Addis Ababa City land Development And Administration Bureau
5.08K subscribers
6.29K photos
66 videos
18 files
256 links
Download Telegram
በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ የምርጫ ክልሎችና የምርጫ ጣቢያዎች ከ12፡00 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘዉ የነበሩ መራጮች ድምጽ እየሰጡ ነዉ
1
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!

ከማለዳ ጀምሮ ድምፁን በመስጠት ላይ የሚገኘው የከተማችን ክንደ ብርቱ ህዝብ አሁንም በተፈጠረው የሲስተም መስተጓገል ሳይበገር፣ ምርጫ ቦርድ በሰጠው የሰዓት ማሻሻያ በመጠቀም ድምፁን ለመስጠት በየምርጫ ጣቢያው በፅናት እንደቆመ ነው::

ይህም ዲሞክራሲ የማፅናት ተምሳሌትነት ጉዞ ማሳያ ነው::

#ኢትዮጵያእየመረጠችነው
#አዲስአበባእየመረጠችነው
1
ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው!
አዲስ አበባ እየመረጠች ነው!

የከተማችን ነዋሪዎች ድምፅ የመስጠት፥ ዴሞክራሲን የማፅናት ቁርጠኝነት፣ የዜግነት ድርሻ ለመወጣት ትጋት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች እየታየ ነው።

ከማለዳ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ 7ኛውን ህገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ ለመስጠት አሁንም በአዲስ አበባ በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች የምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ቀጥሏል፡፡

#በምርጫ_ብቻ