መውሊድ‼
ነገ ማክሰኞ 1,501ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሀገራችን በታላቅ ድምቀት እንደሚከበር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታውቋል።
📌 የዘንድሮው መሪ ቃል፦
"የፍትሃዊው ነብይ"
በዓሉ የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮ መሠረት በማድረግ በተለያዩ መንፈሳዊና ማኅበራዊ መርሐ-ግብሮች ይከበራል።
መውሊድ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ሆነው ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት አንዱ ነው።
፡፡
ነገ የሚከበረውን የመውሊድ በዓል ምክንያት በማድረግ ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
መልካም የመውሊድ በዓል!
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ማክሰኞ 1,501ኛው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የመውሊድ በዓል በሀገራችን በታላቅ ድምቀት እንደሚከበር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታውቋል።
📌 የዘንድሮው መሪ ቃል፦
"የፍትሃዊው ነብይ"
በዓሉ የነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ) አስተምህሮ መሠረት በማድረግ በተለያዩ መንፈሳዊና ማኅበራዊ መርሐ-ግብሮች ይከበራል።
መውሊድ በሀገር አቀፍ ደረጃ የመንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ ሆነው ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ በዓላት አንዱ ነው።
፡፡
ነገ የሚከበረውን የመውሊድ በዓል ምክንያት በማድረግ ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡
መልካም የመውሊድ በዓል!
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤12🤣6🤪3👍2🎉2🤔1
ተጨማሪ የድሮን ጥቃት‼️
በዛሬው ዕለት በራያ አዘቦ ከተፈፀመው የድሮን ጥቃት በተጨማ በሽሬ በአዲ ገብሩ (ከአውራ ጎዳና አቅራቢያ) በሚገኘው እንዳ ባጉና ልዩ መውጫ ላይ ተፈጽሟል። በዚህ ጥቃት አንድ ወታደራዊ ተሽከርካሪ (ኦራል) እና አንድ ታንክ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮች ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በዛሬው ዕለት በራያ አዘቦ ከተፈፀመው የድሮን ጥቃት በተጨማ በሽሬ በአዲ ገብሩ (ከአውራ ጎዳና አቅራቢያ) በሚገኘው እንዳ ባጉና ልዩ መውጫ ላይ ተፈጽሟል። በዚህ ጥቃት አንድ ወታደራዊ ተሽከርካሪ (ኦራል) እና አንድ ታንክ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ምንጮች ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍13❤5🤪2✍1🤔1🕊1🤣1🫡1
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 125 ሚሊዮን ዶላር በጨረታ ሊሸጥ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቡዕ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው የ27ኛው ዙር የውጭ ሀገር ገንዘብ (FX) ጨረታ ይፋ አድርጓል።
በዚህ ጨረታ ላይ 125 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን፣ ፍላጎት ያላቸው ባንኮች የተዘጋጀውን መመሪያ ተከተለው እንዲወዳደሩ ተጠይቀዋል።
የጨረታ ሰዓት: ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት
የማስገቢያ መንገድ: በCSD ኤሌክትሮኒክ የሐራጅ ሥርዓት በኢሜይል
ውጤት የሚገለጽበት: በዕለቱ ከሰዓት በ9:00 ሰዓት
ክፍያና ሂሳብ ማጣሪያ : ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሥራ ቀን ማጠቃለያ ላይ ይፈጸማል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ረቡዕ፣ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በሚያካሂደው የ27ኛው ዙር የውጭ ሀገር ገንዘብ (FX) ጨረታ ይፋ አድርጓል።
በዚህ ጨረታ ላይ 125 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን፣ ፍላጎት ያላቸው ባንኮች የተዘጋጀውን መመሪያ ተከተለው እንዲወዳደሩ ተጠይቀዋል።
የጨረታ ሰዓት: ከጠዋቱ 4:00 እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት
የማስገቢያ መንገድ: በCSD ኤሌክትሮኒክ የሐራጅ ሥርዓት በኢሜይል
ውጤት የሚገለጽበት: በዕለቱ ከሰዓት በ9:00 ሰዓት
ክፍያና ሂሳብ ማጣሪያ : ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሥራ ቀን ማጠቃለያ ላይ ይፈጸማል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤7👍2
👍2
እንድታውቁት‼️
በሀገራዊ ምከክሩ ላይ ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ አልተደረሰም፣አልተሰጠም። እስካሁን ያለው ምክረሀሳብና አስተያየት ነው የተሰጠው። ተመካካሪዎች የተስማሙበት ሀሳብ ለብቻው ይመዘገባል፣ተቃውሞ የቀረበበት አጀንዳ ደግሞ በልዩነት ይመዘገባል።
ተመካካሪዎች በየትኛውም አጀንዳ ላይ ቢስማሙም ወይም ቢቃወሙ የመጨረሻ ውሳኔ አይደለም። በሁለም አጀንዳዎች ላይ ለሀገር ይጠቅማል የሚለውን የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጠው እራሱ የምክክር ኮሚሽኑ መሆኑ የምክክሩ ተሳታፊዎች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሀገራዊ ምከክሩ ላይ ለምክክር በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ አልተደረሰም፣አልተሰጠም። እስካሁን ያለው ምክረሀሳብና አስተያየት ነው የተሰጠው። ተመካካሪዎች የተስማሙበት ሀሳብ ለብቻው ይመዘገባል፣ተቃውሞ የቀረበበት አጀንዳ ደግሞ በልዩነት ይመዘገባል።
ተመካካሪዎች በየትኛውም አጀንዳ ላይ ቢስማሙም ወይም ቢቃወሙ የመጨረሻ ውሳኔ አይደለም። በሁለም አጀንዳዎች ላይ ለሀገር ይጠቅማል የሚለውን የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጠው እራሱ የምክክር ኮሚሽኑ መሆኑ የምክክሩ ተሳታፊዎች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤣29❤12👍3🙈3✍1👌1🥱1🤪1
የንግድ ባንክ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ለወንዶች ያደሉ መሆናቸውን ዓለም ባንክ አረጋገጠ
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ በሥራ ዕድገትና በደመወዝ ክፍያ ረገድ ለወንዶች ያደላ አሠራር መከተሉን የዓለም ባንክ አሳወቀ። ባንኩ ከ50 ሺሕ በላይ ሠራተኞች ያሉት ሲሆን፣ ከሀገሪቱ አጠቃላይ የባንክ ሠራተኞች አንድ ሦስተኛውን ይይዛል። ሆኖም በውስጡ ያለው የሥራ ድልድል ፍትሐዊ እንዳልሆነ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በባንኩ ዘርፍ በብዛት ሴቶች ቢቀጠሩም፣ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎችን መያዝ ላይ ግን ትልቅ ችግር አለ። የዓለም ባንክ ጥናት እንደሚያሳየው፤ በንግድ ባንክ ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ክፍያ የሚከፈላቸው ሲሆን፤ እንደ ኃላፊ ወይም ተቆጣጣሪ ያሉ የሥራ መደቦችን የማግኘት ዕድላቸውም እጅግ ጠባብ ነው።
ይህ በፆታ መካከል የሚታየው ልዩነት በትምህርት፣ በሥራ ልምድ ወይም በብቃት እጥረት የመጣ አይደለም። ባንኩ መደበኛ ደንቦች ቢኖሩትም፣ ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ፍጥነት እንዲያድጉ የሚያደርግ አሠራር መኖሩን ሪፖርቱ አትቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ በሥራ ዕድገትና በደመወዝ ክፍያ ረገድ ለወንዶች ያደላ አሠራር መከተሉን የዓለም ባንክ አሳወቀ። ባንኩ ከ50 ሺሕ በላይ ሠራተኞች ያሉት ሲሆን፣ ከሀገሪቱ አጠቃላይ የባንክ ሠራተኞች አንድ ሦስተኛውን ይይዛል። ሆኖም በውስጡ ያለው የሥራ ድልድል ፍትሐዊ እንዳልሆነ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በባንኩ ዘርፍ በብዛት ሴቶች ቢቀጠሩም፣ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎችን መያዝ ላይ ግን ትልቅ ችግር አለ። የዓለም ባንክ ጥናት እንደሚያሳየው፤ በንግድ ባንክ ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲነጻጸር አነስተኛ ክፍያ የሚከፈላቸው ሲሆን፤ እንደ ኃላፊ ወይም ተቆጣጣሪ ያሉ የሥራ መደቦችን የማግኘት ዕድላቸውም እጅግ ጠባብ ነው።
ይህ በፆታ መካከል የሚታየው ልዩነት በትምህርት፣ በሥራ ልምድ ወይም በብቃት እጥረት የመጣ አይደለም። ባንኩ መደበኛ ደንቦች ቢኖሩትም፣ ሴቶች ከወንዶች ባነሰ ፍጥነት እንዲያድጉ የሚያደርግ አሠራር መኖሩን ሪፖርቱ አትቷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
🤪8👍6❤5🤣4💯1
አሜሪካ የ200,000 ሰዎችን ቪዛ ልትሰርዝ ነው
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በታሪክ ትልቁን የቪዛ ስረዛ እርምጃ ለመውሰድ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ።
እርምጃው በንግድ (B1) እና በቱሪዝም (B2) ቪዛ ወደ አሜሪካ ገብተው የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ ወይም በመጠየቅ ላይ ያሉ እስከ 200,000 የሚደርሱ የውጭ ሀገር ዜጎችን ዓላማ ያደረገ ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሃገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር ከ2016 እስከ 2026 የተሰጡ ቪዛዎችን ለመሰረዝ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት እንደተናገሩት፣ እርምጃው ለአጭር ጊዜ ጉብኝት መጥተው ቪዛውን ለቋሚ መኖሪያነት የተጠቀሙበትን ለመቆጣጠር ታስቦ የተወሰደ ነው።
ይህ የቪዛ ስረዛ ሰዎች ወዲያውኑ ከሀገር እንዲወጡ ባያደርግም፣ ህጋዊ የጉዞ ሁኔታቸውን የሚያሳጣ በመሆኑ ከፍተኛ የህግ ክስና ተቃውሞ እንደሚገጥመው ይገመታል።
የትራምፕ አስተዳደር ከዚህ ቀደምም በቪዛ አመልካቾች ላይ በርካታ ጠንካራ ገደቦችን ሲጥል መቆየቱ ይታወቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በታሪክ ትልቁን የቪዛ ስረዛ እርምጃ ለመውሰድ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ።
እርምጃው በንግድ (B1) እና በቱሪዝም (B2) ቪዛ ወደ አሜሪካ ገብተው የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ ወይም በመጠየቅ ላይ ያሉ እስከ 200,000 የሚደርሱ የውጭ ሀገር ዜጎችን ዓላማ ያደረገ ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሃገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር ከ2016 እስከ 2026 የተሰጡ ቪዛዎችን ለመሰረዝ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት እንደተናገሩት፣ እርምጃው ለአጭር ጊዜ ጉብኝት መጥተው ቪዛውን ለቋሚ መኖሪያነት የተጠቀሙበትን ለመቆጣጠር ታስቦ የተወሰደ ነው።
ይህ የቪዛ ስረዛ ሰዎች ወዲያውኑ ከሀገር እንዲወጡ ባያደርግም፣ ህጋዊ የጉዞ ሁኔታቸውን የሚያሳጣ በመሆኑ ከፍተኛ የህግ ክስና ተቃውሞ እንደሚገጥመው ይገመታል።
የትራምፕ አስተዳደር ከዚህ ቀደምም በቪዛ አመልካቾች ላይ በርካታ ጠንካራ ገደቦችን ሲጥል መቆየቱ ይታወቃል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤8👍6👀2
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤
እንኳን ለ1501 ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
መልካም በዓል
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
እንኳን ለ1501 ኛው የነቢዩ መሐመድ የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
መልካም በዓል
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤16👍6
የድሮን ጥቃት ተፈፀመ
በትግራይ ክልል በምስራቅ ዞን አፅቢ ወረዳ በፈለገ ወይኒ ጣቢያ፣ መብራህቶም በሚባል ቀጠና ልዩ ስሙ « በሊጋ» በተባለው ስፍራ በሚገኘው የሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ትናንት ነሐሴ 18 ከለሊቱ 7:30 አካባቢ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ሲሆን በካምፑ ውስጥ የጦር መሳሪያ ክምችት መኖሩ ተዘግቧል።
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በትግራይ ክልል በምስራቅ ዞን አፅቢ ወረዳ በፈለገ ወይኒ ጣቢያ፣ መብራህቶም በሚባል ቀጠና ልዩ ስሙ « በሊጋ» በተባለው ስፍራ በሚገኘው የሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ትናንት ነሐሴ 18 ከለሊቱ 7:30 አካባቢ የድሮን ጥቃት ተፈፅሟል።
ጥቃቱ የተፈፀመው በሱር ኮንስትራክሽን ካምፕ ላይ ሲሆን በካምፑ ውስጥ የጦር መሳሪያ ክምችት መኖሩ ተዘግቧል።
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤14👍6🤔3😢1
ኦባሳንጆ ወደ መቀሌ አቅንተው ነበር‼️
የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሊሶጉን ኦባሳንጆ ትናንት ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ወደ መቐለ አቅንተው ነበር።
ከዚህ በመነሳት ከፌደራል መንግስቱ ጋር ውይይት የሚጀመር ከሆነ፣ የሚከተሉት ጉዳዮች መመለስ መሠረታዊና ቁልፍ እንደሆኑ ህወሓት አጽንኦት ሰጥቷዋል፦
* የኢኮኖሚ ማዕቀብና እገዳ መነሳት፤
* ወታደራዊ ከበባ ማቆምና የተፈጠረውን ውጥረት ማርገብ፤
* የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ወደ መደበኛ ሁኔታ መመለስ፤
* ተፈናቃዮችን ደህንነታቸውና ክብራቸው በተጠበቀ መንገድ መመለስ፤
* የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ/ህወሓት/ ፖለቲካዊና ሕጋዊ ማንነት መመለስ።የሚሉ ናቸው።
በዚህም ኦሊሶጉን ኦባሳንጆ ከመንግሥት ጋር ተወያይቼ በሚቀጥሉት አንድና ሁለት ሳምንታት ድጋሚ እመለሳለሁ”ማለታቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ኦሊሶጉን ኦባሳንጆ ትናንት ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ወደ መቐለ አቅንተው ነበር።
ከዚህ በመነሳት ከፌደራል መንግስቱ ጋር ውይይት የሚጀመር ከሆነ፣ የሚከተሉት ጉዳዮች መመለስ መሠረታዊና ቁልፍ እንደሆኑ ህወሓት አጽንኦት ሰጥቷዋል፦
* የኢኮኖሚ ማዕቀብና እገዳ መነሳት፤
* ወታደራዊ ከበባ ማቆምና የተፈጠረውን ውጥረት ማርገብ፤
* የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ወደ መደበኛ ሁኔታ መመለስ፤
* ተፈናቃዮችን ደህንነታቸውና ክብራቸው በተጠበቀ መንገድ መመለስ፤
* የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ/ህወሓት/ ፖለቲካዊና ሕጋዊ ማንነት መመለስ።የሚሉ ናቸው።
በዚህም ኦሊሶጉን ኦባሳንጆ ከመንግሥት ጋር ተወያይቼ በሚቀጥሉት አንድና ሁለት ሳምንታት ድጋሚ እመለሳለሁ”ማለታቸውን ምንጮች ገልጸዋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
👍12❤7🤔2
የ12ኛ ክፍል ዉጤት ሲለቀቅ በፍጥነት መረጃ ምታገኙበት እንዲሁም ውጤታችሁን ያለሰርቨር መጨናነቅ እንድታዩ የሚያግዛችሁን ቻናል አሁኑኑ ይቀላቀሉ! 👇
https://t.me/addlist/dLx_2YaQlwFmNjQ8
https://t.me/addlist/dLx_2YaQlwFmNjQ8
😡10🤣4❤3
3ኛው የአፍሪካ ስታር ዋይድ አዋርድ በመስከረም ወር ይካሄዳል!
“ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ፤ መመሰጋገን ባሕላችን እናድርግ” በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው 3ኛው ዙር የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ የሽልማት ሥነ-ሥርዓት በመጪው መስከረም ወር እንደሚካሄድ አዘጋጁ ከለር ፉል ኢቨንት ኦርጋናይዘር በዛሬዉ እለት በአምባሳደር ሆቴል በሰጠዉ መግለጫ አስታዉቋል።
በዝግጅቱ ላይ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) እና ከአፍሪካ ህብረት (Aሀ) የተወጣጡ ተወካዮች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የውጭ ሀገራት እንግዶች እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እንደሚታደሙ ተጠቅሷል።
የዘንድሮው ዝግጅት ከአምናው በበለጠ አድማሱን በማስፋት አህጉራዊ ተደራሽነት ያለው እንዲሆን መደረጉ ተገልፆ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ምሁራንና ባለሙያዎች በዳኝነትና በኮሚቴነት መካተታቸዉም ነዉ የተገለፀዉ።
ሽልማቱ በተለያዩ 11 ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን የአመራር አባልና ኢንቨስትመንት ዘርፍ፣ የኮንስትራክሽንና ሪል እስቴት ዘርፍ፣አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ባንክ፣ አቪየሽንና ቱሪዝም፣ሴትና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች፣ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች እንደሆኑ ተገልጿል።
የአዋርዱ ዋነኛ አላማ በዘርፉ የለፉና የደከሙ ግለሰቦችንና ተቋማትን ፈልፍሎ በማዉጣት የሃገር ባለዉለታ ስለመሆናቸዉና በትዉልዱ ዘንድ ሊመሰገኑ ሊዘከሩ እንደሚገባና ትዉልዱም ከመልካም ሥራቸዉና ከዘወትር ትጋታቸዉ ልምድ እንዲቀስም እድሉን ለማመቻቸት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የቱሪዝም እና የኢንቨስትመንት አቅም ለውጭ ሀገር አልሚዎች ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የሚፈጥር በመሆኑ፣ አሸናፊዎችን በትክክል ለመለየት ከሙያተኞች ግምገማ በተጨማሪ ህዝቡ በድረገፅ አማካኝነት በስልክ፣ በአሜይል፣ በቴሌግራም እና በዋትስአፕ ጥቆማዎችን መስጠቱን እንዲቀጥል አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ ለሕዝብ እና ለአገር በጎ ነገር ያበረከቱ ግለሰቦችና ስኬታማ የኢኮኖሚ ጃግኖች፣ በትጋት በቅንነት እና በሀገር ፍቅር መስራት ተምሳሌት የሆኑ አመራሮች፣ ዉስጥ በመሳተፍ በሙያቸዉ አንቱ ለተባሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ዕውቅና የሚያበረክት ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
“ክብር ለሚገባው ክብር እንስጥ፤ መመሰጋገን ባሕላችን እናድርግ” በሚል መሪ ቃል የሚከናወነው 3ኛው ዙር የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ የሽልማት ሥነ-ሥርዓት በመጪው መስከረም ወር እንደሚካሄድ አዘጋጁ ከለር ፉል ኢቨንት ኦርጋናይዘር በዛሬዉ እለት በአምባሳደር ሆቴል በሰጠዉ መግለጫ አስታዉቋል።
በዝግጅቱ ላይ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) እና ከአፍሪካ ህብረት (Aሀ) የተወጣጡ ተወካዮች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የውጭ ሀገራት እንግዶች እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እንደሚታደሙ ተጠቅሷል።
የዘንድሮው ዝግጅት ከአምናው በበለጠ አድማሱን በማስፋት አህጉራዊ ተደራሽነት ያለው እንዲሆን መደረጉ ተገልፆ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ምሁራንና ባለሙያዎች በዳኝነትና በኮሚቴነት መካተታቸዉም ነዉ የተገለፀዉ።
ሽልማቱ በተለያዩ 11 ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን የአመራር አባልና ኢንቨስትመንት ዘርፍ፣ የኮንስትራክሽንና ሪል እስቴት ዘርፍ፣አገልግሎት ሰጪ ተቋማትና ባንክ፣ አቪየሽንና ቱሪዝም፣ሴትና ወጣት ስራ ፈጣሪዎች፣ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች እንደሆኑ ተገልጿል።
የአዋርዱ ዋነኛ አላማ በዘርፉ የለፉና የደከሙ ግለሰቦችንና ተቋማትን ፈልፍሎ በማዉጣት የሃገር ባለዉለታ ስለመሆናቸዉና በትዉልዱ ዘንድ ሊመሰገኑ ሊዘከሩ እንደሚገባና ትዉልዱም ከመልካም ሥራቸዉና ከዘወትር ትጋታቸዉ ልምድ እንዲቀስም እድሉን ለማመቻቸት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ መርሃ ግብር የኢትዮጵያን የቱሪዝም እና የኢንቨስትመንት አቅም ለውጭ ሀገር አልሚዎች ለማስተዋወቅ ትልቅ እድል የሚፈጥር በመሆኑ፣ አሸናፊዎችን በትክክል ለመለየት ከሙያተኞች ግምገማ በተጨማሪ ህዝቡ በድረገፅ አማካኝነት በስልክ፣ በአሜይል፣ በቴሌግራም እና በዋትስአፕ ጥቆማዎችን መስጠቱን እንዲቀጥል አዘጋጆቹ ጥሪ አቅርበዋል።
የአፍሪካ ስታርዋይድ አዋርድ ለሕዝብ እና ለአገር በጎ ነገር ያበረከቱ ግለሰቦችና ስኬታማ የኢኮኖሚ ጃግኖች፣ በትጋት በቅንነት እና በሀገር ፍቅር መስራት ተምሳሌት የሆኑ አመራሮች፣ ዉስጥ በመሳተፍ በሙያቸዉ አንቱ ለተባሉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ዕውቅና የሚያበረክት ነዉ።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11👍2
በታይላንድ በዝናብ ወቅት ብቻ የሚከሰተው አስደናቂው የምድር "የድንጋይ ዓይን" የተፈጥሮ ክስተት ትኩረት ሳበ
በሰሜን ምስራቅ ታይላንድ ቡኤንግ ካን ግዛት የሚገኘው እና "የምድር ዓይን" በመባል የሚታወቀው አስደናቂው የአሸዋ ድንጋይ ምድር፣ በክረምት ወቅት በሚጥለው የመንሶን የዝናብ ውኃ ሲሞላ ሙሉ በሙሉ ሰዋዊ ዓይን የሚመስል ምስል እንደሚፈጥር ተገለጸ። ይህ ተፈጥሯዊ ክስተት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በውኃ መሸርሸር ምክንያት በድንጋዩ ላይ በተፈጠረው ጥልቅ ጉድጓድ ምክንያት የሚከሰት ነው።
በዝናብ ወቅት ውኃው በድንጋዩ ጉድጓድ ውስጥ በሚጠራቀምበት ጊዜ፣ የጉድጓዱ ጥልቅ ማዕከል ጥቁሩን የዓይን ብሌን የሚመስል ሲሆን፤ በዙሪያው ያለው አጭር የውኃ ገጽታ ደግሞ ውጫዊውን የዓይን ክፍል ይፈጥራል። በተጨማሪም የፀሐይ ብርሃን በውኃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረው ነፀብራቅ ከሰው ልጅ ዓይን ጋር ተመሳሳይነት ያለው እይታ እንዲኖረው ያደርገዋል።
የዝናብ ወቅት ሲያልቅ ውኃው የሚደርቅ በመሆኑ ይህ አስደናቂ ክስተት የሚታየው በክረምት ወቅት ብቻ እንደሆነ ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በሰሜን ምስራቅ ታይላንድ ቡኤንግ ካን ግዛት የሚገኘው እና "የምድር ዓይን" በመባል የሚታወቀው አስደናቂው የአሸዋ ድንጋይ ምድር፣ በክረምት ወቅት በሚጥለው የመንሶን የዝናብ ውኃ ሲሞላ ሙሉ በሙሉ ሰዋዊ ዓይን የሚመስል ምስል እንደሚፈጥር ተገለጸ። ይህ ተፈጥሯዊ ክስተት በሺዎች ለሚቆጠሩ ዓመታት በውኃ መሸርሸር ምክንያት በድንጋዩ ላይ በተፈጠረው ጥልቅ ጉድጓድ ምክንያት የሚከሰት ነው።
በዝናብ ወቅት ውኃው በድንጋዩ ጉድጓድ ውስጥ በሚጠራቀምበት ጊዜ፣ የጉድጓዱ ጥልቅ ማዕከል ጥቁሩን የዓይን ብሌን የሚመስል ሲሆን፤ በዙሪያው ያለው አጭር የውኃ ገጽታ ደግሞ ውጫዊውን የዓይን ክፍል ይፈጥራል። በተጨማሪም የፀሐይ ብርሃን በውኃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረው ነፀብራቅ ከሰው ልጅ ዓይን ጋር ተመሳሳይነት ያለው እይታ እንዲኖረው ያደርገዋል።
የዝናብ ወቅት ሲያልቅ ውኃው የሚደርቅ በመሆኑ ይህ አስደናቂ ክስተት የሚታየው በክረምት ወቅት ብቻ እንደሆነ ተጠቅሷል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤24🤯5👍2🥰2🤔1
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤4👍2
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል።
ውጤት ለማየት ፦
👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል።
ውጤት ለማየት ፦
👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤6👍2
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፡-
✅ከጠዋቱ 11፡00-11፡00
👉ኢዮ ጠቢብ ሆስፒታል፣ አበበ ቢቂላ ስታድየም፣ መድሀኒዓለም ት/ቤት ጀርባ፣ መድሀኒዓለም ኮንዶሚኔም፣ ቦናት እና አካባቢው፣
👉ሸጎሌ ቴሌ፣ ሩፋኤል ፊናንስ፣ አንበሳ ጋራጅ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል ጀርባ፣ ውሃ ጋኑ አካባቢ ( ጎማ አደባባይ) እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡30-10፡30
👉ሱሉልታ መሀል ከተማ ፣ኢንዱስትሪ መንደር ፣ ወሌ ፣ ጎሮ አርባ፣ አቢሲኒያ ባንክ፣ ዳሽን ባንክ፣ ሱሉልታ መዘጋጃ፣ ኪዳነ ምህረት መውጫ ፣ ሱሉልታ ቄራ ፣ ሱሉልታ ስላሴ፣ አለሙ ማደያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00-9፡30
👉 ብሄረ ጽጌ፣ ሳሪስ ነጋ ቦንገር ፣ ስላሴ ቤተክርስቲያን፣ቀይ አፈር፣ ቡራዩ ፣ አኔ ዲማ፣ ወታቤቻ ፣ ሀሙስ ገበያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉 መካኒሳ አርሴማ ቤተክርስቲያን፣ ጀርመን አደባባይ ፣ ጀሞ ሚካኤል፣ አፍሪካ ህንጻ ፣ ዱላ ማርያም ፣
👉 ጭሮ ቤካ፣ ኮራ፣ ኮሞና፣ ጮሮራ፣አንጫር፣ ቦሮዳ፣ ድንድር ፣ ሲዳማ ክልል ይርጋለም፣ ለኩ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ነገ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፡-
✅ከጠዋቱ 11፡00-11፡00
👉ኢዮ ጠቢብ ሆስፒታል፣ አበበ ቢቂላ ስታድየም፣ መድሀኒዓለም ት/ቤት ጀርባ፣ መድሀኒዓለም ኮንዶሚኔም፣ ቦናት እና አካባቢው፣
👉ሸጎሌ ቴሌ፣ ሩፋኤል ፊናንስ፣ አንበሳ ጋራጅ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል ጀርባ፣ ውሃ ጋኑ አካባቢ ( ጎማ አደባባይ) እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡30-10፡30
👉ሱሉልታ መሀል ከተማ ፣ኢንዱስትሪ መንደር ፣ ወሌ ፣ ጎሮ አርባ፣ አቢሲኒያ ባንክ፣ ዳሽን ባንክ፣ ሱሉልታ መዘጋጃ፣ ኪዳነ ምህረት መውጫ ፣ ሱሉልታ ቄራ ፣ ሱሉልታ ስላሴ፣ አለሙ ማደያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00-9፡30
👉 ብሄረ ጽጌ፣ ሳሪስ ነጋ ቦንገር ፣ ስላሴ ቤተክርስቲያን፣ቀይ አፈር፣ ቡራዩ ፣ አኔ ዲማ፣ ወታቤቻ ፣ ሀሙስ ገበያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉 መካኒሳ አርሴማ ቤተክርስቲያን፣ ጀርመን አደባባይ ፣ ጀሞ ሚካኤል፣ አፍሪካ ህንጻ ፣ ዱላ ማርያም ፣
👉 ጭሮ ቤካ፣ ኮራ፣ ኮሞና፣ ጮሮራ፣አንጫር፣ ቦሮዳ፣ ድንድር ፣ ሲዳማ ክልል ይርጋለም፣ ለኩ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤3👍3
በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ጢያ፣ ሱተን እና ኧሽከዲየ ቀበሌዎች የጸጥታ ችግር መከሰቱ ተገለጸ።
በጢያ፣ ሱተን እና ኧሽከዲየ ቀበሌዎች የጸጥታ ችግር መከሰቱን፤ በዚህም ከባድ የጦር መሣሪያ ተኩስ እንደሚሰማና ነዋሪዎች ቀያቸውን ለቀው እየሸሹ መሆኑ ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
የወረዳው የጸጥታ ኃይል በአጥቂዎቹ ጫና ወደ ቡኢ ከተማ ማፈግፈጉን እና አንዳንድ ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቀው ወደ ቡኢ ከተማ መግባታቸውን የአካባቢው ምንጮች ይገልጻሉ።
በተለይ "አቅም-አጠር አረጋውያን፣ እናቶች፣ ሕፃናትና ሕሙማን በግጭቱ መካከል ቀርተዋል" የሚል መረጃ የተሰማ ሲሆን መረጃውም ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
በክስተቱ እስካሁን ምን ያህል የሰው ሕይወት መጥፋቱ ወይም የደረሰውን የጉዳት መጠን ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ሁኔታውን በተመለከተ በይፋ የወጣ መንግሥታዊ መረጃም የለም፡፡ ሆኖም የጸጥታ ችግሩ በፍጥነት እንዲቀረፍና በአካባቢው የሚገኙ ንጹሐን ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ነዋሪዎች እየጠየቁ ነው፡፡
የፌዴራል መንግሥትና የክልሉ የጸጥታ ተቋማት እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅቶች በአካባቢው የሚገኙ ንጹሐንን ለመጠበቅ ፈጣን እርምጃ ይውሰዱ የሚል ጥሪም ቀርቧል።
በዚህ ቀጣና ቀደም ብሎም መሰል የጸጥታ ችግሮች ሲከሰቱ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን አሁን የተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ ችግሩ በተለያየ ጊዜና ቦታ መከሰቱን እንደቀጠለ ለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በጢያ፣ ሱተን እና ኧሽከዲየ ቀበሌዎች የጸጥታ ችግር መከሰቱን፤ በዚህም ከባድ የጦር መሣሪያ ተኩስ እንደሚሰማና ነዋሪዎች ቀያቸውን ለቀው እየሸሹ መሆኑ ከአካባቢው የደረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
የወረዳው የጸጥታ ኃይል በአጥቂዎቹ ጫና ወደ ቡኢ ከተማ ማፈግፈጉን እና አንዳንድ ነዋሪዎችም አካባቢውን ለቀው ወደ ቡኢ ከተማ መግባታቸውን የአካባቢው ምንጮች ይገልጻሉ።
በተለይ "አቅም-አጠር አረጋውያን፣ እናቶች፣ ሕፃናትና ሕሙማን በግጭቱ መካከል ቀርተዋል" የሚል መረጃ የተሰማ ሲሆን መረጃውም ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
በክስተቱ እስካሁን ምን ያህል የሰው ሕይወት መጥፋቱ ወይም የደረሰውን የጉዳት መጠን ማወቅ ያልተቻለ ሲሆን ሁኔታውን በተመለከተ በይፋ የወጣ መንግሥታዊ መረጃም የለም፡፡ ሆኖም የጸጥታ ችግሩ በፍጥነት እንዲቀረፍና በአካባቢው የሚገኙ ንጹሐን ዜጎች ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ነዋሪዎች እየጠየቁ ነው፡፡
የፌዴራል መንግሥትና የክልሉ የጸጥታ ተቋማት እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅቶች በአካባቢው የሚገኙ ንጹሐንን ለመጠበቅ ፈጣን እርምጃ ይውሰዱ የሚል ጥሪም ቀርቧል።
በዚህ ቀጣና ቀደም ብሎም መሰል የጸጥታ ችግሮች ሲከሰቱ መቆየታቸው የሚታወቅ ሲሆን አሁን የተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስ ችግሩ በተለያየ ጊዜና ቦታ መከሰቱን እንደቀጠለ ለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤10👍3🤔1
በኩዌት ኢትዮጵያዊት ሴት በባሏ አሰቃቂ ግድያ ተፈጸመባት
እንደ ኩዌት ታይምስ ዘገባ ከሆነ በኩዌት ጃህራ ግዛት ውስጥ በሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ አንዲት ኢትዮጵያዊት ሴት በገዛ ኢትዮጵያዊ ባለቤቷ በቢላዋ ሶስት ቦታ ተወግታ ህይወቷ አልፏል።
ተጠርጣሪው ባለቤት ወንጀሉን ከፈጸመ በኋላ ከአካባቢው መሰወሩን አቃቤ ህግ እና የወንጀል ምርመራ ቡድን ባደረጉት የመጀመሪያ ደረጃ ማረጋገጫ ታውቋል።
ዘገባው እንደሚያመለክተው የፖሊስ እና የአምቡላንስ ሰራተኞች ጥቆማው እንደደረሳቸው ወዲያውኑ ቦታው ላይ ቢደርሱም የሴቲቱን ህይወት ማዳን አልተቻለም።
የአስከሬን ምርመራ ለማካሄድ እና የሟቿን አካል ለማንሳት አቃቤ ህግ እና የፎረንሲክ ባለሙያዎች በቦታው ተገኝተዋል።
የአካባቢው ፖሊስ የድርጊቱን መንስኤ ለማወቅ እና ከአካባቢው ያመለከተውን ተጠርጣሪ ባለቤት አድኖ ለመያዝ ሰፊ የምርመራ ስራ እየሰራ ይገኛል።
የወንጀሉ አሰቃቂነት በቦታው በነበሩ ነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ድንጋጤን ፈጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
እንደ ኩዌት ታይምስ ዘገባ ከሆነ በኩዌት ጃህራ ግዛት ውስጥ በሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ አንዲት ኢትዮጵያዊት ሴት በገዛ ኢትዮጵያዊ ባለቤቷ በቢላዋ ሶስት ቦታ ተወግታ ህይወቷ አልፏል።
ተጠርጣሪው ባለቤት ወንጀሉን ከፈጸመ በኋላ ከአካባቢው መሰወሩን አቃቤ ህግ እና የወንጀል ምርመራ ቡድን ባደረጉት የመጀመሪያ ደረጃ ማረጋገጫ ታውቋል።
ዘገባው እንደሚያመለክተው የፖሊስ እና የአምቡላንስ ሰራተኞች ጥቆማው እንደደረሳቸው ወዲያውኑ ቦታው ላይ ቢደርሱም የሴቲቱን ህይወት ማዳን አልተቻለም።
የአስከሬን ምርመራ ለማካሄድ እና የሟቿን አካል ለማንሳት አቃቤ ህግ እና የፎረንሲክ ባለሙያዎች በቦታው ተገኝተዋል።
የአካባቢው ፖሊስ የድርጊቱን መንስኤ ለማወቅ እና ከአካባቢው ያመለከተውን ተጠርጣሪ ባለቤት አድኖ ለመያዝ ሰፊ የምርመራ ስራ እየሰራ ይገኛል።
የወንጀሉ አሰቃቂነት በቦታው በነበሩ ነዋሪዎች ዘንድ ትልቅ ድንጋጤን ፈጥሯል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤11😢8👍4
በደቡብ ሱዳን ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ተገደሉ፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስቸኳይ ምርመራ ጠየቀ
ትናንት ሰኞ በደቡብ ሱዳን በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።
ሮይተርስ እንደዘገበው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMISS) ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ሰላም አስከባሪዎቹ መደበኛ የተሽከርካሪ ጥበቃ እና ቅኝት በማድረግ ላይ በነበሩበት ወቅት መሆኑን ገልጿል።
በዚሁ ጥቃት አሰቃቂ ድርጊት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን የገለጸው ድርጅቱ፣ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት በፍጥነት ተለይተው ለሕግ እንዲቀርቡ እና አጣዳፊ ምርመራ እንዲደረግ ጥብቅ ጥሪ አቅርቧል።
እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መረጃ ከሆነ፣ በዚህ ዓመት (2026) ብቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የነበሩ ዘጠኝ የሰላም አስከባሪዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ደቡብ ሱዳን ውስጥ ባለው አለመረጋጋት ምክንያት የሰላም አስከባሪዎች ለከፍተኛ አደጋ እየተጋለጡ ሲሆን፣ ድርጅቱ በአካባቢው ሰላምና ደኅንነት ለማስከበር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ትናንት ሰኞ በደቡብ ሱዳን በተፈጸመ የደፈጣ ጥቃት ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።
ሮይተርስ እንደዘገበው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ (UNMISS) ባወጣው መግለጫ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ሰላም አስከባሪዎቹ መደበኛ የተሽከርካሪ ጥበቃ እና ቅኝት በማድረግ ላይ በነበሩበት ወቅት መሆኑን ገልጿል።
በዚሁ ጥቃት አሰቃቂ ድርጊት የተሰማውን ጥልቅ ኀዘን የገለጸው ድርጅቱ፣ ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት በፍጥነት ተለይተው ለሕግ እንዲቀርቡ እና አጣዳፊ ምርመራ እንዲደረግ ጥብቅ ጥሪ አቅርቧል።
እንደ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መረጃ ከሆነ፣ በዚህ ዓመት (2026) ብቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የነበሩ ዘጠኝ የሰላም አስከባሪዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ደቡብ ሱዳን ውስጥ ባለው አለመረጋጋት ምክንያት የሰላም አስከባሪዎች ለከፍተኛ አደጋ እየተጋለጡ ሲሆን፣ ድርጅቱ በአካባቢው ሰላምና ደኅንነት ለማስከበር የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
❤3😢3