ሲንከባለል የመጣውን የአርሶ አደሩን የይዞታ መብታ ፈጠራ ጥያቄ ለመመለስ በሐምሌ ወር ብቻ ከ1ሺህ 700 በላይ ካርታ መዘጋጀቱን በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ ገለፀ።
ዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የሐምሌ ወር እቅድ አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ተመላክቷል።
ነሀሴ 15/2017) (መልአ)፦
************
በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የሐምሌ ወር እቅድ አፈፃፀም የማዕከልና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት በመገምገም በቀጣይ ልዩ ትኩረት የሚሹ ተግባራትን ተመላክተዋል ።
በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ውጤት ካስመዘገቡ ዘርፎች አንዱ የሆነው የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት በተያዘው አዲሱ የስራ ዘመን በየወሩ የግምገማ መድረክ በማዘጋጀት በአፈፃፀም ወቅት የተስተዋሉ ውስንነቶችን በማረምና የተገኙ ተሞክሮችን በማስፋት ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል ።
ዘርፉ በዛሬው እለትም የሐምሌ ወር የአበይት ተግባራት አፈፃፀሞችን ገምግሟል በዚህ መሰረት በሐምሌ ወር ብቻ ከ1ሺህ 700 በላይ የአርሶ አደር የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ማዘጋጀት መቻሉን የአፈፃፀም ሪፖርቱን ያቀረቡት የይዞታ አገልግሎት ማስተካከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋሚካኤል እንዳለ ተናግረዋል ።
የአፈፃፀም መድረኩን የመሩት የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር ወንድወሰን ባንጃው በበኩላቸው ለተገኘው ውጤት እውቅና ሰጥተው የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት ከቴክኒክ ክህሎት ባሻገር ቅን ልቦና በመላበስ ለተገልጋዮች በተቀመጠው ስታንደርድ መሰረት ከሌብነት የፀዳ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ኃላፊው የሙያ ስነምግባቸውን አክብረው የጠራ አገልግሎት ተደራሽ የሚያደርጉ ባለሙያዎችን በግምገማ በመለየት የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ ገልፀው በሌብነት ተግባራት ላይ በሚሳተፉ ሰራተኞች ላይ ደግሞ አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድ አስገንዝበዋል ።
ኢ/ር ወንድወሰን አክለውም በቀጣይ ለአርሶ አደር መብት ፈጠራና ለገቢ አሰባሰብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ የስራ መመሪያ ተሰጥተዋል ።
በመድረኩ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የአርሶ አደር መብት ፈጠራ ጨምሮ በሌሎች አበይት ተግባራት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ባለሙያዎች የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጠ ሲሆን አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ እንዲረዳ በየደረጃው ከሚገኙ የስራ ክፍሎች ጋር የቃል ኪዳን ትስስር ሰነድ ተፈራርመዋል ።
ለበለጠ መረጃ የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇👇👇👇👇👇
Website:- https://www.aalb.gov.et
Face book :-Addis Ababa City Land Development Administration and Bureau
Email ፦addisabababacityland@gmail.com
Telegram ፦https://t.me/AddisLand
Youtube፦https://www.youtube.com/@AddisAbabaCityLandDevelopment
Tiktok.https፦//www.tiktok.com/@aa.land.administrator?_t=ZM-8uSveGuoY8T&_r=1
Instagram፥https://www.instagram.com/addisababa
ዘርፉ የ2018 በጀት ዓመት የሐምሌ ወር እቅድ አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች ተመላክቷል።
ነሀሴ 15/2017) (መልአ)፦
************
በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ የ2018 በጀት ዓመት የሐምሌ ወር እቅድ አፈፃፀም የማዕከልና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት በመገምገም በቀጣይ ልዩ ትኩረት የሚሹ ተግባራትን ተመላክተዋል ።
በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ውጤት ካስመዘገቡ ዘርፎች አንዱ የሆነው የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት በተያዘው አዲሱ የስራ ዘመን በየወሩ የግምገማ መድረክ በማዘጋጀት በአፈፃፀም ወቅት የተስተዋሉ ውስንነቶችን በማረምና የተገኙ ተሞክሮችን በማስፋት ለተገልጋዮች ቀልጣፋ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል ።
ዘርፉ በዛሬው እለትም የሐምሌ ወር የአበይት ተግባራት አፈፃፀሞችን ገምግሟል በዚህ መሰረት በሐምሌ ወር ብቻ ከ1ሺህ 700 በላይ የአርሶ አደር የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ማዘጋጀት መቻሉን የአፈፃፀም ሪፖርቱን ያቀረቡት የይዞታ አገልግሎት ማስተካከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋሚካኤል እንዳለ ተናግረዋል ።
የአፈፃፀም መድረኩን የመሩት የመብት ፈጠራና ይዞታ አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኢ/ር ወንድወሰን ባንጃው በበኩላቸው ለተገኘው ውጤት እውቅና ሰጥተው የተሳለጠ አገልግሎት ለመስጠት ከቴክኒክ ክህሎት ባሻገር ቅን ልቦና በመላበስ ለተገልጋዮች በተቀመጠው ስታንደርድ መሰረት ከሌብነት የፀዳ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ኃላፊው የሙያ ስነምግባቸውን አክብረው የጠራ አገልግሎት ተደራሽ የሚያደርጉ ባለሙያዎችን በግምገማ በመለየት የማበረታታት ስራ እንደሚሰራ ገልፀው በሌብነት ተግባራት ላይ በሚሳተፉ ሰራተኞች ላይ ደግሞ አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድ አስገንዝበዋል ።
ኢ/ር ወንድወሰን አክለውም በቀጣይ ለአርሶ አደር መብት ፈጠራና ለገቢ አሰባሰብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ የስራ መመሪያ ተሰጥተዋል ።
በመድረኩ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የአርሶ አደር መብት ፈጠራ ጨምሮ በሌሎች አበይት ተግባራት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ ባለሙያዎች የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጠ ሲሆን አገልግሎት አሰጣጡን ለማሳለጥ እንዲረዳ በየደረጃው ከሚገኙ የስራ ክፍሎች ጋር የቃል ኪዳን ትስስር ሰነድ ተፈራርመዋል ።
ለበለጠ መረጃ የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇👇👇👇👇👇
Website:- https://www.aalb.gov.et
Face book :-Addis Ababa City Land Development Administration and Bureau
Email ፦addisabababacityland@gmail.com
Telegram ፦https://t.me/AddisLand
Youtube፦https://www.youtube.com/@AddisAbabaCityLandDevelopment
Tiktok.https፦//www.tiktok.com/@aa.land.administrator?_t=ZM-8uSveGuoY8T&_r=1
Instagram፥https://www.instagram.com/addisababa
❤4👍2
ስድስተኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ ተጠናቀቀ።
ለሦስተ ተከታታይ ቀናት ሲካሄ በቆየው በዚህ ጨረታ
በጨረታ ኮሚቴ አባላት በተደረገው ማጣሪያ 723 ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ ሆነዋል ።
ነሀሴ 15/2017 (መልአ)፦
በሰባት ክፍለ ከተሞች 132 ፕሎቶችን የያዘው 6ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ በዛሬ ውሎው ለሚ ኩራ 14 ፣ ጉለሌ 9 ፣ አዲስ ከተማ 1፣ ኮልፌ 6 ፣ የካ 1 በድምሩ 31 ፕሎቶች የቀረቡበት ነበር።
የጨረታ ሂደቱን ተጫራቾች፣ህጋዊ ወኪሎቻቸውና በተጫራቾች የተመረጡ ታዛቢዎች በቀጥታ እየተከታተሉት ፍፁም ነፃና ግልጽ በሆነ መልኩ ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ለሦስተ ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ በቆየው በዚህ ጨረታ
በጨረታ ኮሚቴ አባላት በተደረገው ማጣሪያ በጨረታው የተቀመጡ መስፈርቶችን ባለሟሟላታቸው ምክንያት 723 ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ ሆነዋል ።
በቀጣይ ቀናት ተገቢው ማጣሪያ ተደርጎ የመጨረሻዎቹ አሸናፊ ተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝር በቢሮው እስትራቴጅክ ካውንስል ፀድቆ በአዲስ ልሳን ጋዜጣ የሚገለጽ ይሆናል።
ለበለጠ መረጃ የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇👇👇👇👇👇
Website:- https://www.aalb.gov.et
Face book :-Addis Ababa City Land Development Administration and Bureau
Email ፦addisabababacityland@gmail.com
Telegram ፦https://t.me/AddisLand
Youtube፦https://www.youtube.com/@AddisAbabaCityLandDevelopment
Tiktok.https፦//www.tiktok.com/@aa.land.administrator?_t=ZM-8uSveGuoY8T&_r=1
Instagram፥https://www.instagram.com/addisababa
ለሦስተ ተከታታይ ቀናት ሲካሄ በቆየው በዚህ ጨረታ
በጨረታ ኮሚቴ አባላት በተደረገው ማጣሪያ 723 ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ ሆነዋል ።
ነሀሴ 15/2017 (መልአ)፦
በሰባት ክፍለ ከተሞች 132 ፕሎቶችን የያዘው 6ኛው ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ በዛሬ ውሎው ለሚ ኩራ 14 ፣ ጉለሌ 9 ፣ አዲስ ከተማ 1፣ ኮልፌ 6 ፣ የካ 1 በድምሩ 31 ፕሎቶች የቀረቡበት ነበር።
የጨረታ ሂደቱን ተጫራቾች፣ህጋዊ ወኪሎቻቸውና በተጫራቾች የተመረጡ ታዛቢዎች በቀጥታ እየተከታተሉት ፍፁም ነፃና ግልጽ በሆነ መልኩ ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ለሦስተ ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ በቆየው በዚህ ጨረታ
በጨረታ ኮሚቴ አባላት በተደረገው ማጣሪያ በጨረታው የተቀመጡ መስፈርቶችን ባለሟሟላታቸው ምክንያት 723 ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ ሆነዋል ።
በቀጣይ ቀናት ተገቢው ማጣሪያ ተደርጎ የመጨረሻዎቹ አሸናፊ ተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝር በቢሮው እስትራቴጅክ ካውንስል ፀድቆ በአዲስ ልሳን ጋዜጣ የሚገለጽ ይሆናል።
ለበለጠ መረጃ የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇👇👇👇👇👇
Website:- https://www.aalb.gov.et
Face book :-Addis Ababa City Land Development Administration and Bureau
Email ፦addisabababacityland@gmail.com
Telegram ፦https://t.me/AddisLand
Youtube፦https://www.youtube.com/@AddisAbabaCityLandDevelopment
Tiktok.https፦//www.tiktok.com/@aa.land.administrator?_t=ZM-8uSveGuoY8T&_r=1
Instagram፥https://www.instagram.com/addisababa
❤3