AACRA
10.7K subscribers
7.96K photos
193 videos
221 files
707 links
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.
Download Telegram
በሀገራዊ ለውጡ ስምንተኛ ዓመት ዋዜማ ላይ፣ በአዲስ አበባ አምስተኛውን የ"አዲስ መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል በይፋ ሥራ አስጀምረናል።

አዲስ አበባ አሁን የደረሰችበት ሁለንተናዊ ለውጥና ዕድገት፣ በለውጡ መንግሥት ቁርጠኝነት የተመዘገቡ የመጋቢት 24 ውጤቶች ናቸው። ከኢትዮጵያ መዲናነት ተሻግራ የአፍሪካ ኩራት የሆነችውን አዲስ አበባን በተግባርም እንደ ስሟ ውብ ለማድረግ፣ የለውጡ መንግሥት ገቢር ያደረጋቸው የልማት ሥራዎች ታሪካዊና ዘመን ተሻጋሪ ስኬትን አስመዝግበዋል።

ከለውጡ መንግሥት ስኬቶች መካከል አንዱ የ"አዲስ መሶብ" ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ነው። የመንግሥት ሥርዓታት በተለዋወጡ ቁጥር ቃል እየተገባ ለመለወጥ ጥረት ቢደረግም፣ ሳይለወጥ ቆይቶ ተገልጋዩን ሲያማርር የኖረውን፣ ስር የሰደደና በተንዛዛ ቢሮክራሲ የተተበተበውን አሰራር ከመሠረቱ የሚቀይር ነው። ጊዜ፣ ወጪና ጉልበት የሚባክንበትን እንዲሁም ጥራትና ቅልጥፍና የራቀውን አገልግሎት አሰጣጥ በተግባር በመለወጥ አዲስ ምዕራፍ መክፈት ተችሏል።

"ማገልገል ክብር ነው" በሚል መርህ በንጹህ የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች፣ በንጹህ አዕምሮ እና በንጹህ እጅ ማገልገልን ይዞ መጥቷል።

ይህ ዛሬ ያስጀመርነው የአዲስ መሶብ ማዕከል፣ መርካቶን ጨምሮ ሰፊ የንግዱ ማህበረሰብ የሚንቀሳቀስበት አካባቢ በመሆኑ፣ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት ረገድ ትልቅ እፎይታን የሚፈጥር ይሆናል።

እያሰፋን ያለነው የዲጂታል የመንግሥት አገልግሎት መስጫ ማዕከል፣ ከከተማችን ነዋሪዎች ባሻገር ለዲፕሎማቶች፣ ለቱሪስቶችና ለኮንፈረንስ ተሳታፊዎች ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ጭምር ነው።

ይህ የአንድ መስኮት ዲጂታል አገልግሎት በታለመለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ለደገፋችሁ በሙሉ፣ በራሴ እና በተገልጋዩ ሕዝብ ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!

Jala bultii waggaa saddeettaffaa jijiirama biyyaalessaa irratti, Finfinneetti giddugala shanaffaa kan ta'e tajaajila dijitaalawaa giddugala tokkoo "Addis Masoob" ifatti hojii eegalchiisnee jirra.
Jijiiramniifi guddinni hundagleessi Finfinneen amma irra geesse, kutannoo mootummaa jijjiiramaatiin kan galmaa'e bu'aalee milkaa'inoota bitooteessa 24 ti. Magaalummaa Itoophiyaa irra ceetee boonicha Afrikaa kan taate Finfinnee qabatamaanis akkuma maqaashee miidhagduu taasisuuf, mootummaan jijjiiramaa hojiiwwan misoomaa hojirra oolchee milkaa'ina seena qabeessaa fi bara cehu galmeessee jira.
Milkaa'inoota mootummaa jijjiiramaa keessaa tokko tajaajila dijitaalawaa giddugala tokkoo"Addis Masoob" dha. Sirnoota mootummaa darban hundaan waadaa galamee jijjiiruuf yaaliin taasifamus, osoo hin jijjiiramni turee tajaajilamtoota rakkisaa kan ture, hidda kan gadi fageeffateefi birookiraasii xaxamaan hoji-maataa lallaaqame bu'uura irraa kan jijjiiruudha. Kenniinsa tajaajilaa yeroo, baasiifi humni itti qisaasa'u akkasumas qulquillinaafi saffisni kan irraa fagaate qabatamaan jijjiiruun boqonnaa haaraa banuun danda'amee jira.
"Tajaajiluun kabaja" mata duree jedhuun bakkeewwan kenniinsa tajaajilaa qulqulluu, sammuu qulqulluu fi harka qulqulluun tajaajiluu qabatee dhufeera. Giddugalli Addis Masoob har'a eegalchiisne kuni, Markaatoo dabalatee naannoo hawaasni daldalaa bal'aan itti socho'u waan ta'eef, tajaajila si'ataafi saffisaa gama kennuutiin haara galfannaa guddaa kan uumu ta'a.
Giddugalli kenniinsa tajaajila mootummaa dijitaalawaan babal'isaa jirru, tuuristootaafi hirmaattota koonfaransiif tajaajila saffisa sadarkaa idil-addunyaa eeggate akka argataniif kan dandeessisuudha.
Tajaajilli dijitaalawaa fooddaa tokkoo kuni yeroo qabameefitti xumuramee tajaajilaaf akka qaqqabu kan deeggartan hundaaf, maqa koofi mqaa uummata tajaajilamaatiin onneerraa galateeffadha.
Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!
5💔1
ለከተማችን ነዋሪዎች ፍትሃዊና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማቅረብ ውጤታማ ስራዎች ተሰርተዋል!

ዶ/ር ጀማሉ ጀምበር (በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፐብሊክ ሰርቪስ እና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ)
አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት የተገልጋዮችን እንግልት በማስቀረት ለነዋሪዎች በቅርበት አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው።

የከተማ አስተዳደሩ ደረጃቸውን የጠበቁ ማዕከላት በሁሉም ክፍለ ከተሞች በፍጥነት ተገንብተው ወደ አገልግሎት እንደሚገቡ በገባው ቃል መሰረት፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የዛሬውን 5ኛ የአዲስ መሶብ አዲስ ከተማ ማዕከል ስታንዳርዱን በጠበቀ መልኩ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል።

በአዲስ መሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት፦በዋና መስሪያ ቤት 22 ተቋማት 140 ዓይነት አገልግሎቶችን እየሰጡ ይገኛሉ። በቅርቡ ወደ ስራ የገቡት 3 የክፍለ ከተማ ማዕከላት ላይ ደግሞ 20 ተቋማት 112 ዓይነት አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ ናቸው። በተበታተነና በተንዛዛ መልኩ ይሰጡ የነበሩ የመንግስት አገልግሎቶችን በማዘመን፣ በተቀናጀ አግባብ በአንድ ማዕከል እንዲሰጡ ማድረግ ተችሏል።

የአዲስ ከተማ "አዲስ መሶብ" የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት በ85 ካውንተሮች አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ በውስጡም፦ምቹ የተገልጋዮች ማረፊያ፣ ቤተ-መጻሕፍት፣ የሕፃናት ማቆያ እና ካፌቴሪያዎችን አካቷል።

አስተዳደሩ በመንግስት ተቋማት የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለቶችን ለማስተካከልና የሕዝቡን ጥያቄ ለመመለስ፣ ባለፉት 3 ዓመታት ሰፋፊ የሪፎርም እና የተቋም ግንባታ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱ ተገልጿል።
4👍1
ዛሬ ከማለዳዉ አንስቶ በአዲስ አበባ በተካሄደዉ የድጋፍ ሰልፍ ላይ የተላለፉ ዋና ዋና መልዕክቶች
• ከመጋቢት ብርሃን ወደ ዓለም አቀፍ ልዕልና!
• በመጋቢት የተገባው ትውልድ ተሻጋሪ ቃል፣ የአዲስ አበባን ልዕልና አረጋግጧል!
• የለውጥ ጮራ ፈንጣቂው አንፀባራቂ ድል!
• መጋቢት ኢትዮጵያን የማላቅ፣ ታሪክን የማደስ የቆራጥነት ወር!
• ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገርነት!
• ከመጋቢት እስከ መጋቢት፤ በትሩፋት የደመቀ፣ በተግባር የተረጋገጠ ጉዞ!
• በፈተና ያልተንበረከከች፣ በመጋቢት የታደሰች ሉዓላዊት ኢትዮጵያ!
• አስተሳሳሪ የወል ትርክታችን ለዘላቂ አንድነትና አብሮነታችን!
• መጋቢት 24 የኢትዮጵያ ከተሞች ትንሳኤ!
• ከአሮጌው ስብራት ወደ አዲስ ከፍታ!
• መጋቢት 24 የአይበገሬዎች መድረክ፣ የከፍታችን መጀመሪያ!
• መጋቢት 24 ለከተማችን ሁለንተናዊ ለውጥ የማይደበዝዝ አሻራ ያኖረ ቀን!
👍32
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ሰው ተኮር የልማት ዕይታዎች፣
የመጋቢት 24 ፍሬዎች!
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የረዳን ፈጣሪ አምላክ የተመሰገነ ይሁን! ዛሬ በታሪካዊቷ መጋቢት 24 ቀን፣ በጉለሌ ክፍለ ከተማ 6ተኛውን ‘አዲስ መሶብ ዲጂታል አንድ ማዕከል’ የመንግሥት አገልግሎት በይፋ አስጀምረናል።
Waaqni nu gargaare haa galatoomu! Har'a guyyaa seena qabeessa bitootessa 24 tti, kutaa magaalaa Gullalleetti 'Addis Masoob' tajaajila mootummaa dijitaalawaa giddugala tokkoo ifatti eegalchiisnee jirra.
5
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በበጀት ዓመቱ 9 ወራት ውስጥ 27.3 ኪሎ ሜትር የፔዳል ሳይክል መንገድ ተገንብቷል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ውስጥ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ 27.3 ኪሎ ሜትር የፔዳል የሳይክል መንገዶችን ገንብቷል፡፡
በከተማዋ በየዓመቱ ጥራታቸውን የጠበቁ የፔዳል የሳይክል መስመሮች ግንባታ እያደገ መምጣቱ ለነዋሪዎች የትራንስፖርት አማራጭ ከመፍጠሩም ባሻገር የዜጎችን ጤንነትን በመጠበቅ ረገድ የጎላ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል፡፡
2
ባለፉት 9 ወራት ከ1 ሺህ 100 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታና ጥገና ስራ ተከናውኗል
መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በአለፉት ዘጠኝ ወራት፤ በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች 1 ሺህ 180 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የመንገድ ግንባታ እና የጥገና ስራዎች አከናወነ፡፡
የበጀት ዓመቱ የ9 ወራት አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር፤ በግንባታ 4.53 በመቶ እና በጥገና 10.25 በመቶ እድገት ተመዝግቧል።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከ 258 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ግንባታና ከ 921 ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ጥገና ሥራዎችን ያከናወነ ሲሆን፤ ይህም የአስፋልት፣ የኮብል ንጣፍ፣ የጠጠር መንገዶች፣ የድሬኔጅ እና የድጋፍ ግንብ ሥራዎችን፣ እንዲሁም የእግረኛና የሳይክል መንገዶች ግንባታ ያካትታል።
በሌላም በኩል፤ የአስፋልትና የኮብል ንጣፍ ጥገና፣ የጠጠር መንገዶች እድሳት፣ የድሬኔጅ መስመሮች ጽዳትና ጥገና፣ የእግረኛ መንገዶች እና ከርቭ ስቶን ስራዎች እንዲሁም የእግረኛ መከላከያ አጥር ጥገና ባለፉት 9 ወራት ከተከናወኑ አበይት ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ባለፉት 9 ወራት በመንገድ ልማት ዘርፍ ላከናወናቸው ሥራዎች ማስፈፀሚያ፤ በጥቅሉ ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ ጥቀም ላይ አውሏል።
👍4