አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
7.45K subscribers
4.47K photos
149 videos
15 files
3.52K links
ለፈጣን መረጃዎች አዲስ ዘይቤ

Twitter : https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Website : https://addiszeybe.com/
YouTube : https://youtube.com/c/AddisZeybe
Instagram : https://bit.ly/3D1tEwC


ስልክ +251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com
Download Telegram
Ustaz Abubeker Ahmed made this statement on an interview he gave to the Ethiopian Press Agency on the stand Egypt is taking regarding the #GERD
በሁለተኛው የአለም ጦርነትን በተለይም የናዚ ጀርመንን የግፍ ጭፍጨፋን ባለማስቆሙ የቀድሞው ሊግ ኦፍ ኔሽንስንን ተክቶ ሰኔ 19፣ 1937 ዓ.ም የተመሰረተው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 75 አመት ሊሞላው ሁለት ቀናት ይቀሩታል። በወቅቱ በአሜሪካዋ ከተማ ሳን ፍራንሲስኮ ከተገኙት 50 መስራች አገራት መካከል፣ ኢትዮጵያ አንዷ ነበረች። ኢትዮጵያን ጨምሮ ግብጽ፣ ላይቤርያና ደቡብ አፍሪካ አህጉሪቷን ወክለው በወቅቱ በሳን ፍራንሲስኮ መገኘታቸው ይታወሳል::

በፎቶው ላይ እንደሚታየው በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው፣ ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የነበሩትን አቶ አክሊሉ ሃብተወልድ ፣ ምክትል የፍትህ ሚኒስተር የነበሩት አቶ አምባይ ወልደማርያም፣ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት ብላታ ኤፍሬም ተወልደ መድህን፣ የትምህርት ሚንስቴር ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ አማኑኤል አብርሃም እንዲሁም የፋይናንስ ሚኒስቴር ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ምናሴ ለማ ኢትዮጵያን በመወከል በስፍራው ተገኝተው ፊርማቸውን ማሳረፋቸውን ታሪክ ያስረዳል።

@addiszeybe
Lake Tana - recognized in UNESCO's World Network of Biosphere Reserves list for its rich biodiversity and significant cultural heritage - has been battling with Emboch since 2011/12. Getu Eristu has invented a machine to help fight the water hyacinth.

Read our web story http://addiszeybe.com/…/meet-getu-the-innovator-the-carpent…

And watch the you tube video https://youtu.be/uqj0mDEgYhA
Ethiopia won the bid to host the African Union by competing against strong contenders like Libya, Nigeria and Kenya. As we enter another decade of hosting the organization it is time to ask how well we are hosting the organization representing the African continent and its 1.26 Billion inhabitants. Bruck Negash did just that read his article by clicking the link http://addiszeybe.com/currentaffairs/featured/addis-ababa-and-the-african-union-meeting-the-standards-of-a-continental-capital
አሃዱ ባንክ የተባለ አዲስ የንግድ ባንክ ተቋቋመ

አሃዱ ባንክ የተባለ አዲስ የንግድ ባንክ ተቋቁሟል። ባንኩ እስካለፈው ሳምንት ድረስ 200 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የአክሲዮን ሽያጭ ያካሄደ ሲሆን አንድ ባለይዞታ መግዛት የሚችለው ትንሹ የድርሻ መጠን 40 ሲሆን በ500 ብር ነጠላ የአክሲዮን ዋጋ እንደሆነ ተገልፅዋል። አንድ ባለአክሲዮን ከፍተኛውን ድርሻ እስከ 20,000,000 ሚሊዮን ብር ሊገዛ ይችላል።

እንደ አዲስ ኢንሳይት ዘገባ በባንክ ፣ በቢዝነስ ፣ በ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ በመስራት እና በግንባታ ልምድ ያላቸው አሥራ ሰባት ሰዎች አሐዱን ያስጀመሩ ሲሆን የቀድሞው የፌዴራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ካሳሁን ኃይለማርያም ከባንኩ መስራቾች አንዱ ነው ። በአሁኑ ጊዜ አማራ ፣ ጎህ ቤቶች ፣ ጃኖ ፣ ዛድ ፣ አሀዱ እና ዘምዘም ባንክን ጨምሮ ከደርዘን በላይ የሆኑ ባንኮች በምስረታ ላይ ይገኛሉ። እናት ባንክ የባንኩን ኢንዱስትሪ ለመጨረሻ ጊዜ የተቀላቀለ ባንክ መሆኑ ይታወሳል።

@addiszeybe
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኘው ራስ አርኪቴክቸር በ ዶመስ የአርኪቴክቸር መፅሄት ከምርጥ 50 የምህንድስና ድርጅቶች ውስጥ ተካተተ።

ራሄል ሻውል በ1991 ከአዲስ አበባ የምህንድስና ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ስትሆን በ1994 አባ አርክቴክት በ2004 ደግሞ ራስ አርክቴክቸርን አቋቁማለች ። የራሄል ሙያ በዘመነ ኢትዮጵያ ባሕላዊና ሙያዊ ዐውድ ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡ ራስ አርክቴክት በአገር ውስጥ አዳዲስ ሕንጻዎች እና ከውጭ ኩባንያዎች ጋር ዓለም አቀፍ ትብብር በማድረግ የግንባታ ንድፍ እንዲሁም የግንባታ ክትትል ሥራዎችን ያከናውናል።

ራሄል አዲስ አበባ በሚገኘው ሮያል ኔዘርላንድስ ኤምባሲ ግምባታ ላይ በነበራት ተሳትፎ የ2007 አጋ ካን ሽልማት ተቀባይ ሆናለች።ከተገነቡ ፕሮጀክቶች መካከል ኤምባሲዎች ፣ ትምህርት ቤቶች ፣ ሆስፒታሎች ፣ ክሊኒኮች ፣ መኖሪያ ቤቶች ፣ ሆቴሎች እና ካምፓኒዎች ፣ ይገኙበታል ። ሁሉም ፕሮጀክት የአካባቢውን እውቀት ተጠቅሞ አዳዲስ ነገሮችን የመሥራትና በዚያ ለሚገኘው አውድ እና መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ትኩረት የመስጠት ዓላማ ያልው ተደርጎ የተሰራ ፕሮጀክት ነው።

ራሄል ፣ ራስ አርክቴክትን በመጠቀም በወንድ ቁጥጥር ሥር ባለው የምህንድስና ኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሠሩ ወጣት ሴት አርክቴክቶችን ለማበረታታት ትሰራለች ። ወጣት ባለሙያዎችን በአጠቃላይ በእውቀት በማካፈልና በተግባር ላይ በተመሠረተ ትምህርትም ታግዛለች። ዶመስ የአርኪቴክቸር መፅሄትም ይህንን ሁሉ ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2020 ምርጥ ሀምሳ የምህንድስና ድርጅቶች ውስጥ ራስ አርኪቴክትን አካትቷል።

@addiszeybe
የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን ለመቋቋም የሚረዳ የሶስት አመት ጥምረት ለመፍጠር ተስማሙ

የተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) እና የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) በኢትዮጵያ በሕፃናትና እናቶች ላይ የሚከሰተውን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ለመከላከል በትምህርት ቤት ላይ የተመሠረተ የተመጣጠነ ምግብና የጤና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል የሦስት ዓመት ጥምረት ፈጥረዋል።

በሦስት ዓመት ውስጥ ሊከናወን የታሰበው የእርዳታ ፕሮግራም በ100 ወረዳዎች ውስጥ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን በ600 ትምህርት ቤቶች ውስጥ የጤናና የተመጣጠነ ምግብ እንዲኖር ይደረጋል። ይህ አካሄድ ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2030 ዓ.ም በህጻናት ላይ የሚታየውን የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ከአስር በመቶ ወደ ሶስት በመቶ ዝቅ ለማድረግ የያዘችውን ግብ ለማሳካት ይረዳል ተብሎ ይገመታል።

ይህ ጥምረት በአፋር፣ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፣ በሶማሌና በትግራይ ክልሎች ለድርቅ ከተጋለጡ መቶ ወረዳዎች ዒላማ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

@addiszeybe
አዲስ ዘይቤ ከወግ ቡና ጋር በመተባበር የህይወት ክህሎትን እና የንግድ ሥራ ችሎታን ለማዳበር የሚጠቅሙ ቪዲዮዎችን በማዘጋጅት ላይ ይገኛል። በዚህ ሳምንት ‘ፐርሰናል ብራንዲንግ’ በሚል ርዕስ የራስን ስብዕና፣ እሴት እና ማንነት መገንባት እንዴት እንደሚቻል የሚያሳየውን የመቅደላ መኩሪያ ከዙም የተቀዳ ቪድዮ እንዲመለከቱ እንጋብዛለን።
https://youtu.be/_SbTbe-xzrM

Other similar videos - ሌሎች ተመሳሳይ ቪዲዮዎች

Habit formation - ልማድ ማዳበር https://youtu.be/fg6gieITYLc

Social business during and post COVID-19 - ማኅበረሰብ አቀፍ የንግድ ሥራ በወረርሽ ወቅትና ከወረርሽኝ በኋላ https://youtu.be/iZ2CPNC9n2U
እስራኤል በአወዛጋቢው የዌስት ባንክ አካባቢ ተጨማሪ መሬት ለመጠቅለል ማቀዷ በቀጠናው ስጋትን ወልዷል

ቢቢሲ በትላንትናው ዕለት ይዞት በወጣው መረጃ፣ የእስራኤል መንግስት በመጪው ክረምት በአወዛጋቢው የዌስት ባንክ አካባቢ ተጨማሪ መሬትን ለመጠቅለል እየተዘጋጀ ስለመሆኑ ዘገቧል። በፈረንጆቹ አመት መጀመርያ በአሜሪካው ፕሬዚደንት አማካኝነት በቀጠናው ያለውን ውጥረት ለማብረድ በቀረበው እቅድ ላይ የተመሰረተ ስለመሆኑ የሚነገርለት የእስራኤል ተጨማሪ መሬትን በዌስት ባንክ የመጠቅለል አጀንዳ በትራምፕ እቅድ በጥርጥር በሚመለከቱት የፊሊስጤም ፖለቲካዊ አመራሮች ዘንድ ተቀባይነት እንደማይኖረውም ዘገባው ጨምሮ አስነብቧል። ዘገባው አክሎም በመጪው ክረምት የኔቴንያሁ መንግስት ሊያጠቃልለው እቅድ ላይ ያለው ግዛት ከዌስት ባንክ ግዛት 3% የሚያክለውን ቢሆንም በመጪዎቹ አመታት እስከ 30 በመቶ ሊደርስ ይችላል በማለት ትንታኔውን አቅርቧል።

በቀጠናው ባለፉት ጥቂት አመታት ከታየው አንጻራዊ ሰላም በኋላም በቀጣይ ወራት ከፍተኛ ውጥረት ሊኖር ይችላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ለፍልስጤም አገር የመሆንን ተስፋ የሚያጨልም እርምጃ ስለመሆኑ በዘገባው ተጠቅሷል። በወቅቱ በዌስት ባንክ ከሁለት ሚልዮን በላይ ፊሊስጤማውያንና 391,000 የሚደርሱ እስራኤላውያን እንደሚኖሩ የሚገመት ሲሆን፣ የዶናልድ ትራምፕ መንግስት ባሳለፍነው ሕዳር በዌስት ባንክ ያለውን የእስራኤል ሰፈራ የአለምአቀፍ ህግን የማይጻጻር አይደለም በማለት አለማቀፉን ማህበረሰብ ማስደመሙ ይታወሳል። @addiszeybe
ከላይ የቀጠለ...

የኔቴንያሁ መንግስት ሊተገበረው ያሰበውን እቅድ ተከትሎም፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ካውንስል ባሳለፍነው ሳምንት እሮብ ባካሄደው ስብሰባ ላይ የህብረቱ ሊቀመንበር አንቶንዮ ጉቲሬዝ በአሜሪካ የሚደገፈውን የግዛት ማስፋፋትና መጠቅለል እቅድ በቀጠናው ያለውን የሰላም ድርድር የሚጎዳ በመሆኑ እስራኤል ይህን እቅዷን እንድትተው ጠይቀው እንደነበረ ይታወሳል። በተጨማሪም የአረብ ሊጉ ሊቀመንበር አህመድ አብል ጌይት የእስራኤል ውሳኔ የፊልስጤማውያንን የራሳቸውን ነጻ አገር የመመስረት የሶስት አስርት አመታት ህልም የሚያጨልም ሲሉ ገልጸውታል።

@addiszeybe
የአፍሪካ ህብረት በመዲናችን አዲስ አበባ የአፍሪካ የበሸታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል (African Center For Disease Control and Prevention) የተሰኘ መጠርያ የያዘ ተቋም ለመመስረት ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ይገኛል። የማእከሉ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ የሚሆን ሲሆን የማእከሉ ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር ተገልጿል። ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ 👇👇

@addiszeybe

http://am.addiszeybe.com/2020/06/26/%e1%8b%a8%e1%8a%a0%e1%8d%8d%e1%88%aa%e1%8a%ab-%e1%8b%a8%e1%89%a0%e1%88%b8%e1%89%b3-%e1%88%98%e1%89%86%e1%8c%a3%e1%8c%a0%e1%88%aa%e1%8b%ab%e1%8a%93-%e1%88%98%e1%8a%a8%e1%88%8b%e1%8a%a8%e1%8b%ab/
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
On this weeks episode of Recap Ethiopia, Wongel Tamene summarizes the major incidents that took place in Ethiopia in the past week. Click the link below to see more 👇

https://www.youtube.com/watch?v=cTIpRsTYjPM
በሶስት ወራት ዉስጥ በአስገድዶ መድፈር በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተባቸዉ 40 መዝገቦች ዉስጥ 8 ዉሳኔ ማገኘታቸዉ ተገለፀ፡፡

በሶስት ወራት ዉስጥ በአስገድዶ መድፈር በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተባቸዉ 40 መዝገቦች ዉስጥ 8 ዉሳኔ ማገኘታቸዉ ተገለፀ፡፡ጠቅላይ አቃቤ ህግ በፌስቡክ ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ መሰረት ከመዝገቦቹ ዉስጥ በዐቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው የ64 ዓመቱ ተከሳሽ በአዲስ አበባ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዕድሜያቸው ስምንት እና ዘጠኝ አመት የሆኑ ሁለት ሴት ህፃናቶችን በተለያዩ ቀናቶች ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ውስጥ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል እንደፈፀመባቸውና ተከሳሹ የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 627(1) ተላልፎ በመገኘቱ አራት ክሶችን እንደተመሰረበት እንዲሁም ተከሳሽ የተከሰሰበትን ክስ ሊያስተባብል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽን በአራቱም ክሶች ጥፋተኛ እንዳደረገ ገልፅዋል፡፡በዚህም ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ60 አመት እንዲቀጣ የፈረደበት ቢሆንም የተከሰሰበት ድንጋጌ ጣሪያው 25 ዓመት በመሆኑ በ 25 አመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ልዩ ቦታው ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ ከህፃንነቷ ጀምሮ ያሳደጋትን የ15 ዓመት የእንጀራ ልጁን የደፈረው ግለሰብ በ11 ዓመት ከ9 ወር ጽኑ እስራት የተቀጣ ሲሆን ቅጣቱም በቂ አይደለም ተብሎ በታመነበት ኪዝ ላይ የይግባኝ ክርክራችን ይቀጥላል ሲል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታውቋል። ጠቅላይ አቃቤ ህግ ባወጣው መግለጫ የተገለትፁት ኬዞች ለአብነት የተገለፁ እንጂ በሌሎች የጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተገቢ የህግ ቅጣት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ ከምንጊዜም በላይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት የኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ለቴሌኮም ፈቃድ ለመስጠት ከአስራ ሁለት ድርጅቶች ጥያቄ ተቀበለ

የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚንስቴር እና የኢትዮጵያ የኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ባሳለፍነው ግንቦት 13 ቀን 2012 ዓም ሁለት የቴሌኮሚኒኬሽን ፈቃድ ለመስጠት የፍላጎት ማስታወቂያ ማውጣታቸው ይታወቃል። ባሳለፍነው ሰኔ 19 ቀን 2012 በኢትዮጵያ የኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ድህረገጽ የወጡ መግለጫዎች እንደሚያመለክቱት ከሆነ ባለስልጣኑ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት አስራ ሁለት የፈቃድ ጥያቄዎችን መሰብሰብ ችሏል። ባለስልጣኑ ለኢትዮጵያ የቴሌኮሙኒኬሽን ገበያ ተስማሚ የሆኑ አገልግሎት ሰጪዎችን ለማግኘት ሲባል የአመልካቾችን ተቋማዊ አደረጃጀት፣ የድርጅቶቹን አለማቀፋዊ ሽፋን፣ በወቅቱ አገልግሎት የሚሰጡባቸውን ሀገራት ዝርዝርና ሌሎች ተጨማሪ መስፈርቶችን መጠቀሙን በግልጽ አስቀምጧል።

ባለስልጣኑ ከተረከባቸው አስራ ሁለት ጥያቄዎች መካከል ዘጠኙ ከቴሌኮም ኦፕሬተሮች እና ሁለቱ የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ካልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ደግሞ ተሟልቶ ያልቀረበ መሆኑን መግለጫው ያስረዳል። ጥያቄውን ካቀረቡ ድርጅቶች መካከል ሳፋሪኮም፣ ቮዳኮምና ቮዳፎን የፈጠሩትን ዓለምአቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያ የተሰኘውን ጥምረት ጨምሮ ኢቲሳላት፣ አክሲያን፣ ኤምቲኤን፣ ኦሬንጅ፣ ሳውዲ ቴሌኮም ኩባንያና ቴሌኮም ደቡብ አፍሪካ ይገኙበታል።

ባለስልጣኑ ጨምሮም የቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ ማሻሻያውን ለማሳካት እና የዲጂታል ሽግግሩን ለማሳለጥ ያለውን ጽኑ አቋም ገልጾ፣ በቀጣይ ምዕራፍ የሚያደርገውን ዝግጅት ለተመራጮች የሚያሳውቅ መሆኑን በመግለጽ በውድድሩ የተሳተፉትን ሁሉ አመስግኗል። የድርጅት መረጣው ሲጠናቀቅ በመንግስት ቁጥጥር ስር የቆየውን የቴሌኮሚኒኬሽን ዘርፍ ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል።

@addiszeybe
የማኅበራዊ ሚድያ ድርጅቱ ትዊተር በኢንተርኔት መዝባሪዎች መጠቃቱን ገለጸ
ገናናው ማኅበራዊ ሚድያ ትዊተር በትላንትናው እለት በኢንተርኔት መዝባሪዎች መጠቃቱን የተለያዩ የሚዲያ ምንጮች በመዘገብ ላይ ይገኛሉ። ከቢትኮይን ጋር የተያያዘ የማታለል ሙከራ ነው የተባለው ድርጊት ራሱን ክሪፕቶፎርሄልዝ (Criptoforhealth) በማለት በሚጠራ ቡድን ስለመካሄዱ ቢቢሲ የዘገበ ሲሆን፤ በጥቃቱ የቀድሞ የአሜሪካ የፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማን ጨምሮ የተለያዩ ታዋቂ ግለሰቦችንና ፖለቲከኞች ገጾች መጠቃታቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።
ከነዚህ ግለሰቦች መካከል በመጪው የአሜሪካ ምርጫ የዲሞክራት ፓርቲን ወክለው የሚወዳደሩት ሴናተር ጆው ባይደን፣ የአማዞን ባለቤት ጄፍ ቤዞስ፣ ታዋቂው ራፐር ካንዬ ዌስትና ባለቤቱ ኪም ካርዳሽያን እንዲሁም ታዋቂ የአለም ሃብታሞች ቢል ጌትስና ኤሎን መስክ የሚጠቀሱ ናቸው።
ጥቃቱ ከላይ የተጠቀሱት አካውንቶች በመጠቀም የተለያዩ መልክቶችን በማስተላለፍ የተደረገ ሲሆን ጥቃቱን የፈጸመው ድርጅት ወንጀሉን የፈጸመው ለበጎ ተግባር መሆኑን በሌላኛው ማኅበራዊ ሚድያ ኢንስታግራም ገልጿል። በግለሰቦቹ ገጽ ላይ የሰፈረው መልዕክት ተጠቃሚዎች በቢትኮይን ገንዘብ እንዲለግሱና ሲለግሱ የሰጡትን እጥፍ መልሰው እንደሚያገኙ የሚገልጽ እንደሆነ መረጃዎች ያስረዳሉ። እስካሁን በወንጀል ድርጊቱ ምን ያህል ገንዘብ እንዳጋበሱ ያልተገለጸ ሲሆን በድህረ ገጽ ወንጀሎች ላይ እንደሚስተዋለው ወንጀለኞቹን ለመያዝ ቀላል እንደማይሆን ይገመታል።
ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ ትዊተር በሰጠው መግለጫ ድርጅቱ የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ስለመሆኑ አስረድቷል። የተለያዩ አካውንቶች ትዊት እንዳያረጉ ከማድረግ አንስቶ የይለፍ ቃልን መቀየርን እስከመከልከል ድረስ የሚደርሱ የደህንነት እርምጃዎችን ስለመውሰዱም ድርጅቱ አስረድቷል።

@addiszeybe
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሃምሌ ወር ተጨማሪ በረራዎችን መልሶ እንደሚጀምር አስታወቀ

በአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ በማለት የሚጠራው ገናናው የኢትዮጰያ አየር መንገድ በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ የተነሳ አቋርጧቸው የነበሩትን በረራዎች ሊጀምር ስለመሆኑ ሲምፕል ፍላዪንግ የተሰኘው መካነ ድር በዛሬው እለት አስነብቧል።

የኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ከተከሰተ ወዲህ መጋቢት 21፣2012 ጀምሮ መዳረሻዎቹን ወደ 19 ቀንሶ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገሪቱ የተቀመጠው የመዘዋወር እገዳ መላላቱን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ መዳረሻዎችን መጓዝ እንደሚጀምር ዘገባው ገልጿል።

ባሳለፍነው ሳምንት ሃምሌ 1 ቀን 2012 ወደ ዱባይ የሚያደርገውን በረራ መልሶ የጀመረው አየር መንገዱ በተጨማሪ ወደተለያዩ ሃገራት የሚያደርጋቸውን ጉዞዎች መልሶ በመጀመር የበረራ መዳረሻዎቹን ወደ 40 ከፍ ለማድረግ መወጠኑን ዘገባው ያስረዳል።

ከአየር መንገዱ የትዊተር ገፅ መረዳት እንደሚቻለው ወደ ለንደን፣ ፓሪስ፣ ፍራንክፈርትና ብራስልስ የሚደረጉት እለታዊ በረራዎች በሃምሌ ወር መልሰው ከተከፈቱ መዳረሻዎች መካከል ይገኛሉ። አየርመንገዱ ወደ ፍራንክፈርትና ለንደን የሚያደርጋቸው በረራዎች በወረርሺኙ ምክንያት ካልተቋረጡት በረራዎች መካከል እንደሆኑ ይታወቃል።

በኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ከመምጣቱ በኋላ እንደሌሎች የበረራ ድርጅቶች ኪሳራን ያስተናገደው የኢትዮጵያ አየርመንገድ የሰሞንኛው የመዘዋወር እገዳ መላላት የተሻለ ጊዜን ለአየር መንገዱ ይዞ ይመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

@addiszeybe
የትግራይ ክልል ምክር ቤት የምርጫ ኮሚሽን አመራሮችን እንደሾመ አስታወቀ

ሐምሌ 9 ቀን 2012 ባካሄደው 5ኛ ዘመን 8ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የትግራይ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስድስተኛውን ክልላዊ ምርጫ የሚያስፈፅሙ የምርጫ ኮሚሽን አመራሮችን ሹመት አፅድቋል።
በዚህም መሰረት ፣ በነሐሴ መገባደጃ ላይ ይካሄዳል የተባለውን ምርጫ እንዲያስፈጽሙ ፣ አቶ ሙሉወርቅ ኪዳነማርያም (መምህር) የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ሆኖው ሲሾሙ ፣ ወይዘሮ ጽጌሬዳ ዲበኩሉ ደግሞ ምክትል ኮሚሽነር ሆነው ተሰይመዋል። መረሳ ጸሃዬ (ተባባሪ ፕ/ር) ፣ ጸጋ ብርሃነ (ዶ/ር) እና አቶ መሀመድ ስዒድ ደግሞ የኮሚሽኑ አባላት ሆነዋል።

@addiszeybe