የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ምሁራን በአዲስ አበባ ጉብኝት አደረጉ
የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ምሁራንን ያካተተ የልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ጎበኙ::
የልዑካን ቡድኑ የአብርሆት ቤተ መጽሀፍ፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአራዳ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማት እና የአንድነት ፓርክን ጎብኝተዋል:: በጉብኝታቸው ባዩት የቱሪዝም ሀብትና በአዲስ አበባ ፈጣን የልማት ጉዞ እጅግ መደነቃቸውን ገልጸዋል::
አዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታም በከተማዋ የሚገኙ ሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የልማት ስራዎችን የሚጎበኙ ሲሆን ጉብኝቱ የከተማዋን የቱሪዝም ሀብት በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ፣ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለማስፋት እና የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ምሁራንን ያካተተ የልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ የተለያዩ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ጎበኙ::
የልዑካን ቡድኑ የአብርሆት ቤተ መጽሀፍ፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአራዳ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማት እና የአንድነት ፓርክን ጎብኝተዋል:: በጉብኝታቸው ባዩት የቱሪዝም ሀብትና በአዲስ አበባ ፈጣን የልማት ጉዞ እጅግ መደነቃቸውን ገልጸዋል::
አዲስ አበባ በሚኖራቸው ቆይታም በከተማዋ የሚገኙ ሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎችንና የልማት ስራዎችን የሚጎበኙ ሲሆን ጉብኝቱ የከተማዋን የቱሪዝም ሀብት በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ፣ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለማስፋት እና የጋራ ትብብርን ለማጠናከር ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
❤2
ምቹ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል የሆነችው አዲስ አበባ
የመሰረተ ልማት መዘመንና የተፈጥሮ ውበት ተዋህደው አዲስ አበባን ምቹ የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል አድርገዋታል፡፡
የአፍሪካ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ፣ በ2018 ዓ.ም በርካታ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችንና ስብሰባዎችን በደመቀ ሁኔታ አስተናግዳለች።
ከተማዋ ከተለያዩ የዓለም ማዕዘናት የመጡ መሪዎችን፣ ዲፕሎማቶችን፣ የቢዝነስ ሰዎችንና ባለሙያዎችን በክብር ተቀብላ፣ በብቃት በማስተናገድ በሰላም ሸኝታለች።
ይህ ስኬት ከተማዋ ያላትን ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ከማሳየቱም በላይ፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ያስመዘገበቻቸውን ፈጣን የእድገትና የመዘመን ጉዞ ለዓለም ያበሰረ አጋጣሚ ሆኗል።
አዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም ለነበሩት ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች አዲስ ፊትና ድምቀት ይዛ እንድትቀርብ ካደረጓት ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል በከተማዋ የተተገበረው መጠነ-ሰፊ የኮሪደር ልማት ግንባታ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
ሰፋፊና ንፁህ የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መስመሮች፣ ዘመናዊ የጎዳና ላይ መብራቶችና ውብ የአረንጓዴ ስፍራዎች የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
ይህ የመሰረተ ልማት መዘመን በኮንፈረንሱ ወቅት የመጡ እንግዶች በከተማዋ ውስጥ ያለምንም እንግልትና በከፍተኛ ደህንነት እንዲንቀሳቀሱ ከመርዳቱም በላይ፣ ለአዲስ አበባ ዘመናዊና ማራኪ ውበትን አላብሷታል።
የትራፊክ ፍሰቱን በማቃለልና የእይታ ውበትን በመጨመር ረገድ የኮሪደር ልማቱ ለኮንፈረንስ ቱሪዝሙ ትልቅ አጋዥ ሆኗል።
ከተማዋ በቅርብ ጊዜያት የገነባቻቸው ድንቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች፣ የወንዝ ዳርቻ ልማቶችና ዘመናዊ ፓርኮች ለስብሰባ የመጡ እንግዶች የትርፍ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉባቸው ተመራጭ ስፍራዎች ሆነዋል።
እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ እና ሌሎች አዳዲስ የወንዝ ዳርቻ መዝናኛዎች እንግዶችን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል።
እነዚህ ስፍራዎች ከተማዋ ከመደበኛ የስብሰባ አዳራሾች ባለፈ፣ እንግዶች የሚዝናኑባቸው፣ ተፈጥሮን የሚያደንቁባቸውና የኢትዮጵያን ባህልና ታሪክ በአንድ ቦታ የሚያዩባቸው የቱሪዝም ማዕከላት ሆነው አገልግለዋል።
ይህም የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከባህላዊና ከተፈጥሮ ቱሪዝም ጋር በማስተሳሰር የከተማዋን የቱሪዝም ገቢና ዝና ከፍ አድርጎታል።
ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና ታዋቂ የሆቴል ብራንዶች በአዲስ አበባ መበራከታቸው ከተማዋ በ2018 ዓ.ም ላስመዘገበችው ስኬት ሌላኛው ምሰሶ ነው።
ሆቴሎቹ እንግዶችን በከፍተኛ የደህንነት፣ የፅዳትና የቅልጥፍና ደረጃ ከማስተናገዳቸውም በላይ፣ የኢትዮጵያውያንን ባህላዊ የእንግዳ ተቀባይነት ጨዋነት ከዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር አዋህደው አቅርበዋል።
የስብሰባ አዳራሾች ዝግጁነት፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችና የሰለጠነ የሰው ኃይል መኖር ሆቴሎቹ ለኮንፈረንሶቹ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ አስችሏቸዋል።
ከተማዋ በአንድ ጊዜ በሺህ የሚቆጠሩ እንግዶችን በምቾት የማሳደርና የማስተናገድ ሙሉ ብቃት እንዳላት በተግባር የታየበት ሆኗል።
በአጠቃላይ አዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም ያስተናገደቻቸው በርካታ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ከተማዋ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያላትን የማይተካ ሚና ዳግም ያረጋገጡ ነበሩ። ከተማዋ እንግዶቿን ተቀብላ፣ በከፍተኛ ፍቅር አስተናግዳ፣ በሰላም በመሸኘት ያሳየችው ብቃት የሚደነቅ ነው።
ይህ ስኬት ከተማዋ የገነባቻቸው ዘመናዊ የኮሪደር መሰረተ ልማቶች፣ ማራኪ የወንዝ ዳርቻዎችና የቱሪዝም ፓርኮች እንዲሁም የላቀ የሆቴሎች ዝግጁነት ጥምር ውጤት ነው።
አዲስ አበባ አሁን ላይ ስብሰባዎች የሚካሄዱባት ከተማ ብቻ ሳትሆን፣ የመሰረተ ልማት መዘመንና የተፈጥሮ ውበት የተዋሃዱባት፣ አስተማማኝና ምቹ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል መሆኗን ለዓለም አስመስክራለች።
ይህ ተሞክሮ ወደፊትም ከተማዋ ይበልጥ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እንድትስብና እንድታስተናግድ በር የሚከፍት ነው።
የመሰረተ ልማት መዘመንና የተፈጥሮ ውበት ተዋህደው አዲስ አበባን ምቹ የዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል አድርገዋታል፡፡
የአፍሪካ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መዲና የሆነችው አዲስ አበባ፣ በ2018 ዓ.ም በርካታ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችንና ስብሰባዎችን በደመቀ ሁኔታ አስተናግዳለች።
ከተማዋ ከተለያዩ የዓለም ማዕዘናት የመጡ መሪዎችን፣ ዲፕሎማቶችን፣ የቢዝነስ ሰዎችንና ባለሙያዎችን በክብር ተቀብላ፣ በብቃት በማስተናገድ በሰላም ሸኝታለች።
ይህ ስኬት ከተማዋ ያላትን ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ከማሳየቱም በላይ፣ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ያስመዘገበቻቸውን ፈጣን የእድገትና የመዘመን ጉዞ ለዓለም ያበሰረ አጋጣሚ ሆኗል።
አዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም ለነበሩት ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች አዲስ ፊትና ድምቀት ይዛ እንድትቀርብ ካደረጓት ዋና ዋና ምክንያቶች መካከል በከተማዋ የተተገበረው መጠነ-ሰፊ የኮሪደር ልማት ግንባታ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል።
ሰፋፊና ንፁህ የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መስመሮች፣ ዘመናዊ የጎዳና ላይ መብራቶችና ውብ የአረንጓዴ ስፍራዎች የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
ይህ የመሰረተ ልማት መዘመን በኮንፈረንሱ ወቅት የመጡ እንግዶች በከተማዋ ውስጥ ያለምንም እንግልትና በከፍተኛ ደህንነት እንዲንቀሳቀሱ ከመርዳቱም በላይ፣ ለአዲስ አበባ ዘመናዊና ማራኪ ውበትን አላብሷታል።
የትራፊክ ፍሰቱን በማቃለልና የእይታ ውበትን በመጨመር ረገድ የኮሪደር ልማቱ ለኮንፈረንስ ቱሪዝሙ ትልቅ አጋዥ ሆኗል።
ከተማዋ በቅርብ ጊዜያት የገነባቻቸው ድንቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች፣ የወንዝ ዳርቻ ልማቶችና ዘመናዊ ፓርኮች ለስብሰባ የመጡ እንግዶች የትርፍ ጊዜያቸውን የሚያሳልፉባቸው ተመራጭ ስፍራዎች ሆነዋል።
እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ እና ሌሎች አዳዲስ የወንዝ ዳርቻ መዝናኛዎች እንግዶችን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል።
እነዚህ ስፍራዎች ከተማዋ ከመደበኛ የስብሰባ አዳራሾች ባለፈ፣ እንግዶች የሚዝናኑባቸው፣ ተፈጥሮን የሚያደንቁባቸውና የኢትዮጵያን ባህልና ታሪክ በአንድ ቦታ የሚያዩባቸው የቱሪዝም ማዕከላት ሆነው አገልግለዋል።
ይህም የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከባህላዊና ከተፈጥሮ ቱሪዝም ጋር በማስተሳሰር የከተማዋን የቱሪዝም ገቢና ዝና ከፍ አድርጎታል።
ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና ታዋቂ የሆቴል ብራንዶች በአዲስ አበባ መበራከታቸው ከተማዋ በ2018 ዓ.ም ላስመዘገበችው ስኬት ሌላኛው ምሰሶ ነው።
ሆቴሎቹ እንግዶችን በከፍተኛ የደህንነት፣ የፅዳትና የቅልጥፍና ደረጃ ከማስተናገዳቸውም በላይ፣ የኢትዮጵያውያንን ባህላዊ የእንግዳ ተቀባይነት ጨዋነት ከዘመናዊ አገልግሎት አሰጣጥ ጋር አዋህደው አቅርበዋል።
የስብሰባ አዳራሾች ዝግጁነት፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶችና የሰለጠነ የሰው ኃይል መኖር ሆቴሎቹ ለኮንፈረንሶቹ ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ አስችሏቸዋል።
ከተማዋ በአንድ ጊዜ በሺህ የሚቆጠሩ እንግዶችን በምቾት የማሳደርና የማስተናገድ ሙሉ ብቃት እንዳላት በተግባር የታየበት ሆኗል።
በአጠቃላይ አዲስ አበባ በ2018 ዓ.ም ያስተናገደቻቸው በርካታ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች ከተማዋ በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያላትን የማይተካ ሚና ዳግም ያረጋገጡ ነበሩ። ከተማዋ እንግዶቿን ተቀብላ፣ በከፍተኛ ፍቅር አስተናግዳ፣ በሰላም በመሸኘት ያሳየችው ብቃት የሚደነቅ ነው።
ይህ ስኬት ከተማዋ የገነባቻቸው ዘመናዊ የኮሪደር መሰረተ ልማቶች፣ ማራኪ የወንዝ ዳርቻዎችና የቱሪዝም ፓርኮች እንዲሁም የላቀ የሆቴሎች ዝግጁነት ጥምር ውጤት ነው።
አዲስ አበባ አሁን ላይ ስብሰባዎች የሚካሄዱባት ከተማ ብቻ ሳትሆን፣ የመሰረተ ልማት መዘመንና የተፈጥሮ ውበት የተዋሃዱባት፣ አስተማማኝና ምቹ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከል መሆኗን ለዓለም አስመስክራለች።
ይህ ተሞክሮ ወደፊትም ከተማዋ ይበልጥ ታላላቅ ዓለም አቀፍ ሁነቶችን እንድትስብና እንድታስተናግድ በር የሚከፍት ነው።
ተመራቂ የፖሊስ መኮንኖች እንኳን ደስ አላችሁ!
ዛሬ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ በሁለተኛ ዙር የሰለጠኑ 864 የፖሊስ መኮንኖችን መርቀናል።
ተመራቂዎቹ በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር በጠንካራ ዲሲፕሊን ስልጠናቸውን በብቃት ያጠናቀቁ ፤ በአካልና በመንፈስ ጠንክረው የወጡ በመሆናቸው በፖሊስ መኮንንነት ማዕረግ ተመርቀዋል።
ተመራቂዎች በቆይታችሁ ያገኛችሁት እውቀት ለላቀ ፖሊሳዊ ስብዕና የሚያበቃችሁ እንደመሆኑ ወደ ስራ ስትሰማሩም ያለአድልዎና ልዩነት በታማኝነት፣ በጀግንነት፣ በሰብዓዊነትና በክብር፣ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንደምታገለግሉ ሙሉ እምነት አለኝ።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ በሁለተኛ ዙር የሰለጠኑ 864 የፖሊስ መኮንኖችን መርቀናል።
ተመራቂዎቹ በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር በጠንካራ ዲሲፕሊን ስልጠናቸውን በብቃት ያጠናቀቁ ፤ በአካልና በመንፈስ ጠንክረው የወጡ በመሆናቸው በፖሊስ መኮንንነት ማዕረግ ተመርቀዋል።
ተመራቂዎች በቆይታችሁ ያገኛችሁት እውቀት ለላቀ ፖሊሳዊ ስብዕና የሚያበቃችሁ እንደመሆኑ ወደ ስራ ስትሰማሩም ያለአድልዎና ልዩነት በታማኝነት፣ በጀግንነት፣ በሰብዓዊነትና በክብር፣ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ እንደምታገለግሉ ሙሉ እምነት አለኝ።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤3