ለረዳን ፈጣሪ አምላክ ታላቅ ክብርና ምስጋና ይሁንለት!
አዲስ ታሪክ፣ አዲስ ምእራፍ፣ በአዲስ የመከባበር፣ የመመካከርና የመደማመጥ የመግባባት ታሪክ የተደረገ ሽግግር!!
"ከአሸናፊ-ተሸናፊ” ትርክት በመላቀቅ፣ በሀሳብ ልዕልና ወደ በጋራ የማሸነፍ፣ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲባል የጋራ መፍትሄ ለማምጣት በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ ወደ መግባባት የተሸጋገርንበት ታላቅ የታሪክ እጥፋት ነው፡፡ በዚህ የምክክር ሂደት የተለየ አሸናፊና ተሸናፊ ፈጽሞ አልተፈጠረም፤ ይልቁንም ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
እንዲመከሩባቸው ከቀረቡት 400 ከሚጠጉ አበይት ጉዳዮች (ምክረ ሀሳቦች) ኢትዮጵያውያን ተደማምጠውና አንዱ የሌላውን ህመም ተረድተው ወደ አንድ በመሰብሰብ በ99 % ላይ ሙሉ ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ ተችሏል። አንድ አይነት ድምዳሜ ላይ ባልተደረሰባቸው በአራት 4 (1%) ጉዳዮች ላይ ብቻ በአማራጭ መፍትሄዎች እንዲታለፉ በሙሉ መግባባት ላይ ተደርሷል። ይህም ሂደቱን እስካሁን በዓለም ላይ ከሰማናቸው የምክክር ሂደቶች እጅጉን በምሳሌነት የሚጠቀስና አስደናቂ አድርጎታል።
ያለፉት ትውልዶች በጽኑ ተመኝተውት ያላዩትን ይህንን የሰለጠነ አብሮነት የሰፈነበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ በዓይናችን እንድናይ ስለፈቀደልን ቸሩ አምላካችንን ከልብ እናመሰግናለን። የእኛም ትውልድ ይህን ስላሳካን በእውነትም እጅግ የታደልን ትውልዶች ነን።
ለዚህ ሀገራዊ ድል መሳካት ከየአካባቢው የመጡ ውድ ኢትዮጵያውያን ያሳዩት አስደናቂ በሳልነት እና ጥልቅ አስተዋይነት እጅግ የሚመሰገን ነው።
ሀገር የምትገነባውና ኢትዮጵያ የምትጸናው በትክክልም በዚህ የሰለጠነ መንገድ ነው! በመተሳሰብ፣ በአብሮነት፣ አንዱ የሌላውን ሀሳብ ለማዳመጥና ለመቀበል ፈቃደኛ በመሆን፣ እንዲሁም በመከባበር የምንገነባት ኢትዮጵያ የሁላችንም ኩራት ናት። ይህ አስደናቂ የመደማመጥ አዲስ ባህል እና የጋራ ታሪካችን በመሆኑ ላሳኩት ሁሉ ክብር ይገባቸዋል።
በርግጥ ዛሬ ተመካክረን በእነዚህ ጉዳዮች ተግባብተናል ማለት ነገ ምንም አይነት ልዩነቶች አያጋጥሙንም ማለት አይደለም። ነገር ግን ልዩነትን በመመካከርና በሰለጠነ መንገድ መፍታት ተጀምሯል፤ በሩም ተከፍቷል፤ ከእንግዲህ ወደ ኋላ አንመለስም። ከእንግዲህ ልጆቻችን ልዩነቶቻቸውን በጠመንጃ ለመፍታት በመሞከር እና እርስ በእርስ በመገዳደል አይቀጥሉም። ይህ የጦርነት እዳ ወደ እነሱ እንደማይተላለፍ እምነት አለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ ታሪክ፣ አዲስ ምእራፍ፣ በአዲስ የመከባበር፣ የመመካከርና የመደማመጥ የመግባባት ታሪክ የተደረገ ሽግግር!!
"ከአሸናፊ-ተሸናፊ” ትርክት በመላቀቅ፣ በሀሳብ ልዕልና ወደ በጋራ የማሸነፍ፣ ለጋራ ተጠቃሚነት ሲባል የጋራ መፍትሄ ለማምጣት በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ ወደ መግባባት የተሸጋገርንበት ታላቅ የታሪክ እጥፋት ነው፡፡ በዚህ የምክክር ሂደት የተለየ አሸናፊና ተሸናፊ ፈጽሞ አልተፈጠረም፤ ይልቁንም ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
እንዲመከሩባቸው ከቀረቡት 400 ከሚጠጉ አበይት ጉዳዮች (ምክረ ሀሳቦች) ኢትዮጵያውያን ተደማምጠውና አንዱ የሌላውን ህመም ተረድተው ወደ አንድ በመሰብሰብ በ99 % ላይ ሙሉ ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ ተችሏል። አንድ አይነት ድምዳሜ ላይ ባልተደረሰባቸው በአራት 4 (1%) ጉዳዮች ላይ ብቻ በአማራጭ መፍትሄዎች እንዲታለፉ በሙሉ መግባባት ላይ ተደርሷል። ይህም ሂደቱን እስካሁን በዓለም ላይ ከሰማናቸው የምክክር ሂደቶች እጅጉን በምሳሌነት የሚጠቀስና አስደናቂ አድርጎታል።
ያለፉት ትውልዶች በጽኑ ተመኝተውት ያላዩትን ይህንን የሰለጠነ አብሮነት የሰፈነበት ታሪካዊ የምክክር መድረክ በዓይናችን እንድናይ ስለፈቀደልን ቸሩ አምላካችንን ከልብ እናመሰግናለን። የእኛም ትውልድ ይህን ስላሳካን በእውነትም እጅግ የታደልን ትውልዶች ነን።
ለዚህ ሀገራዊ ድል መሳካት ከየአካባቢው የመጡ ውድ ኢትዮጵያውያን ያሳዩት አስደናቂ በሳልነት እና ጥልቅ አስተዋይነት እጅግ የሚመሰገን ነው።
ሀገር የምትገነባውና ኢትዮጵያ የምትጸናው በትክክልም በዚህ የሰለጠነ መንገድ ነው! በመተሳሰብ፣ በአብሮነት፣ አንዱ የሌላውን ሀሳብ ለማዳመጥና ለመቀበል ፈቃደኛ በመሆን፣ እንዲሁም በመከባበር የምንገነባት ኢትዮጵያ የሁላችንም ኩራት ናት። ይህ አስደናቂ የመደማመጥ አዲስ ባህል እና የጋራ ታሪካችን በመሆኑ ላሳኩት ሁሉ ክብር ይገባቸዋል።
በርግጥ ዛሬ ተመካክረን በእነዚህ ጉዳዮች ተግባብተናል ማለት ነገ ምንም አይነት ልዩነቶች አያጋጥሙንም ማለት አይደለም። ነገር ግን ልዩነትን በመመካከርና በሰለጠነ መንገድ መፍታት ተጀምሯል፤ በሩም ተከፍቷል፤ ከእንግዲህ ወደ ኋላ አንመለስም። ከእንግዲህ ልጆቻችን ልዩነቶቻቸውን በጠመንጃ ለመፍታት በመሞከር እና እርስ በእርስ በመገዳደል አይቀጥሉም። ይህ የጦርነት እዳ ወደ እነሱ እንደማይተላለፍ እምነት አለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤2
ዛሬ የኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስን መርቀን ሥራ አስጀምረናል።
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!
ከተማችን አዲስ አበባ የጤና ቱሪዝም ማዕከል እናደርጋታለን ስንል በመንግስት ብቻ የምናሳካው ሳይሆን በግሉ ዘርፍ የሚገነቡትንም ታሳቢ በማድረግ ስለሆነ፣ ዛሬ ያስመረቅነው የኒው ሊፍ ሜዲካል ሆስፒታልም የዚህ አንዱ ማሳያ ነው ።
ኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ በሃገራችን ከላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቀጥሎ ሁለተኛው PET-CT SCAN CAT LAB እና ሌሎች ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች የተሟሉለት ትልቅ የጤና ማዕከል ነው። በጤናው ዘርፍ የምናደርገው ኢንቨስትመንት ክፍያው ከሁሉ የላቀ ስለሆነ እንደዚህ አይነት በጤናው ዘርፍ ለሚሰሩ የጤና ተቋማት እና ሆስፒታሎች ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
የኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ መስራችና ስራአስኪያጅ ዶ/ር ኢማን አብዱልራህማን እና ባለቤታቸው አቡበከር መሃመድ ሳላህን በራሴና በከተማው አስተዳደር ስም በጣም እናመሰግናለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!
ከተማችን አዲስ አበባ የጤና ቱሪዝም ማዕከል እናደርጋታለን ስንል በመንግስት ብቻ የምናሳካው ሳይሆን በግሉ ዘርፍ የሚገነቡትንም ታሳቢ በማድረግ ስለሆነ፣ ዛሬ ያስመረቅነው የኒው ሊፍ ሜዲካል ሆስፒታልም የዚህ አንዱ ማሳያ ነው ።
ኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ በሃገራችን ከላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቀጥሎ ሁለተኛው PET-CT SCAN CAT LAB እና ሌሎች ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎች የተሟሉለት ትልቅ የጤና ማዕከል ነው። በጤናው ዘርፍ የምናደርገው ኢንቨስትመንት ክፍያው ከሁሉ የላቀ ስለሆነ እንደዚህ አይነት በጤናው ዘርፍ ለሚሰሩ የጤና ተቋማት እና ሆስፒታሎች ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
የኒው ሊፍ ሜዲካል ኮምፕሌክስ መስራችና ስራአስኪያጅ ዶ/ር ኢማን አብዱልራህማን እና ባለቤታቸው አቡበከር መሃመድ ሳላህን በራሴና በከተማው አስተዳደር ስም በጣም እናመሰግናለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤1