔን ዘመናዊ ዚኀሌክቔáˆȘክ መáŠȘና áŠ„áŠ“á‰€áˆ­á‰ŁáˆˆáŠ• ዹሚል አማላይ ኄና áŠ áˆłáˆłá‰œ áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á‹Žá‰œáŠ• በመመልኚቔ á‰ áˆ­áŠ«á‰ł ግለሰቊቜ ወደ ዔርጅቱ ሄደው በመመዝገቄ ቅዔመ ክፍያ 950 áˆșህ ቄር ኹኹፈሉ በኋላ á‰ áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹« ላይ ኹተነገሹው ገንዘቄ 950 áˆșህ ቄር በተጹማáˆȘ (ተጹማáˆȘ ኄሎቔ ታክáˆČ) በሚል 285 áˆșህ ቄር ኄና ለቩሎ ኄና ለታርጋ ተቄሎ ኹ130 áˆșህ ቄር ኄንá‹Čኹፍሉ አዔርገዋል áˆČል ዐቃቀ ሕግ በክሱ ዝርዝር ላይ áŠ áˆ˜áˆáŠ­á‰·áˆáą

በአጠቃላይ 1 ሚሊዹን 365 áˆșህ ቄር በማሔኚፈል በ3 ወር ውሔጄ መáŠȘና áŠ„áŠ“áˆ”áˆšáŠ­á‰ŁáˆˆáŠ• በማለቔ á‰ á‰°áŠšáˆłáˆœ ኄና á‰ á‰°áŠšáˆłáˆœ ዔርጅቔ በተሹቀቀው ውል ላይ ኄንá‹Čፈርሙ በማዔሚግ ኄንá‹Čሁም በ3 ወር ውሔጄ መáŠȘና áŠ áˆ”áˆšáŠ­á‰Łá‰žá‹‹áˆˆáˆ በማለቔ ኹ1 áˆșህ 430 በላይ ግለሰቊቜን በመመዝገቄ ኚኄያንዳንዱ ተመዝጋቱ ኚቄር 950 áˆșህ ኄሔኚ 1 ነጄቄ 86 ሚሊዹን ቄር በላይ ሰቄሔበው 100 መáŠȘኖቜን áˆˆáˆ«áˆ±áŁ ግቄሚ-አበሩ ኄና ዚጄቅም ተጋáˆȘ ለሆኑ ግለሰቊቜ ቄቻ አሔሚክቊ ሳለ በሚá‹Čያዎቜ ኹ520 በላይ መáŠȘኖቜን አሔሚክበናል በማለቔ áŠ áˆłáˆłá‰œ መሚጃዎቜን በመናገር ግለሰቊቜ ቀርበው ኄንá‹Čመዘገቡ ኄና ገንዘቄ ኄንá‹Čኹፍሉ áˆČያደርግ ነበሹ በሚል 19 á‰°á‹°áˆ«áˆ«á‰ą ክሶቜ á‰°áˆ˜áˆ”áˆ­á‰°á‹á‰ á‰łáˆáą

ዚክሔ መዝገቡን ዹተመለኹተው ዚፌዎራል ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ልደታ ምዔቄ 2ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ቜሎቔ ነው፱

በመቅደሔ ኹበደ
❀3
vacancie for lawyers
👎2❀1
ዹ2 ጠበቆቜ ወግ

አንá‹Čቔ ደምበኛዬ á‰łáˆ”áˆ« ላገኛቔ ዚፌደራል ፖሊሔ áŒŁá‰ąá‹« መሄዔ ነበሚቄኝፀ ጠበቃ ነኝ ቄዏ ልገባ ሔል ፖሊሱ ኄንደ ምሔáŠȘን á‰°áŠźáˆáŠ©áˆˆá‹ መንገዔ ዳር ኄዚጠበቁ ያሉቔን ጠበቆቜ áŠ„á‹«áˆłá‹šáŠ "ወደዛ ሂዔና ጠቄቅ " አለ áŠ„á‹«áˆ˜áŠ“áŒšá‰€áŠáą ሌላውም ፖሊሔ ይመጣና ወደዛ ራቅ በሉ ኄያለ áˆŠá‹«á‰Łáˆ­áˆ­áˆ á‹­áˆžáŠ­áˆ«áˆáą
ኚዚቔ ዹመጣ ልምዔ ኄንደሆነ አላውቅም ቄቻ ጠበቃ ለነሱ ኄንደ አንዔ ዚፍቔህ አጋር አይደለምፀ ኄንደሰው ኄንኳን ዹማይታይ ጠላቔ ነው ዚሚመሔላ቞ው (ኄርግጄ ነው ኚዐቃቀ ህጎቜም ጋር ዹ inferiority complex áŠ„áŠ•á‹łáˆˆá‰Łá‰žá‹áŠ“ ለመታዘዝ ኄንደሚያቅማሙ አውቃለሁ) ጠበቆቜ ላይ á‹šáˆšá‹«áˆłá‹©á‰” ባህáˆȘ ግን ኚቔግሔቔ በላይ ነው፱

ኄንደ አጋጣሚ ኹሰሞኑ ግርግር ጋር በተያያዘ á‹šá‰łáˆ°áˆ© አርá‰Čሔቶቜንም ኄያዚኋ቞ው ነበርፀ ኄውነቔ ነው ዹማንም á‰łáˆ«áˆš ክቄር መነካቔ á‹šáˆˆá‰ á‰”áˆáą ግን (ኄነሱ ኄንግá‹Č ታሳáˆȘ ና቞ውፀ) ኄንá‹Čያው ኄንዎቔ ኚኄነሱ ያነሰ መሔተንግዶ ሊሰጠን ይገባል?đŸ„ș(ቱ! ኹጹነቀው ሰው ጋር አነካኩኝ)

ኄዚተነጫነጭኩ ወጄቌ ሔሄዔ ሔክን ያለውን ጠበቃ ወዳጄን áŠ áŒˆáŠ˜áˆá‰”áą በጣም አንባቱና ዹተሹጋጋ አዋቂ ሰው ነውፀ በዚህ ጉዳይ ግን መሚጋጋቔ áŠ áˆá‰»áˆˆáˆáą በአንዔ ወቅቔ ኚቅንጅቔ ፓርá‰Č áŠ áˆ˜áˆ«áˆźá‰œ ኄሔር ጋር በተያያዘ አንዔ ዹቱቱáˆČ ጋዜጠኛ ፍ/ቀቔ ገቄቶ ያሔተዋለውን áŠ áˆ”á‰łá‹áˆ¶áŠ á‰°á‰„áˆ°áŠšáˆ°áŠ­áŠ•áą "á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ጠበቆቜ ፖሊሔ ኄንኳን áˆČፈልግ á‹šáˆšá‹«á‰Łáˆ­áˆ«á‰žá‹áŁ ፍ/ቀቔ ውሔጄ áŠ„áŠ•á‹°á‰°áŠšáˆłáˆœ ዹሚገላምጧቾው ምሔáŠȘኖቜ ናቾው" ነበር á‹«áˆˆá‹áą

ፍርሀተኞቜ ሔለሆንን ነው አለኝ á‹ˆá‹łáŒ„á€ ዹሳንá‰Čም ሜርፍራፊ ኄንጂ áˆ˜á‰„á‰”áŁ ክቄር ዹሚባለው ነገር ዹማይገባን ሆነናል፱

ዚሌሎቜ áŠ áŒˆáˆźá‰œ ዚጄቄቅና ማህበራቔ ኄንዎቔ áˆ˜á‰„á‰łá‰žá‹áŠ• ኄንደሚያሔኚቄሩ ታውቃለህ? áˆČል ጠዚቀኝፀ አላውቅም አልኩቔፀ ያቄራራልኝ ጀመር፱

አሜáˆȘካ (ABA Standards) በአሜáˆȘካ ጠበቃ Officer of the Court (ዚቜሎቔ መኼንን) ነው፱ በሕገ-መንግሄቱ 6th Amendment áˆ˜áˆ áˆšá‰”áŁ አንዔ ጠበቃ ደንበኛውን በፈለገው ሰዓቔ ዚማግኘቔ መቄቱ ዚማይገሚሰሔ ነው፱ ፖሊሔ ጠበቃን ካገተ ወይም ካመናጚቀ "Civil Rights Violation ተቄሎ በኚባዔ áŠ«áˆłáŠ“ በሄራ ሔንቄቔ ይጠዹቃል፱
ኄንግሊዝ (Bar Council) በኄንግሊዝ ዚጠበቆቜ ማኅበር (Bar Council) ኄጅግ ኃያል ነው፱ አንዔ ፖሊሔ በጠበቃ ላይ ተገቱ ያልሆነ ግፊቔ áŠ«áˆłá‹šáŁ ማኅበሩ ወá‹Čያውኑ ምርመራ ኄንá‹Čኚፈቔ ዚማዔሚግና ፖሊሱን ኚሄራ áŠ„áˆ”áŠšáˆ›á‰Łáˆšáˆ­ ያለ ተጜዕኖ አለው፱

ደብቄ አፍáˆȘካ (LSSA)- ዚደብቄ አፍáˆȘካ ዚጠበቆቜ ማኅበር (Law Society of South Africa) ዚመንግሄቔ ዚፍቔህ አካላቔ በጠበቆቜ ላይ á‹šáˆšá‹«áˆłá‹©á‰”áŠ• ማንኛውንም ንቀቔ በሕግ ይፋለማል፱
ፈሹንሳይ፣ ኏ኒያ.....
ጠበቃ ኄዛ አገር ዚፍቔህ ምሰሶ ኄንጂ ዚፖሊሔ áˆČሳይ አይደለም፱

ጠበቃ ነኝ ቄለህ ፖሊሔ áŒŁá‰ąá‹« áˆ”á‰”á‹°áˆ­áˆ”áŁ ዘበኛው ፖሊሔ ኄንደፈለገ ዚሚሟፍርህ ኹሆነና ዛሬ አይገባም ቄሎ ኄንደ ደጅ ጠኚ áŠ«áŠ•áŒˆáˆ‹á‰łáˆ…áŁ ዚፍቔህ áˆ„áˆ­á‹“á‰łá‰œáŠ• ገደል ገቄቷል ማለቔ ነው፱ ኄኛ ጠበቆቜ ዹሰው መቄቔ ኄናሔኚቄራለን ኄያልን ኄንፎክራለን áŠ„áŠ•áŒ‚áŁ á‹šáˆ«áˆłá‰œáŠ•áŠ• መቄቔ ኄንኳ በፖሊሔና á‰ áˆŹáŒ…áˆ”á‰”áˆ«áˆ­ ፊቔ ማሔኚበር አቅቶን ኚኩሊ ያልተሻለ ሚና ነው á‹«áˆˆáŠ•áą

á‰°á‰ áˆłáŒšá‹á€ ጎራውና... ማለቔም ቃጣኝ
.
ቄቻ ግን ኹአá‹Čሱ ዚጠበቆቜ ማኅበር ምን ይጠበቅበታል? Hailu Hasena
አá‹Čሱ ማኅበር ዹቱሼ ጉዳይ ላይ ቄቻ áŠšáˆ˜áˆ˜áˆ°áŒ„áŁ ዹጠበቃውን ሞራልና ክቄር ዚሚያሔመለሔ "National Protocol á‰ áŠ áˆ”á‰žáŠłá‹­ መቅሚጜ áŠ áˆˆá‰ á‰”áą ፖሊሔ ዛሬ ሰኞ ሔለሆነ ግባ ምናምን.. ዚሚልበቔ ሳይሆን፣ ጠበቃው á‰ áˆ˜á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á‹ ቄቻ ኄንደ ዚፍቔህ አካል ዚሚኚበርበቔ አሠራር ካልተዘሚጋ ሙያው áˆ˜áˆłáˆˆá‰‚á‹« መሆኑ አይቀርም፱

ዚራሱን መቄቔ áˆłá‹«áˆ”áŠšá‰„áˆ­áŁ ዹሌላውን ላሔኚቄር ዹሚል ጠበቃ ቆም ቄሎ ሊያሔቄ ይገባል!

ጓዶቜ á‰„á‰łáˆáŠ‘áˆ ባታምኑም ተደፍሹናል ተንቀናልđŸ’Șâ˜č
👉 Lawyer Fikerslase Mitiku áŠ„áŠ•á‹łáŒ‹áˆ«áŠ• ኄንደወሚደ ዹተወሰደ ነው🙏👏
👉 ዹ኱ፌዮáˆȘ ፍቔህ ሚ/ርና ፌዎራል ፖሊሔ ቔኩሚቔ á‰ąáˆ°áŒĄá‰” ጄሩ ነው፱ አቄዛኛው ፖሊሔ ይሁን ዐቃቀ ህግ ጠበቆቜን ይሁን ህ/ቡን አክባáˆȘ ናቾው አንዳንዶá‰č ግን ለጠበቃ ያላ቞ው አመለካኚቔ ቔክክል አይደለም ኄሱም ነገ ጠበቃ ኄንኳን ባይሆኑ ተገልጋይ መሆናቾው አይቀርም⚖⚖
👍6❀4
ዹሕግ ቔምህርቔ ዹመማር ፍላጎቔ ላላቜሁ ዹሚሆን መሹጃ:

â€‹á‰ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ዹሕግ ቔምህርቔ ቀቶቜ áŠźáŠ•áˆ¶áˆ­á‰Čዹም በ2013 ዓ.ም (2021 ኄ.ኀ.አ) በወጣው ዚተሻሻለው ቄሔራዊ ሄርዓተ ቔምህርቔ áˆ˜áˆ áˆšá‰”áŁ ወደ ሕግ ቔምህርቔ ቀቔ (LL.B á•áˆźáŒáˆ«áˆ) áˆˆáˆ˜áŒá‰Łá‰” ዹተቀመጡ መሔፈርቶቜ ዚሚኚተሉቔን á‹­áˆ˜áˆ”áˆ‹áˆ‰áą

​በመጀመáˆȘያ ደሹጃ አንዔ ተማáˆȘ ለውዔዔር ቄቁ ለመሆን ዝቅተኛውን መሔፈርቔ ማሟላቔ ይኖርበታል፱ ይህም ዹመጀመáˆȘያ ሎሚሔተር ዚዩኒቚርáˆČá‰Č ውጀቔ (GPA) ለወንዔ ተማáˆȘዎቜ 3.0 ኄና ኚዚያ በላይ áˆČሆን፣ ለሎቔ ተማáˆȘá‹Žá‰œáŁ ለአካል áŒ‰á‹łá‰°áŠžá‰œ ኄንá‹Čሁም ኹታዳጊ ክልል ለመጡ ተማáˆȘዎቜ ደግሞ 2.75 ኄና ኚዚያ በላይ መሆን ይኖርበታል፱ በተጹማáˆȘም ዹኹፍተኛ ቔምህርቔ áˆ˜áŒá‰ąá‹« ፈተና ውጀቔ 50% ኄና ኚዚያ በላይ መሆኑ ለቄቁነቔ ዚግዔ ነው፱

ዹቅበላ ነጄቄ አያያዝን (Weighting) በተመለኹተ ደግሞ ምደባው በውዔዔር ላይ ዹተመሰሹተ ሆኖ ዚውጀቔ ዔርሻው 50% ኚዩኒቚርáˆČá‰Č ዹመጀመáˆȘያ ሎሚሔተር GPA፣ 30% ኹሕግ ቔምህርቔ ቀቔ á‹šáˆ˜áŒá‰ąá‹« ፈተና፣ ኄንá‹Čሁም 20% ኚቄሔራዊ ዹኹፍተኛ ቔምህርቔ áˆ˜áŒá‰ąá‹« ፈተና ዹሚሰላ ይሆናል፱ ለአዎንታዊ ዔጋፍ (Affirmative Action) ዹሚገባቾው ተማáˆȘዎቜ ደግሞ ተጹማáˆȘ 5% ኄዔል ይሰጣቾዋል፱

​ሌላው ልቄ ሊባል ዹሚገባው áŠáŒ„á‰„áŁ ተማáˆȘዎቜ ቁጄራ቞ው አነሔተኛ በሚሆንበቔ ጊዜ ቔምህርቔ ቀቶá‰č መሔፈርቱን ዝቅ ሊያደርጉ á‰ąá‰œáˆ‰áˆáŁ በማንኛውም ሁኔታ ውጀቱ ለወንዔ ተማáˆȘዎቜ ኹ 2.8 ኄንá‹Čሁም áˆˆáˆŽá‰”áŁ ለአካል ጉዳተኛና ኹታዳጊ ክልል ለመጡ ተማáˆȘዎቜ ኹ 2.6 á‰ á‰łá‰œ ዝቅ ሊል áŠ á‹­á‰œáˆáˆáą

በአጠቃላይ ዝቅተኛውን መሔፈርቔ ማሟላቔ ቄቻውን ወደ ሕግ ቔምህርቔ ቀቔ áˆˆáˆ˜áŒá‰Łá‰” ዋሔቔና አይሆንም፱ ቅበላው በተቋማቱ ዹመቀበል አቅም ኄና በውዔዔር ላይ ዹተመሰሹተ መሆኑን ማወቅ ይገባል፱

​ለተኹታታይ ቔምህርቔ (Continuing Education) á•áˆźáŒáˆ«áˆ ደግሞ á‹šáˆ˜áŒá‰ąá‹« መሔፈርቱ ዹሚወሰነው በኄያንዳንዱ ዹሕግ ቔምህርቔ ቀቔ ዹቅበላ ኼሚቮ (Admission Committee) ነው፱ ኼሚቮው መሔፈርቶá‰čን áˆČá‹«á‹ˆáŒŁ á‹šáŒŸá‰ł ሔቄጄርን ኄና ለመደበኛው á•áˆźáŒáˆ«áˆ ዹተቀመጡ á‹šáˆ˜áŒá‰ąá‹« መሔፈርቶቜን áŠ áŒá‰Łá‰„áŠá‰” ባለው መልኩ ግምቔ ውሔጄ á‹«áˆ”áŒˆá‰Łáˆáą

ለሕግ ቔምህርቔ ፍላጎቱ ላላቜሁ ሁሉ ይህ መሹጃ ለግንዛቀ ይሹዳ ዘንዔ ዹቀሹበ ነው፱

https://t.me/Aid432
❀5
‎áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 22/5018 ዓ.ም

‎ክፍቔ ዚሄራ áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹«á€

‎ዕለተ ማክሰኞ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 22 ቀን 2018 ዓ.ም
‎( ዹጌዮኩ ዞን ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ሕዝቄ ግንኙነቔ)
‎በጌዮኩ ዞን ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ውሔጄ በአሉቔ ክፍቔ ዚሄራ መደቊቜ ላይ ዹዋና áˆŹáŒ…áˆ”á‰”áˆ«áˆ­ ኄና áˆšá‹łá‰” ዳኛ መሔፈርቶቜን ወይም ተፈላጊ á‰œáˆŽá‰ł ዚሚያሟሉቔን ዹሕግ á‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œáŠ• áŠ á‹ˆá‹łá‹”áˆź ለማሟም በወጣው áˆ›áˆ”á‰łá‹ˆá‰‚á‹« መሠሚቔ በመመዝገቄ áŠ„áŠ•á‹”á‹ˆá‹łá‹°áˆ© ዹጌዮኩ ዞን ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ንዑሔ á‹łáŠáŠá‰” áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ áŒ‰á‰ŁáŠ€ ጜ/ቀቔ ይጋቄዛል ፱

‎@ ዹጌዮኩ ዞን ኹፍተኛ ፍርዔ ቀቔ ሕዝቄ ግንኙነቔ
‎ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 22/2018 ዓ.ም
‎ á‹Čላፀ
ሐሰተኛ ሰነዔ በመፍጠር ወይም በመገልገል ወንጀል ላይ ዹተሰጠ አá‹Čሔ ዹሰበር ውሳኔ
​ዚፌደራል ጠቅላይ ፍርዔ ቀቔ ሰበር ሰሚ ቜሎቔ በቅርቡ (ጄቅምቔ 05 ቀን 2017 ዓ.ም) በመዝገቄ ቁጄር 247213 በሰጠው ውሳኔ፣ በሀሰተኛ ሰነዔ ክሔ ሂደቔ ውሔጄ ሊሟሉ áˆ”áˆˆáˆšáŒˆá‰Ą ማሔሚጃዎቜ አጜንኊቔ áˆ°áŒ„á‰·áˆáą
​ዹውሳኔው ፍሬ áˆ€áˆłá‰„áĄ-
አንዔ ሰው ሀሰተኛ ሰነዔ አዘጋጅቷል ወይም ተገልግሎበታል ተቄሎ ክሔ áˆČá‰€áˆ­á‰„á‰ á‰”áŁ ተኹሳáˆč "ሰነዱ ሀሰተኛ አይደለም/ቔክክለኛ ነው" ዹሚል ክርክር ካቀሚበፀ ዐቃቀ ህግ ዚሚኚተሉቔን በግልጜ á‹šáˆ›áˆ”áˆšá‹łá‰” ግዮታ áŠ áˆˆá‰ á‰”áĄ-
​ሰነዱ ሀሰተኛ መሆኑን፡ በመጀመáˆȘያ ደሹጃ ሰነዱ ራሱ ፎርጂዔ (Fake) መሆኑን በማሔሚጃ áˆ›áˆšáŒ‹áŒˆáŒ„áą
​ዹተኹሳáˆčን ሚና፡ ያንን ሀሰተኛ ሰነዔ ዹፈጠሹው ወይም ያዘጋጀው ወይም ዚተገለገለበቔ ተኹሳáˆč ራሱ መሆኑን áˆ›áˆšáŒ‹áŒˆáŒ„áą
​ዹህጉ መሰሚቔ (አዋጅ ቁ. 881/2007 አንቀጜ 23)፡
በሙሔና ወንጀሎቜ አዋጅ መሰሚቔ አንዔ ሰው ጄፋተኛ ዹሚባለው፡-
â€‹áˆ˜áŠ•áŒáˆ”á‰łá‹Š ወይም ህዝባዊ ሰነዔን አሔመሔሎ áŠšáˆ°áˆ«áŁ
​ኄውነተኛውን ሰነዔ ኹለወጠ/ኹደለዘ (ፊርማ፣ á‰áŒ„áˆ­áŁ ይዘቔ በመቀዹር)፣ ወይም
​ሰነዱ ሀሰተኛ መሆኑን ኄያወቀ ኚተገለገለበቔ ነው፱
​📌 áˆ›áŒ á‰ƒáˆˆá‹«áĄ ሰነዱ ሀሰተኛ ሔለመሆኑ ኄና ተኹሳáˆč ሔለማዘጋጀቱ በተገቱው ማሔሚጃ áˆłá‹­áˆšáŒ‹áŒˆáŒ„ በደፈናው ዚሚቀርቄ ክሔ ተቀባይነቔ ዹለውም፱
​📖 ዋቱ áˆ˜á‹›áŒá‰„á‰”áĄ ሰ/መ/ቁ 247213፣ 241756 ኄና 245579
❀1
" ማንኛውም ሰው በቜሎቔ ውሔጄ ሆነ ኚቜሎቱ ውጭ ማንኛውም በደብቄ ፍ/ቀቔ ዳኛን áˆČጠራ ለሎቔ "ክቄርቔ ዳኛ" ለወንዔ " ክቡር ዳኛ" በማለቔ መጄራቔ አለበቔ!! "

(ዹደ/኱/ክ/ጠ/ፍ/ቀቔ ዹክልሉ ፍ/ቀቶቜ ዚቜሎቔ ሄነ ሄርዓቔ መመáˆȘያ ቁጄር 04/2017 አንቀጜ 16/2 )
#ዜናመሠሚቔ ለ64 á‹“áˆ˜á‰łá‰” ሔራ ላይ ዹዋለው ዹወንጀለኛ መቅጫ ሄነ-ሄርዓቔ ሕግ በነገው ኄለቔ በፓርላማ á‰°áˆœáˆź በአá‹Čሔ ሊቀዹር መሆኑ ታወቀ

ዹወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ በ1996 ዓ.ም áˆČሻሻል ዚሄነ-ሄርዓቔ ሕጉ áŠ á‰„áˆź መሻሻል አለበቔ በሚል በወቅቱ ክርክር ተነሔቶበቔ ዹነበሹ áˆČሆን ኹ64 á‹“áˆ˜á‰łá‰” በኋላ ነገ ዚካá‰Čቔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአá‹Čሔ ሕግ ሊተካ áˆ°á‹“á‰łá‰” ቀርተውታል፱ https://t.me/Aid432
👍8❀2
ኹ500 ቄር በላይ ለሌላ ሰው ዹተሰጠ ገንዘቄን ለማሔመለሔ በሰው ምሔክር áˆ›áˆ”áˆšá‹łá‰” አይቻልም ዹሚለው ህግ ለማን ነው á‹šáˆšáˆ°áˆ«ï€ż
ዚፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቀቔ ሰበር ሰሚ ቜሎቔ ዚሚኚተሉቔን ነጄቊቜ ግልጜ áŠ á‹”áˆ­áŒ“áˆáĄáĄ
á‰„á‹”áˆ­áĄ- ፍቔሐቄሄር ህግ ቁጄር 2472 ዚሚሰራው ለቄዔር ቄቻ ነው፡፡
á‹•á‰á‰„áĄ- ዚዕቁቄ ገንዘቄ ክፍያን áˆˆáˆ›áˆ”áˆšá‹łá‰” ዹሰው ምሔክር መጠቀም á‹­á‰»áˆ‹áˆáĄáĄ (ዚመዝገቄ ቁጄር 94240)
ዹዕቃ መግዣ፡- ለዕቃ መግዣ ዹተሰጠን ገንዘቄ áˆˆáˆ›áˆ”áˆšá‹łá‰” ማንኛውንም ዓይነቔ ማሔሚጃ መጠቀም á‹­á‰»áˆ‹áˆáĄáĄ (ዹመ/ቁጄር 64397)
ማታለል፡- በማታለል ዹተወሰደ ገንዘቄን áˆˆáˆ›áˆ”áˆšá‹łá‰” ዹሰው ምሔክር መጠቀም á‹­á‰»áˆ‹áˆáĄáĄ (ዹመ/ቁጄር 85270)
👍1
" ኹዛሬ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 21 ጀምሼ ዚኄጅ ሔልክን በመደበኛ ዚሄራ ሰዓቔ መጠቀም ተኹልክሏል " - ቱሼው

âžĄïž " á‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œ ዚኄጅ ሔልካ቞ውን በመጠቀም ዚግቄር ኚፋዩ ጊዜ ኄንá‹Čቃጠል ዚማዔሚግ ሁኔታ አለ ! "

ዹአá‹Čሔ አበባ ኹተማ áŒˆá‰ąá‹Žá‰œ ቱሼ፣ ለሠራተኞá‰č "ኹዛሬ áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 21/2018 ዓ/ም ጀምሼ ዚኄጅ ሔልክን በመደበኛ ዚሄራ ሰዓቔ መጠቀም ተኹልክሏል" áˆČል ለá‰Čክቫህ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ገልጿል፱

ዹቱሼው á‹šáŠźáˆšá‹©áŠ’áŠŹáˆœáŠ• ዳይሬክተር አቶ ሰውነቔ አዹለ፣ " ሠራተኞቜ መደበኛ ዚሄራ ሰዓታቾውን áˆČጀምሩ በተዘጋጀው ሎኹር áˆ”áˆáŠźá‰čን  áˆ›áˆ”á‰€áˆ˜áŒ„áŁ በዚሄራ ክፍሉ ላሉ á‹łá‹­áˆŹáŠ­á‰°áˆźá‰œ ሰጄቶ ወደ ሄራ áˆ˜áŒá‰Łá‰” አለባቾው " áˆČሉ ነግሹውናል፱

ለሄራ ሔልክ መጠቀም á‹«áˆˆá‰Łá‰žá‹ ግን ተለይተው ኄንደሚጠቀሙም ገልጾዋል፱

ግቄር áŠšá‹á‹źá‰œ ኚሚያሷ቞ው á‰…áˆŹá‰łá‹Žá‰œ መካኚል አንዱ " ኚሔልክ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ ያለ ቜግር " መሆኑን ጠቅሰው፣ በተለይ ግቄር ኚፋዩ አገልግሎቔ ለማግኘቔ በሚሄዔበቔ ጊዜ " አንዳንዔ á‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œ ዚኄጅ ሔልካ቞ውን በመጠቀም ዚግቄር ኚፋዩ ጊዜ ኄንá‹Čቃጠል ዚማዔሚግ ሁኔታ አለ " áˆČሉ ለá‰Čክቫህ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ገልጾዋል፱

በዚህ ጉዳይ " 7 áˆșሕ ኚሚደርሱ ሠራተኞቜ ጋር ዚጋራ áˆ˜áŒá‰Łá‰Łá‰”" ላይ ዚደሚሱበቔ ነገር "በተለይ በመደበኛ ዚሄራ ሰዓቔ ዚኄጅ ሔልክን ኹመጠቀም" ኄንá‹Čቆጠቄ መሆኑን á‰ áˆ˜áŒáˆˆáŒœáŁ ዓላማውም " ዚግቄር ኚፋዩን áŠ„áˆ­áŠ«á‰ł ማሚጋገጄ ነው " á‰„áˆˆá‹‹áˆáą

በኄርግጄ ሠራተኛ ዚሄራ ሰዓቔን በአግባቡ ዹመጠቀም ኃላፊነቔ አለበቔፀ ግን በሄራ ሰዓቔ " አቔጠቀሙ " ቄሎ ህግ áˆ›á‹áŒŁá‰” ኄንጅ ኄንá‹Čሁ መኹልኹሉ መቄቔን መጋፋቔ አይሆንም ? በሚል á‰Čክቫህ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ዹጠዹቅናቾው አቶ áˆ°á‹áŠá‰”áŁ " ኹህግ ጋር ዹሚገናኝ ነገር ዹለም፱ ሔልክ መጠቀም ኹተፈለገ በዚቅርንጫፉ መደበኛ áˆ”áˆáŠźá‰œ አሉ መጠቀም ይቻላል " áˆČሉ መልሰዋል፱

" ዹግል ሔልካ቞ውንም ቱሆን ኹመደበኛ ዚሄራ ሰዓቔ ውጭ (ለምሳሌ በምሳ ሰዓቔ ኹ6 ኄሔኚ 7 ሰዓቔ á‰°áŠ©áˆáŁ በሻይ áŠ„áˆšáá‰”áŁ ዚግቄር ኚፋዩን አገልግሎቔ áŠ áˆ°áŒŁáŒ„ በማይሻማ መንገዔ መጠቀም ዚሚቻልበቔ ሁኔታ አለ" áˆČሉ አክለው፣ "ኚመቄቔ ጋር ዚሚያያይዘው ነገር ይኖራል ቄዚ አላምንም" ነው á‹«áˆ‰á‰”áą

ዹቱሼ መደበኛ áˆ”áˆáŠźá‰œáŠ• ለመደበኛ ግንኙነቔም መጠቀም ኄንደሚቻል áŠ áˆ”áˆšá‹”á‰°á‹‹áˆáą

ኚአገልግሎቔ áŠ áˆ°áŒŁáŒ„ ጋር á‰ á‰°á‹«á‹«á‹˜áŁ " ሔልክ ዹመጎርጎር፣ ማህበራዊ ሚá‹Čያዎቜ ላይ á‹šáˆ˜áŒŁá‹” " ኄና መሰል á‰œáŒáˆźá‰œ መሔተዋላ቞ውን áŠ á‹áˆ”á‰°á‹áŁ በዋነኛነቔ áŠšá‰ŁáˆˆáŒ‰á‹łá‹źá‰œ ጋር ፊቔ ለፊቔ ያሉ ኄና ኹዚህ ጋር ዚተያያዙ ሠራተኞቜ ሄራ቞ው ላይ ቔኩሚቔ አዔርገው ለግቄር ኚፋዩ ተገቱውን ክቄር ሰጄተው ማገልግል ይጠበቅባቾዋል á‰„áˆˆá‹‹áˆáą

ለዚህ ውሳኔ ያደሚሷ቞ው á‰œáŒáˆźá‰œáŠ• ምንነቔ áˆ”áŠ•áŒ á‰ƒá‰žá‹áŁ " áŠšá‰Łáˆˆáˆ™á‹«á‹Žá‰œ áˆ”áŠáˆáŒá‰Łáˆ­áŁ ኚሰዓቔ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ በግቄር áŠšá‹á‹źá‰œ ዚሚነሱ á‰œáŒáˆźá‰œ አሉ " á‰„áˆˆá‹áŁ á‰œáŒáˆźá‰čን ለመቅሹፍ " 24 ዚሚደርሱ áŠ áˆ°áˆ«áˆźá‰œ ተለይተው ወደ ተግባር ተሾጋግሹዋል" áˆČሉ áŠ áˆ”áˆšá‹”á‰°á‹‹áˆáą

" ኹምሰጣቾው 23 ኚሚደርሱቔ አገልግሎቶቜ አሁን ላይ 22 ዚሚደርሱቔ በቮክኖሎጂ ኄንá‹Čደገፉ ለማዔሚግ ጄሚቔ ኄያደሚግን ነው " ያሉቔ አቶ áˆ°á‹áŠá‰”áŁ " በዚህም ግቄር ኚፋዩ በቀቱ ሆኖ አገልግሎቔ ማግኘቔ ዚሚቜልበቔ ሁኔታ ለመፍጠር ጄሚቔ ኄዚተደሚገ ነው" á‰„áˆˆá‹‹áˆáą

via á‰Čክቫህ áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹«
👍1
ሰበር ዜና ምክር ቀቱ ዹወንጀል ሕግ ሄነ-ሔርአቔ ኄና ዚማሔሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን መርምሼ አፀደቀ
----------------------
(ዜና ፓርላማ) áˆ˜áŒ‹á‰ąá‰” 24፣ 2018 ዓ.ምፀ ዚሕዝቄ á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ ምክር ቀቔ በ13ኛ መደበኛ áˆ”á‰„áˆ°á‰Łá‹á€ á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ፌዎራላዊ á‹ČሞክራáˆČያዊ áˆȘፐቄሊክ ዹወንጀል ሕግ ሄነ-ሔርአቔ ኄና ዚማሔሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅን áŠ á…á‹”á‰‹áˆáĄáĄ

በህዝቄ á‰°á‹ˆáŠ«á‹źá‰œ ምክር ቀቔ ዹሕግና ፍቔህ áŒ‰á‹łá‹źá‰œ ቋሚ ኼሚቮ áˆ°á‰„áˆłá‰ą ዚተኚበሩ ወ/ሟ ኄፀገነቔ መንግሔቱ áˆȘፖርቔ ኄና ዹውሳኔ áˆ€áˆłá‰„ አቅርበዋል፡፡

ሹቂቅ ሕጉ በወንጀል ፍቔህ áŠ áˆ”á‰°á‹łá‹°áˆ­ ሄርዓቔ ዹወንጀል ፍርዔ ሂደቔ ዹተጠርጣáˆȘን ኄና á‹šá‰°áŠšáˆłáˆœáŠ• ኄንá‹Čሁም በወንጀል ምክንያቔ ዚተጎዱ ሰዎቜን ሰቄአዊ መቄቶቜ ለማክበርና ለማሔኚበር ዹሕግ ዚበላይነቔ በማሔፈን ዚአሰራር ሔርዓቔን ለመዘርጋቔ ዚሚያሔቜል መሆኑን áˆ°á‰„áˆłá‰ąá‹‹ ገልጾዋል፡፡

ዹተቀላጠፈ ዚፍቔህ ሄርዓቔ ኄንá‹Čኖር ለማሔቻል ኄና ልዩ ዹወንጀል ምርመራ ዘዮን ኄንá‹Čሁም ለተጎጂዎቜ áŠ«áˆŁ ዚሚኚፈልበቔን áŠ áŒá‰Łá‰„ ያካተተ ዓለም አቀፍ መርህን ዹተኹተለ ሹቂቅ ሕግ ኄንደሆነ ዚተኚበሩ ወ/ሟ ኄፀገነቔ መንግሔቱ አያይዘው áŠ áˆ”áˆšá‹”á‰°á‹‹áˆáĄáĄ

ሹቂቅ ሕጉ áŠšáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ሕገ-መንግሄቔ ኄና áŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ኚተቀበለቻ቞ው ዓለም አቀፍ áˆ”áˆáˆáŠá‰¶á‰œáŁ መርሆቜ ኄና ኄሎቶቜ ኄንá‹Čሁም ኹወንጀል ህጉ ጋር ዹተጣጣመና ዘመናዊ በመሆኑ ጠቀሚ ኄንደሆነ áˆ°á‰„áˆłá‰ąá‹‹ ጠቁመዋል፡፡

ሹቂቅ ህጉ በህገ áˆ˜áŠ•áŒáˆ”á‰±áŁ በወንጀል ሕጉ፣ ዓለም አቀፍ ህጎቜ ኄና በሌሎቜ áŠ áŒá‰Łá‰„áŠá‰” ባላቾው ህጎቜ ዹተሹጋገጡ ልዩ ቔኩሚቔ ለሚያሻ቞ው áˆˆáˆŽá‰¶á‰œáŁ ህፃናቔ ኄና አካል áŒ‰á‹łá‰°áŠžá‰œ ዹተሰጣቾውን መቄቶቜ ለማሚጋገጄ ዚሚያሔቜል ኄንደሆነም ዚተኚበሩ ወ/ሟ ኄፀገነቔ መንግሔቱ ገልጾዋል፡፡

ዹምክር ቀቔ áŠ á‰Łáˆ‹á‰” በበኩላ቞ው ሹቂቅ አዋጁ ሹጅም ጊዜ ዹቆዹና ዹዘገዹ ቱሆንም በህዝቡ ዘንዔ ዹቅሬታ ምንጭ ዚነበሩ á‰œáŒáˆźá‰œáŠ• áˆˆáˆ˜áá‰łá‰” ወቅቱን ዚሚመጄን አዋጅ በመሆኑ ዚህዝቄን ዚፍቔህ ሄርዓቱን ለማሔፈን ኄንደሚያግዝ ገልጾዋል፡፡

ዚዜጎቜን ሰቄአዊ ኄና á‹ČሞክራáˆČአዊ መቄቶቜን ለማሔኚበር ኄና ዚፍቔህ ሄርዓቱን በማዘመን ወቅቱን ያዋጅ አግልግሎቔ ለመሔጠቔ ሹቂቅ አዋጁ ሚናው ዹጎላ መሆኑን ዹምክር ቀቔ áŠ á‰Łáˆ‹á‰” አመላክተዋል፡፡፡

በሌላ በኩል ዹምክር ቀቔ áŠ á‰Łáˆ‹á‰” በበኩላ቞ውፀ ሹቂቅ አዋጁ በአተገባበር ሂደቔ ላይ ሊያጋጄሙ ዚሚቜሉ á‰œáŒáˆźá‰œáŠ• ታሳቱ በማዔሚግ ኚፍቔህ አካላቔ ጋር መወያዚቔ ኄንደሚያሔፈልግ áŠ áˆ”áŒˆáŠ•á‹á‰ á‹‹áˆáĄáĄ

ኚምርመራ ሂደቔ ኄና ኹá‹Čጂታል áŠ áˆ°áˆ«áˆźá‰œ ጋር በተያያዘ ዜጎቜን ህገ áˆ˜áŠ•áŒáˆ”á‰łá‹Š መቄቔን በጠበቀ መልኩ መሆን áŠ„áŠ•á‹łáˆˆá‰ á‰” ዹምክር ቀቔ áŠ á‰Łáˆ‹á‰± አሔገንዝበውፀ በማሚሚያ ቀቔ ቆይተው ፍርዔ ቀቔ ነፃ ዹሚላቾው ዜጎቜ á‹šáŠ«áˆł ክፍያ ሄርዓቔን ለመዘርጋቔ በግልጜ በሹቂቅ አዋጁ ማሔቀመጄ áŠ„áŠ•á‹°áˆšáŒˆá‰Ł áŠ áˆłáˆ”á‰ á‹‹áˆáĄáĄ

ምክር ቀቱፀ á‹šáŠąá‰”á‹źáŒ”á‹« ፌዎራላዊ á‹ČሞክራáˆČያዊ áˆȘፐቄሊክ ዹወንጀል ሕግ ሄነ-ሔርአቔ ኄና ዚማሔሚጃ ሕግ ሹቂቅ አዋጅ ፀ አዋጅ ቁጄር 1410/2018 አዔሚጎ በሁለቔ ተቃውሞፀ በአቄላጫ ዔምጜ áŠ áŒœá‹”á‰‹áˆáĄáĄ
via hpr https://t.me/Aid432
👏2
Channel photo updated
ዛሬ በፓርላማው ውሎ አጚቃጫቂ ዹነበሹው ዔንጋጌ:: https://t.me/Aid432