ኢትዮጵያ እየመረጠች ነው
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ ትዕግስታችሁና ጽናታችሁ እጅግ በጣም የሚደነቅ ነው።
በዘንድሮው ምርጫ ኢትዮጵያችንን ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላምንም ለማረጋገጥ እና የሀገረ መንግስት ግንባታችንን ለማጠናከር ያላችሁን ቁርጠኝነት ዳግም አሳይታችኋል።
ለረጅም ሰዓት እስካሁን ድረስ ተሰልፋችሁ ያላችሁ፣ ሕፃን ልጃችሁን በጀርባችሁ ያዘላችሁ እመጫቶች፣ ነፍሰ ጡር እናቶች፣ የአካል ጉዳተኞች፣ አዛውንቶች፣ ጎልማሶች እና ወጣቶች፤ ምዝገባው ዲጂታል የነበረ እና በወረቀት ፕሪንት የተደረገ በመሆኑ የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚዎች የስም ፍለጋ ጊዜ መውሰዱ የፍጥነት ላይ ችግር በማጋጠሙ ይቅርታ ጠይቋል ።
በመሆኑም ይህንን በመረዳት እንደጀመራችሁት በጽናት ይበጀኛል ያላችሁትን ለመምረጥ በትግስት ምርጫችሁን እንድታከናውኑ እጠይቃለሁ።
#ኢትዮጵያእየመረጠችነው #ኢትዮጵያ #ዲሞክራሲ #የሕዝብሉዓላዊነት
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች፣ ትዕግስታችሁና ጽናታችሁ እጅግ በጣም የሚደነቅ ነው።
በዘንድሮው ምርጫ ኢትዮጵያችንን ለማጽናት፣ ዘላቂ ሰላምንም ለማረጋገጥ እና የሀገረ መንግስት ግንባታችንን ለማጠናከር ያላችሁን ቁርጠኝነት ዳግም አሳይታችኋል።
ለረጅም ሰዓት እስካሁን ድረስ ተሰልፋችሁ ያላችሁ፣ ሕፃን ልጃችሁን በጀርባችሁ ያዘላችሁ እመጫቶች፣ ነፍሰ ጡር እናቶች፣ የአካል ጉዳተኞች፣ አዛውንቶች፣ ጎልማሶች እና ወጣቶች፤ ምዝገባው ዲጂታል የነበረ እና በወረቀት ፕሪንት የተደረገ በመሆኑ የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚዎች የስም ፍለጋ ጊዜ መውሰዱ የፍጥነት ላይ ችግር በማጋጠሙ ይቅርታ ጠይቋል ።
በመሆኑም ይህንን በመረዳት እንደጀመራችሁት በጽናት ይበጀኛል ያላችሁትን ለመምረጥ በትግስት ምርጫችሁን እንድታከናውኑ እጠይቃለሁ።
#ኢትዮጵያእየመረጠችነው #ኢትዮጵያ #ዲሞክራሲ #የሕዝብሉዓላዊነት
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤1
የኢትዮጵያን መፃዒ እድል ለመወሰን ወሳኝ የሆነዉ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት አንደቀጠለ ነዉ፡፡
የኢትዮጵያን መፃዒ እድል ለመወሰን ወሳኝ የሆነዉ ይህ ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳዉ 12 ሰዓት የተጀመረዉ 7ኛዉ ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምቸዉን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
የኢትዮጵያን መፃዒ እድል ለመወሰን ወሳኝ የሆነዉ ይህ ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳዉ 12 ሰዓት የተጀመረዉ 7ኛዉ ሃገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች መራጮች ድምቸዉን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።
ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።
በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።
ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።
በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ የምርጫ ክልሎችና የምርጫ ጣቢያዎች ከ12፡00 ሰዓት በፊት ሰልፍ ይዘዉ የነበሩ መራጮች ድምጽ እየሰጡ ነዉ
❤1