AACRA
10.7K subscribers
7.98K photos
195 videos
221 files
707 links
Addis Ababa City Roads Authority (AACRA) is a government organization under the Addis Ababa City Adminstration. It was established on March 1998 with the aim of realizing sustainable road infrastructure and creating interchangeable road transport to A.A.
Download Telegram
የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ መንደር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በገላን ጉራ ኢንዱስትሪ መንደር የአስፓልት መንገድ ግንባታ በማከናወን ላይ ይገኛል።

በባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ የራስ ኃይል እየተገነባ የሚገኘው ይህ የውስጥ ለውስጥ መንገድ በዘጠቃላይ 1.3 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ነው፡፡

አሁን ላይ ሰቤዝ የማንጠፍ ስራ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን፤ የመንገድ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ፤ የኢንዱስትሪ መንደሩ የሥራ እንቅስቃሴ እንዲቀላጠፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይጠበቃል፡፡

የፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን የባለሥልጣን መስሪያቤቱ የደቡብ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡
4
የምርጫ ካርድ ወስደዋል?
ባሉበት ሆነው በ*ምርጫዬ” የሞባይል መተግበሪያ ወይም ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ በኖሩበት አካባቢ በሚገኝ የምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቀላሉ መመዝገብ ይችላሉ።
የዛሬው ካርድዎ የነገዋን ታላቂቷን ኢትዮጵያ መገንቢያ ዋነኛ መሣሪያ ነው!
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቀይ ባሕር ከኛ በላይ ለማን አጀንዳ ይሆናል?
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
👍21
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ
መዲናችን ለስፖርት ዘርፉ በሰጠችዉ ልዩ ትኩረት እና ባስመዘገበቻቸዉ የልማት ስኬቶች በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረክ ተመራጭ እንድትሆን አስችሏታል፡፡

ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ በመዲናችን አዲስ አበባ የስፖርቱን ዘርፍ ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት በርካታ ውጤታማ ተግባራት በመከናወናቸዉ የከተማዋን የስፖርት ገጽታ ከመቀየር፤ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስሮችን ከማጠናከር ባሻገር በዓለም አቀፍ የስፖርት መድረክ ተመራጭ እንድትሆን አስችለዋታል፡፡

ከ1,589 በላይ ደረጃቸዉን የጠበቁ ዘመናዊ እና ምቹ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች በከተማዋ የተገነቡ ሲሆን ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት አኳያም በከተማዋ በሚገኙ 11ዱም ክፍለ ከተሞች 723 የታዳጊ ወጣቶች የስፖርት ስልጠና ጣቢያዎችን ተመርቀዉ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

በመዲናዋ ያሉ የስፖርት መሰረተ ልማቶች በተለያዩ የእድሜ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ታዳጊ ህፃናት እና ወጣቶች፤ለባለሙያዎች እና ለስፖርተኞች እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚዘጋጁ ስፖርታዊ ዉድድሮች ጭምር ታሳቢ ተደርገዉ የለሙ የእግር ኳስ፤የእጅ ኳስ፤የቅርጫት ኳስ፤የሜዳ ቴኒስ፤የመዋኛ ገንዳ፤የቤት ውስጥና የውጪ ጂም፣ የዌልነስ ሴንተር እና የአጭር እርቀት የመሮጫ ትራኮች ዘመናዊና ባህላዊ የመጫወቻ ስፍራዎች እና የአሸዋ ላይ ስፖርት ሜዳዎች የተካተተባቸዉ የዘርፉ የስኬት ማሳያዎች ናቸዉ፡፡

ትዉልድ በአካልና በአዕምሮ እንዲታነፅ ታሳቢ ተደርገው የተገነቡ የስፖርት ማዘዉተሪያዎች በስፖርት ማዘዉተሪያ ቦታዎች እጥረት ምክንያት ወጣቶች በመኪና መንገዶች ላይ በመጫወት የሚደርስባቸዉን አደጋ በመቀነስ፤ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስርን በማጠናከር፤ለከተማዋም ሆነ ለሀገር የሚተርፉ የስፖርት ተሰጥኦ ያላቸው ወጣቶችን በየደረጃው እንዲወጡ በማስቻል ጤናማና አምራች ዜጋን ለመፍጠር የተያዘው ግብ ተጨባጭ ውጤቶች እንዲመዘገቡ አስችሏል፡፡

በመሆኑም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመዲናችን አዲስ አበባ ሶስት ዓለም አቀፍ ሲቲ ማውንቴን ባይክ ኢሊሚኔተር ዓለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር፣ ግራንድ ኢትዮጵያን ረን እና የአትሌቲክስ ውድድሮችን ለማዘጋጀት ተመራጭ እንድትሆን አስችሏታል፡፡

ይህ የተቀናጀ የልማት ዘርፍ ከተማ አስተዳደሩ በዓለም አቀፍ ግንኙነት፤በስፖርት ዲፕሎማሲ እና በስፖርት መሰረተ-ልማት መስፋፋት ላከናወናቸዉ ስኬቶች አንዱ ተጨባጭ እዉነታ ነዉ፡
2
አዲስ አበባ በአምስት አመት ከ 60 ሺ በላይ ፕሮጀክቶችን ገንብታለች !

አዲስ አበባ ከተማ ከለውጡ ወዲህ በተለይም በአምስት አመታት ጊዜ ውስጥ በርካታ ፕሮጀክቶችን በብቃት ሰርታ አጠናቃለች፡፡ በዋናነትም በመሰረተ ልማት እና በመንገድ ግንባታ ከተማዋን የማይመጥን እና አነስተኛ የነበረውን የከተማዋ የመንገድ ስፋት ሌት ተቀን በመስራት ከለውጡ ወዲህ እና ባለፉት አምስት አመታት ጊዜ ውስጥ ከ1ሺ 500 ኪ.ሜ በላይ የመንገድ ግንባታዎችን መገንባት ችላለች፡፡

በተጨማሪም የከተማዋ የውሃ አቅርቦትና አቅም ከነበረበት ላይ 40 በመቶ በመጨመር ሰፊ ስራ መስራት ተችሏል፡፡

ከሁሉም በላይ የህዝቡን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቅረፍ የሚያስችሉና ገቢያውን ለማረጋጋት የሚረዱ የገቢያ ማዕከላትን በማስፋትና በማዘመን አምራችና ሸማቹን በቀጥታ ማስተናገድ የሚያስችሉ 6 የገቢያ ማዕከላትን መገንባት ችለናል፡፡ በተጨማሪም ግዙፍ የግብርና የልህቀት ማዕከል በመገንባት በቀን 60 ሺ እንቁላል ማምረት የማትችል የነበረችው አዲስ አበባ ፤ አሁን ላይ በቀን በሚሊዮን የሚቆጠሩ እንቁላሎችን ማቅረብ ችላለች፡፡

በእነዚህ የልማት ስራዎች ከተሞች የህንፃ ጫካ ብቻ ሳይሆኑ ማምረት የሚችሉ ሁሉን አቀፍ መሆናቸውን አሳይተናል፡፡

በአጠቃለይ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ የውሃ ፣ የደረቅና የፍሳሽ ቆሻሻ አወጋገድ ስርዓት እንዲሁም ማህበረሱቡ በከፍተኛ ሁኔታ ጥያቄ ያነሳባቸው የነበሩ እንደ ጤናና የትምህርት ተቋማት ፣ የህፃናት መጫወቻ ሜዳ እና የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያዎች ጨምሮ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ከ60 ሺ በላይ ፕሮጀክቶችን ገንብተን ለህዝባችን አስረክበናል፡፡

ከዚህ ቁጥር ውስጥ 50 በመቶ የሚሆነው ማህበረቡ የልማት ጥሪውን ተቀብሎ በጉልበቱ በገንዘቡ እና በእውቀቱ ተሳትፎ ያደረገባቸው ናቸው ፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ
1👍1