ኢትዮጵያ- ከሰሃራ በታች ከሚገኙ ሀገራት ቀዳሚ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ባለቤት እንደምትሆን የዓለም-አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ቅድመ-ትንበያውን አስቀምጧል።
በ2026 የፈረንጆችዓመት፣ ኢትዮጵያ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራት በቀዳሚነት ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እንደምታስመዘግብ የዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ትንበያ ያመላክታል። ይኸውም፥ ኢትዮጵያ 9.2% ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድነት እንደምታስመዘግብ ተመላክቷል።
ኢትዮጵያ ከዚህ የላቀ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በላቀ ጥረትና ትጋት እየሰራች እንደሆነ ይታወቃል።
በ2026 የፈረንጆችዓመት፣ ኢትዮጵያ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራት በቀዳሚነት ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እንደምታስመዘግብ የዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ትንበያ ያመላክታል። ይኸውም፥ ኢትዮጵያ 9.2% ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ዕድነት እንደምታስመዘግብ ተመላክቷል።
ኢትዮጵያ ከዚህ የላቀ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ በላቀ ጥረትና ትጋት እየሰራች እንደሆነ ይታወቃል።
የጎርፍ መከላከል ቅድመ-ዝግጅት ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በዝናብ ወቅት የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋን ለመከላከል የሚያስችል የግንባታ፣ ጥገና እና የውሃ መፋሰሻ መስመሮች ፅዳት ትኩረት ሰጥቶት እየተሰራ መሆኑ ተገልፀጿል፡፡
ይህ የተገለፀው የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ፤ በስሩ ከሚገኙ የተለያዩ ስራ ክፍሎች ጋር የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት ነው፡፡
የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድአወል ሰይድ እንደገለፁት፤ መጪው የክረምት ወቅት ከመግባቱ በፊት፣ ቀሪ የጎርፍ መከላከል ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ በርብርብ እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፤ የመንገድ ዳር የውሃ መፋሰሻ መስመሮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል፤ የጎርፍ ውሃ መውረጃ ቱቦዎችና ቦዮች በደለልና በቆሻሻ እንዳይዘጉ፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በየአካባቢው ማፅዳት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ፤ ጉዳት የደረሰባቸውን የጎርፍ ማስወገጃ መስመሮች ፅዳትና መጠገን፣ በተለያዩ ምክንያቶች ክፍት የሆኑ ማንሆል ክዳኖችን መልሶ በመክደን ለትራፊክ ፍሰቱ ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት አብይ ተግባር መሆኑን ኢንጅነር መሀመድአወል አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በዝናብ ወቅት የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋን ለመከላከል የሚያስችል የግንባታ፣ ጥገና እና የውሃ መፋሰሻ መስመሮች ፅዳት ትኩረት ሰጥቶት እየተሰራ መሆኑ ተገልፀጿል፡፡
ይህ የተገለፀው የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ፤ በስሩ ከሚገኙ የተለያዩ ስራ ክፍሎች ጋር የ9 ወራት እቅድ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት ነው፡፡
የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የመንገድ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድአወል ሰይድ እንደገለፁት፤ መጪው የክረምት ወቅት ከመግባቱ በፊት፣ ቀሪ የጎርፍ መከላከል ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ በርብርብ እንዲሰራ አሳስበዋል፡፡
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፤ የመንገድ ዳር የውሃ መፋሰሻ መስመሮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል፤ የጎርፍ ውሃ መውረጃ ቱቦዎችና ቦዮች በደለልና በቆሻሻ እንዳይዘጉ፤ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በየአካባቢው ማፅዳት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ፤ ጉዳት የደረሰባቸውን የጎርፍ ማስወገጃ መስመሮች ፅዳትና መጠገን፣ በተለያዩ ምክንያቶች ክፍት የሆኑ ማንሆል ክዳኖችን መልሶ በመክደን ለትራፊክ ፍሰቱ ምቹ እንዲሆኑ ማድረግ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት አብይ ተግባር መሆኑን ኢንጅነር መሀመድአወል አስታውቀዋል።
❤1👍1
የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር ተሳታፊ አትሌቶች በአዲስ አበባ ስታዲየም ያደረጉት ቅድመ ዝግጅት - በምስል
ምስል፦ AMN
ምስል፦ AMN
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Addis Ababa Makes History with Its First-Ever Grand Prix!
The inaugural Addis Ababa Grand Prix will take place tomorrow, marking a major milestone in the city’s emergence as a hub for international sporting events and global engagement.
Addis Ababa, The New Face of Africa!
#AddisAbaba
#VisitAddisAbaba
#Sport-tourism
The inaugural Addis Ababa Grand Prix will take place tomorrow, marking a major milestone in the city’s emergence as a hub for international sporting events and global engagement.
Addis Ababa, The New Face of Africa!
#AddisAbaba
#VisitAddisAbaba
#Sport-tourism
አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ዕውን ለማድረግ ፅኑ መሠረት ያስቀመጠች ከተማ!
የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ፣ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ያሳየችውን ልዕልና፣ በስፖርት ቱሪዝም ለመድገም ዝግጁነቷን ለዓለም እየገለጠች ነው። መንግስት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ የሰጠው ትኩረት አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ ረገድ ያላትን አቅም ዕውን እየሆነ ነው።
ይኸውም፥ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ70 በላይ ስመ-ጥር ዓለም-አቀፍ አትሌቶች የሚሳተፉበት የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድርን (Addis Ababa Grand Prix One Day Meeting) ነገ ቅዳሜ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለማስተናገድ መዘጋጀቷ በቂ ማሳያ ነው።
ውድድሩ የአትሌቲክስ እናት የሆነችውን ኢትዮጵያ፣ የዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መዳረሻነት ደረጃዋን ከፍ የሚያደርግ፣ የስፖርት ቱሪዝም መልኅቁን የሚጥልባት እንድትኾን በር ከፉች ነው።
በዚሁ በያዝነው ሚያዝያ ወር ብቻ፣ ከቅዳሜው “የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር” በተጨማሪ ሁለት ዓበይት ዓለማቀፍ ውድድሮች በከተማችን አዲስ አበባ ይከናወናሉ።
ነገ አዲስ አበባ ስታዲየም በዓለም አቀፍ አትሌቶች ብቃት እና በስፖርት አፍቃሪያን ድምቀት ትደምቃለች። ኢትዮጵያ በድጋሚ በአትሌቲክስ የዓለም ማዕከልነቷን ታረጋግጣለች።
የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ፣ በኮንፈረንስ ቱሪዝም ያሳየችውን ልዕልና፣ በስፖርት ቱሪዝም ለመድገም ዝግጁነቷን ለዓለም እየገለጠች ነው። መንግስት ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ የሰጠው ትኩረት አዲስ አበባን ዓለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ ረገድ ያላትን አቅም ዕውን እየሆነ ነው።
ይኸውም፥ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ70 በላይ ስመ-ጥር ዓለም-አቀፍ አትሌቶች የሚሳተፉበት የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድርን (Addis Ababa Grand Prix One Day Meeting) ነገ ቅዳሜ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ለማስተናገድ መዘጋጀቷ በቂ ማሳያ ነው።
ውድድሩ የአትሌቲክስ እናት የሆነችውን ኢትዮጵያ፣ የዓለም አቀፍ ስፖርታዊ መዳረሻነት ደረጃዋን ከፍ የሚያደርግ፣ የስፖርት ቱሪዝም መልኅቁን የሚጥልባት እንድትኾን በር ከፉች ነው።
በዚሁ በያዝነው ሚያዝያ ወር ብቻ፣ ከቅዳሜው “የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር” በተጨማሪ ሁለት ዓበይት ዓለማቀፍ ውድድሮች በከተማችን አዲስ አበባ ይከናወናሉ።
ነገ አዲስ አበባ ስታዲየም በዓለም አቀፍ አትሌቶች ብቃት እና በስፖርት አፍቃሪያን ድምቀት ትደምቃለች። ኢትዮጵያ በድጋሚ በአትሌቲክስ የዓለም ማዕከልነቷን ታረጋግጣለች።
👍2