AACRA
10.7K subscribers
8K photos
195 videos
221 files
707 links
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.
Download Telegram
አዲስ አበባ በአምስት አመት ከ 60 ሺ በላይ ፕሮጀክቶችን ገንብታለች !

አዲስ አበባ ከተማ ከለውጡ ወዲህ በተለይም በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ በርካታ ፕሮጀክቶችን በብቃት ሰርታ አጠናቃለች፡፡ በዋናነትም በመሰረተ ልማት እና በመንገድ ግንባታ ከተማዋን የማይመጥን እና አነስተኛ የነበረውን የከተማዋ የመንገድ ስፋት ሌት ተቀን በመስራት ከለውጡ ወዲህ እና ባለፉት አምስት አመታት ጊዜ ውስጥ ከ1ሺ 500 ኪ.ሜ በላይ የመንገድ ግንባታዎችን መገንባት ችላለች፡፡

በተጨማሪም የከተማዋ የውሃ አቅርቦትና አቅም ከነበረበት ላይ 40 በመቶ በመጨመር ሰፊ ስራ መስራት ተችሏል፡፡

ከሁሉም በላይ የህዝቡን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቅረፍ የሚያስችሉና ገቢያውን ለማረጋጋት የሚረዱ የገቢያ ማዕከላትን በማስፋትና በማዘመን አምራችና ሸማቹን በቀጥታ ማስተናገድ የሚያስችሉ 6 የገቢያ ማዕከላትን መገንባት ችለናል፡፡ በተጨማሪም ግዙፍ የግብርና የልህቀት ማዕከል በመገንባት በቀን 60 ሺ እንቁላል ማምረት የማትችል የነበረችው አዲስ አበባ ፤ አሁን ላይ በቀን በሚሊዮን የሚቆጠሩ እንቁላሎችን ማቅረብ ችላለች፡፡

በእነዚህ የልማት ስራዎች ከተሞች የህንፃ ጫካ ብቻ ሳይሆኑ ማምረት የሚችሉ ሁሉን አቀፍ መሆናቸውን አሳይተናል፡፡

በአጠቃለይ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ የውሃ ፣ የደረቅና የፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት እንዲሁም ማህበረሱቡ በከፍተኛ ሁኔታ ጥያቄ ያነሳባቸው የነበሩ እንደ ጤናና የትምህርት ተቋማት ፣ የህፃናት መጫወቻ ሜዳ እና የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያዎች ጨምሮ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ከ60 ሺ በላይ ፕሮጀክቶችን ገንብተን ለህዝባችን አስረክበናል፡፡

ከዚህ ቁጥር ውስጥ 50 በመቶ የሚሆነው ማህበረቡ የልማት ጥሪውን ተቀብሎ በጉልበቱ በገንዘቡ እና በእውቀቱ ተሳትፎ ያደረገባቸው ናቸው ፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1👍1
ኢትዮጵያ- ከሰሃራ በታች ከሚገኙ ሀገራት ቀዳሚ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ባለቤት እንደምትሆን የዓለም-አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ቅድመ-ትንበያውን አስቀምጧል።
በ2026 የፈረንጆችዓመት፣ ኢትዮጵያ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራት በቀዳሚነት ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እንደምታስመዘግብ የዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ትንበያ ያመላክታል። ይኸውም፥ ኢትዮጵያ 9.2% ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድነት እንደምታስመዘግብ ተመላክቷል።
ኢትዮጵያ ከዚህ የላቀ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በላቀ ጥረትና ትጋት እየሰራች እንደሆነ ይታወቃል።
የጎርፍ መከላከል ቅድመ-ዝግጅት ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በዝናብ ወቅት የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋን ለመከላከል የሚያስችል የግንባታ፣ ጥገና እና የውሃ መፋሰሻ መስመሮች ፅዳት ትኩረት ሰጥቶት እየተሰራ መሆኑ ተገልፀጿል፡፡
ይህ የተገለፀው የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ፤ በስሩ ከሚገኙ የተለያዩ ስራ ክፍሎች ጋር የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት ነው፡፡
የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድአወል ሰይድ እንደገለፁት፤ መጪው የክረምት ወቅት ከመግባቱ በፊት፣ ቀሪ የጎርፍ መከላከል ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ በርብርብ እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፤ የመንገድ ዳር የውሃ መፋሰሻ መስመሮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል፤ የጎርፍ ውሃ መውረጃ ቱቦዎችና ቦዮች በደለልና በቆሻሻ እንዳይዘጉ፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በየአካባቢው ማፅዳት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ፤ ጉዳት የደረሰባቸውን የጎርፍ ማስወገጃ መስመሮች ፅዳትና መጠገን፣ በተለያዩ ምክንያቶች ክፍት የሆኑ ማንሆል ክዳኖችን መልሶ በመክደን ለትራፊክ ፍሰቱ ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት አብይ ተግባር መሆኑን ኢንጅነር መሀመድአወል አስታውቀዋል።
1
የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር ተሳታፊ አትሌቶች በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደረጉት ቅድመ ዝግጅት - በምስል
ምስል፦ AMN