የፋኑኤል፣ በረከቴና ወታደር ሰፈር ሎት 2 የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ በመከናወን ላይ ነው
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ የፋኑኤል፣ በረከቴና ወታደር ሰፈር ሎት 2 የአስፓልት መንገድ ግንባታ እያካሄደ ይገኛል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ ቀደም ሲል በድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ሲከናወነ የቆየ ቢሆንም፤ ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ በፍጥነት ባለመከናወኑ፤ የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ለህብረተሰቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የኮንትራት ውሉን በማቋረጥ፤ አሁን ላይ በማህበራትና በራስ ኃይል ግንባታው በማከናወን ላይ ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 2.86 ኪሎ ሜትር ርዝመትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ከ16 እስከ 20 ሜትር የሚደርስ የጎን ስፋት የሚሸፍን ሲሆን፤ አሁን ላይ የቁፋሮና የገረጋንቲ ሙሌት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም 700 ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው ከፋኑኤል ኮንዶሚኒየም - ስልጤ ሰፈር - ዓለም ባንክ የሚወስደውን መንገድ ግንባታ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ፣ ከፋኑኤል ኮንዶሚኒየም - በረከቴና ወታደር ሰፈርን አቋርጦ እስከ ዓለም ባንክ ያለውን የትራፊክ ፍሰት በማሳለጥ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ለረጅም ጊዜ ሲያነሱት ለነበረው የትራንስፖርትና የመሠረተ ልማት ጥያቄ ዘላቂ መፍትሄ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ የፋኑኤል፣ በረከቴና ወታደር ሰፈር ሎት 2 የአስፓልት መንገድ ግንባታ እያካሄደ ይገኛል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ ቀደም ሲል በድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ሲከናወነ የቆየ ቢሆንም፤ ግንባታው በተያዘለት የጊዜ ገደብ በፍጥነት ባለመከናወኑ፤ የህብረተሰቡ የረጅም ጊዜ ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ለህብረተሰቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የኮንትራት ውሉን በማቋረጥ፤ አሁን ላይ በማህበራትና በራስ ኃይል ግንባታው በማከናወን ላይ ነው፡፡
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 2.86 ኪሎ ሜትር ርዝመትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ከ16 እስከ 20 ሜትር የሚደርስ የጎን ስፋት የሚሸፍን ሲሆን፤ አሁን ላይ የቁፋሮና የገረጋንቲ ሙሌት ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም 700 ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው ከፋኑኤል ኮንዶሚኒየም - ስልጤ ሰፈር - ዓለም ባንክ የሚወስደውን መንገድ ግንባታ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ፣ ከፋኑኤል ኮንዶሚኒየም - በረከቴና ወታደር ሰፈርን አቋርጦ እስከ ዓለም ባንክ ያለውን የትራፊክ ፍሰት በማሳለጥ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ለረጅም ጊዜ ሲያነሱት ለነበረው የትራንስፖርትና የመሠረተ ልማት ጥያቄ ዘላቂ መፍትሄ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
❤4👍4
አዲስ አበባ ስሟን መሆን የቻለችበት እጅግ ፈጣን፣ ሁለንተናዊ ለውጥ - ቃልን በተግባር!
አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ ለማድረግ ባቀድነው መሠረት፣ በ24/7 የተለወጠ የሥራ ባሕል፣ በትጋት እና ታማኝነት ከተማችንን በሁሉም መስፈርቶች ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን የላቀ መዲና የማድረግ ሕልማችን በአስተማማኝ መንገድ ላይ ነው።
ከተማችን እየተገበረች ባለችው ሁለንተናዊ ልማት ለሁሉም የምትመች፣ ሁሉንም በፍትሀዊነት የምታገለግል ፣ ማንንም ያልዘነጋች የአካታች ልማት ማሳያ ከተማ እያደረግናት ነው።
ለሕፃናት፣ ለወጣቶች፣ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች፣ ለእግረኛው፣ ለባለ መኪናውና ለባለ ሳይክሉ የትራንስፖርት አማራጮችንና መሠረተ-ልማቶችን በፍትሐዊነት ያመቻቸች፤ ለስማርት ከተማነት፣ ለአገልግሎት አሰጣጥ፣ ለሸማቹ፣ ለባለሀብቱ ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን የፈጠረች እና የኮፍረንስ ቱሪዚም ማዕከል ከተማ እየሆነች ነው።
ብዝሃ የምርት አቅርቦትን ለሸማቹ የሚያቀርቡ ተደራሽ የገበያ ማዕከላት፣ ሸማች ብቻ ሳሆን አምራችም እየሆነች የመጣችበት እንዲሁም የትናንት ቀደምቶች ታሪክና አሸናፊነትን ከዛሬና ከነገ ጋር የሚያስተሳስሩ እንደ አድዋ ድል ሙዚየም፣ የአብረሆት የእውቀት መሸመቻ ማዕከል፣ አስደናቂ አረንጓዴ የሕዝብ መዝናኛ ስፍራዎችና የአደባባይ የኪነ-ጥበብ ትዕይንት ማቅረቢያዎችን አካትታ፤ የዲፕሎማሲ፣ የብዝሃ ማንነት፣ የብዝሃ ባህል ድምቀት እና የጠንካራ የአንድነት ማዕከል “አዲስ አበባ “የሁላችንም ከተማ ናት ።
በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባን የኢትዮጵያ የብልጽግና ተምሳሌት ከማድረግ ባሻገር፣ የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬ መሆኑን በአዲስ አበባ ልማት በተግባር እያስመሰከርን እንገኛለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ ለማድረግ ባቀድነው መሠረት፣ በ24/7 የተለወጠ የሥራ ባሕል፣ በትጋት እና ታማኝነት ከተማችንን በሁሉም መስፈርቶች ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቷን የላቀ መዲና የማድረግ ሕልማችን በአስተማማኝ መንገድ ላይ ነው።
ከተማችን እየተገበረች ባለችው ሁለንተናዊ ልማት ለሁሉም የምትመች፣ ሁሉንም በፍትሀዊነት የምታገለግል ፣ ማንንም ያልዘነጋች የአካታች ልማት ማሳያ ከተማ እያደረግናት ነው።
ለሕፃናት፣ ለወጣቶች፣ ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች፣ ለእግረኛው፣ ለባለ መኪናውና ለባለ ሳይክሉ የትራንስፖርት አማራጮችንና መሠረተ-ልማቶችን በፍትሐዊነት ያመቻቸች፤ ለስማርት ከተማነት፣ ለአገልግሎት አሰጣጥ፣ ለሸማቹ፣ ለባለሀብቱ ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታን የፈጠረች እና የኮፍረንስ ቱሪዚም ማዕከል ከተማ እየሆነች ነው።
ብዝሃ የምርት አቅርቦትን ለሸማቹ የሚያቀርቡ ተደራሽ የገበያ ማዕከላት፣ ሸማች ብቻ ሳሆን አምራችም እየሆነች የመጣችበት እንዲሁም የትናንት ቀደምቶች ታሪክና አሸናፊነትን ከዛሬና ከነገ ጋር የሚያስተሳስሩ እንደ አድዋ ድል ሙዚየም፣ የአብረሆት የእውቀት መሸመቻ ማዕከል፣ አስደናቂ አረንጓዴ የሕዝብ መዝናኛ ስፍራዎችና የአደባባይ የኪነ-ጥበብ ትዕይንት ማቅረቢያዎችን አካትታ፤ የዲፕሎማሲ፣ የብዝሃ ማንነት፣ የብዝሃ ባህል ድምቀት እና የጠንካራ የአንድነት ማዕከል “አዲስ አበባ “የሁላችንም ከተማ ናት ።
በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባን የኢትዮጵያ የብልጽግና ተምሳሌት ከማድረግ ባሻገር፣ የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬ መሆኑን በአዲስ አበባ ልማት በተግባር እያስመሰከርን እንገኛለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
❤6
"የበርካቶችን ሸክም ያቀለሉ፣ የነገ ተስፋን ያበሩ ሰው ተኮር የመጋቢት ፍሬዎች!"
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም፣ የለውጡ መንግስት ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ያደረገበት ታሪካዊ ቀን ሲሆን መንግስት ሀገራዊ ኃላፊነቱን ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ "ሰው ተኮር" ስራዎችን ዋነኛ መገለጫው በማድረግ፣ የዜጎችን ማህበራዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመቅረፍ ያለሙ ዘርፈ-ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመደገፍ፣ በበጋና ክረምት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች ፤-የቤት ዕድሳት፣ የተስፋ ብርሀን ምገባ ማዕከላት ማስፋፋት፣ የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም፣ ማዕድ ማጋራት እና ሌሎች መሰል ተግባራትን ተቋማዊ በሆነ መልኩ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራባቸዉ የበርካቶችን ሸክም ያቀለሉ፣ የነገ ተስፋን ያበሩ ሰው ተኮር የመጋቢት ፍሬ ዉጤቶች ናቸዉ፡፡
በተጨማሪም እንደ “የነገዋ” ያሉ የነገን ብሩህ ተስፋ የሚያሰንቁ የሴቶች የክህሎት ማበልፀጊያ እና የስነ-ልቦና ድጋፍ የሚሰጡ ማዕከላትን በመገንባት ሙያዊ ክህሎት በማስጨበጥ እና ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ እህቶቻችን ነገአቸውን እንዲያልሙ በዚህም ተስፋቸው እንዲገለጥ እና እፎይታን እንዲጎናፀፉ ማድረግ መቻሉ ሌላዉ ማሳያ ነዉ፡፡
በሌላ በኩልም ከውጭ ለሚመጡ ስደተኞች ዜጋ ተኮር ፖሊሲ በመቅረፅ ህይወታቸዉ በአዲስ መልክ እንዲለወጥ፤የሃገር እና የወገን ኩራት ስሜት እንዲያድርባቸዉ በሚያስችላቸዉ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ ማድረግ መጀመሩ መንግስት ለዜጎች ክብር የሰጠዉ መገለጫ ነዉ ማለት ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ እነዚህን በመሳሰሉት እና ሰው ላይ ኢንቨስት የማድረግ ቀዳሚ ጉዳዮች ለሀገር የወደፊት ተስፋ መሰረት ነው በሚል እሳቤ እየተከናወኑ የሚገኙ ሸክም አቅላይ፣ እፎይታ ሰጪ “ሰው ተኮር” ስራዎች ዛሬ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም የበለጠ ተጠናክረዉ የሚቀጥሉ የመጋቢት ፍሬዎች እና አሳቤዎች ናቸው፡፡
መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም፣ የለውጡ መንግስት ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ያደረገበት ታሪካዊ ቀን ሲሆን መንግስት ሀገራዊ ኃላፊነቱን ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ "ሰው ተኮር" ስራዎችን ዋነኛ መገለጫው በማድረግ፣ የዜጎችን ማህበራዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመቅረፍ ያለሙ ዘርፈ-ብዙ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ዜጎችን ለመደገፍ፣ በበጋና ክረምት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች ፤-የቤት ዕድሳት፣ የተስፋ ብርሀን ምገባ ማዕከላት ማስፋፋት፣ የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም፣ ማዕድ ማጋራት እና ሌሎች መሰል ተግባራትን ተቋማዊ በሆነ መልኩ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራባቸዉ የበርካቶችን ሸክም ያቀለሉ፣ የነገ ተስፋን ያበሩ ሰው ተኮር የመጋቢት ፍሬ ዉጤቶች ናቸዉ፡፡
በተጨማሪም እንደ “የነገዋ” ያሉ የነገን ብሩህ ተስፋ የሚያሰንቁ የሴቶች የክህሎት ማበልፀጊያ እና የስነ-ልቦና ድጋፍ የሚሰጡ ማዕከላትን በመገንባት ሙያዊ ክህሎት በማስጨበጥ እና ወደ ስራ እንዲገቡ በማድረግ እህቶቻችን ነገአቸውን እንዲያልሙ በዚህም ተስፋቸው እንዲገለጥ እና እፎይታን እንዲጎናፀፉ ማድረግ መቻሉ ሌላዉ ማሳያ ነዉ፡፡
በሌላ በኩልም ከውጭ ለሚመጡ ስደተኞች ዜጋ ተኮር ፖሊሲ በመቅረፅ ህይወታቸዉ በአዲስ መልክ እንዲለወጥ፤የሃገር እና የወገን ኩራት ስሜት እንዲያድርባቸዉ በሚያስችላቸዉ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ ማድረግ መጀመሩ መንግስት ለዜጎች ክብር የሰጠዉ መገለጫ ነዉ ማለት ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ እነዚህን በመሳሰሉት እና ሰው ላይ ኢንቨስት የማድረግ ቀዳሚ ጉዳዮች ለሀገር የወደፊት ተስፋ መሰረት ነው በሚል እሳቤ እየተከናወኑ የሚገኙ ሸክም አቅላይ፣ እፎይታ ሰጪ “ሰው ተኮር” ስራዎች ዛሬ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም የበለጠ ተጠናክረዉ የሚቀጥሉ የመጋቢት ፍሬዎች እና አሳቤዎች ናቸው፡፡
❤2