በጤናው ዘርፍ በ5 ዓመታት ውስጥ ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው በእጥፍ የሚበልጥ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል ።
አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል የማድረግ ጉዞ ተጨባጭ ለውጦችን አስመዝግቧል።
ከተማችን በሁለንተናዊ መልኩ እንድትለወጥ ከተሰሩ ስራዎች አንዱ በጤናው ዘርፍ የታየው የጤና መሰረተ ልማት የማስፋፋት ስራ ዋነኛው ነው፡፡
ባለፉት 5 ዓመታት ውስጥ የጤና መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ከተሰሩ ስራዎች ውስጥ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ውስጥ የተገነቡት ዘመናዊ የአይን ሕክምና፣ የኩላሊት እጥበት እንዲሁም የፎረንሲክ እና ስነምረዛ ምርምር አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ይጠቀሳሉ፡፡
በዘውዲቱ ሆስፒታል እጅግ ዘመናዊ ተደርጎ የተገነባው የህክምና ልህቀት ማዕከል እና በራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ውስጥ ለታካሚዎች ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ “አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል” ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ በማዕከላቱ በነባሮቹ ሆስፒታሎች በኋላቀር የህክምና መሳሪዎች እና ለታካሚዎች በማይመችና በተጨናነቀ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን በመቀየር የዘመኑ ቴክኖሎጂ ተሟልተውላቸው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በተጨማሪም የአበበች ጎበና እናቶችና ህጻናት ሆስፒታል፣ ላፍቶ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ ኮልፌ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የገላን ድንገተኛ ህክምና ሆስፒታል በጥቂት ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ የተገነቡ የህክምና ማዕከላቶች ናቸው።
ለ4ዐ ጤና ጣቢያዎች መሰረታዊ ማስፋፊያ እና 9 አዳዲስ የጤና ጣቢያዎች ተገንብተው ወደ አገልግሎት ገብተዋል፡፡
አዲሰ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ማድረግ እና በጤናው ዘርፍ ያለው ፍላጎት በመንግስት ብቻ የማይሟላ በመሆኑ የግሉን ዘርፍ በመደገፍም እጅግ ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ሆስፒታሎች እንዲገነቡ ተደጓል።
በአጠቃላይ በጤናው ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች ከ 5 ዓመት በፊት የነበሩትን አልጋዎች ቁጥር ከ 2 እጥፍ በላይ ማሳደግ ተችሏ፡፡ በዚህም በ 5 ዓመታት ውስጥ የታየው እድገት ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው እድገት በእጥፍ እንዲበልጥ አድርጎታል፡፡
ጤናችንን የምንጠብቀው በሕክምና ብቻ ሳይሆን በመከላከል ጭምር በመሆኑ አዲስ አበባን ከብክለት በመከላከል፣ ፅዱ አረንጓዴ እና ለኑሮ ተስማሚ ከተማ በማድረግ ጤናማ አካባቢን የመፍጠር የጤና ፖሊሲያችን በከተማችን በተሟላ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል፡፡
አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል የማድረግ ጉዞ ተጨባጭ ለውጦችን አስመዝግቧል።
ከተማችን በሁለንተናዊ መልኩ እንድትለወጥ ከተሰሩ ስራዎች አንዱ በጤናው ዘርፍ የታየው የጤና መሰረተ ልማት የማስፋፋት ስራ ዋነኛው ነው፡፡
ባለፉት 5 ዓመታት ውስጥ የጤና መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ከተሰሩ ስራዎች ውስጥ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ውስጥ የተገነቡት ዘመናዊ የአይን ሕክምና፣ የኩላሊት እጥበት እንዲሁም የፎረንሲክ እና ስነምረዛ ምርምር አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ይጠቀሳሉ፡፡
በዘውዲቱ ሆስፒታል እጅግ ዘመናዊ ተደርጎ የተገነባው የህክምና ልህቀት ማዕከል እና በራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ውስጥ ለታካሚዎች ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ “አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል” ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ በማዕከላቱ በነባሮቹ ሆስፒታሎች በኋላቀር የህክምና መሳሪዎች እና ለታካሚዎች በማይመችና በተጨናነቀ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን በመቀየር የዘመኑ ቴክኖሎጂ ተሟልተውላቸው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በተጨማሪም የአበበች ጎበና እናቶችና ህጻናት ሆስፒታል፣ ላፍቶ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ ኮልፌ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የገላን ድንገተኛ ህክምና ሆስፒታል በጥቂት ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ የተገነቡ የህክምና ማዕከላቶች ናቸው።
ለ4ዐ ጤና ጣቢያዎች መሰረታዊ ማስፋፊያ እና 9 አዳዲስ የጤና ጣቢያዎች ተገንብተው ወደ አገልግሎት ገብተዋል፡፡
አዲሰ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ማድረግ እና በጤናው ዘርፍ ያለው ፍላጎት በመንግስት ብቻ የማይሟላ በመሆኑ የግሉን ዘርፍ በመደገፍም እጅግ ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ሆስፒታሎች እንዲገነቡ ተደጓል።
በአጠቃላይ በጤናው ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች ከ 5 ዓመት በፊት የነበሩትን አልጋዎች ቁጥር ከ 2 እጥፍ በላይ ማሳደግ ተችሏ፡፡ በዚህም በ 5 ዓመታት ውስጥ የታየው እድገት ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው እድገት በእጥፍ እንዲበልጥ አድርጎታል፡፡
ጤናችንን የምንጠብቀው በሕክምና ብቻ ሳይሆን በመከላከል ጭምር በመሆኑ አዲስ አበባን ከብክለት በመከላከል፣ ፅዱ አረንጓዴ እና ለኑሮ ተስማሚ ከተማ በማድረግ ጤናማ አካባቢን የመፍጠር የጤና ፖሊሲያችን በከተማችን በተሟላ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል፡፡
❤1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስለ ወዳጅነት ፓርክ ካስተላለፉ መልዐክት፦
“በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት በመደመር መንግሥት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ያስገኘ ሲሆን፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሥራ ዕድሎችንና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ፈጥሯል።”
Prime Minister Abiy Ahmed’s message about Friendship Park:
“Friendship Park, located in the heart of Addis Ababa, is one of the first multifunctional public spaces built by the Medemer Government over the past eight years. In the past four years alone, the park has generated close to one billion birr in revenue, while creating employment opportunities and economic benefits both directly and indirectly.”
#PMOEthiopia
#EthiopiaDelivers
“በአዲስ አበባ መሐል የሚገኘው የወዳጅነት ፓርክ ባለፉት ስምንት ዓመታት በመደመር መንግሥት ከተገነቡት የመጀመሪያዎቹ ዘርፈ-ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው የሕዝብ መገልገያ ቦታዎች አንዱ ነው። ይህ ፓርክ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ ወደ አንድ ቢሊዮን ብር ገደማ ገቢ ያስገኘ ሲሆን፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሥራ ዕድሎችንና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ፈጥሯል።”
Prime Minister Abiy Ahmed’s message about Friendship Park:
“Friendship Park, located in the heart of Addis Ababa, is one of the first multifunctional public spaces built by the Medemer Government over the past eight years. In the past four years alone, the park has generated close to one billion birr in revenue, while creating employment opportunities and economic benefits both directly and indirectly.”
#PMOEthiopia
#EthiopiaDelivers
ኢትዮጵያን ከወጣቶቿ ነጥሎ ማየት አይቻልም!
የህዝባችን የእድሜ ስብጥር እንደሚያመላክተው ወጣቶች ከፍተኛውን "ቁጥር መያዛቸው፣ ብልጽግናን ለማረጋገጥና ለማፅናትም ታላቅ እድል ነው።
የኢትዮጵያ ወጣት መልካም ዓላማን አንግቦ የሚንቀሳቀስ፣ የለውጥ ዋነኛ ሞተርና የሉዓላዊነታችን ጽኑ ማገር ነው! የኢትዮጵያ ወጣት የሀገሩን ታሪክ በአዲስ ብዕርና ብራና እየጻፈ ይገኛል። ሀገራችንን የኋሊት ጠፍንገው የያዟትን አጓጉል ልማዶች፣ አላስፈላጊ ንትርኮች፣ ጭቅጭቅ እና ግጭቶች በመራቅ የአሁን ወጣት በልማት ላይ አተኩሯል፣ ድህነትን ተጠይፏል።
የመደመር መንግሥት የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና የአመራርነት ሚና ለማጠናከር በትኩረትና በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል።
ሀገራዊ ርዕያችንን ዕውን ለማድረግ ሁላችሁም በንቃት እየተጋን፣ በፍቅር እንድንመላለስ ጥሪዬን አቀርባለሁ።"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
የህዝባችን የእድሜ ስብጥር እንደሚያመላክተው ወጣቶች ከፍተኛውን "ቁጥር መያዛቸው፣ ብልጽግናን ለማረጋገጥና ለማፅናትም ታላቅ እድል ነው።
የኢትዮጵያ ወጣት መልካም ዓላማን አንግቦ የሚንቀሳቀስ፣ የለውጥ ዋነኛ ሞተርና የሉዓላዊነታችን ጽኑ ማገር ነው! የኢትዮጵያ ወጣት የሀገሩን ታሪክ በአዲስ ብዕርና ብራና እየጻፈ ይገኛል። ሀገራችንን የኋሊት ጠፍንገው የያዟትን አጓጉል ልማዶች፣ አላስፈላጊ ንትርኮች፣ ጭቅጭቅ እና ግጭቶች በመራቅ የአሁን ወጣት በልማት ላይ አተኩሯል፣ ድህነትን ተጠይፏል።
የመደመር መንግሥት የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትና የአመራርነት ሚና ለማጠናከር በትኩረትና በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል።
ሀገራዊ ርዕያችንን ዕውን ለማድረግ ሁላችሁም በንቃት እየተጋን፣ በፍቅር እንድንመላለስ ጥሪዬን አቀርባለሁ።"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
❤2
ለውበት፥ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት
አስተዋፅኦ እያደረገ ያለው የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት!
አዲስ አበባ በደረቅ እና ፈሳሽ ቆሻሻ አስተዳደር የከተማዋን ገጽታ የለወጡ መጠነ ሰፊ ሥራዎችን አከናውናለች። ከተማ አስተዳደሩ የተገበረው የተቀናጀ የቆሻሻ አስተዳደር ሥርዓት ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ጽዱና ተስማሚ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ የማህበረሰቡ ጤና እንዲጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ባለፉት አምስት አመታት የዘመነ የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት ተግባራዊ በመደረጉ እጅግ ከፍተኛ ቶን የደረቅ ቆሻሻ እና ፈሳሽ ቆሻሻ በመልሶ መጠቀም ኡደት ውስጥ ውሏል፡፡
የቆሻሻ አስተዳደር ሥርዓቱ ከንጽህና ባሻገር ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት የማይናቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በዘርፉ በተደራጁ ወጣቶች፣ ሴቶችና ማህበራት አማካይነት ሰፊ የሥራ እድል ከመፍጠሩም በላይ ቆሻሻን ወደ ሀብት የመቀየር (Recycling) አሰራር ተተግብሯል። ከዚህ በፊት ለከተማ ብክለትና ለጤና ስጋት የነበረው ቆሻሻ ዛሬ ሃብት እንዲሆን ተደርጓል፡፡ በየዓመቱ በከተማችን ከደረቅ ቆሻሻ በብዙ ቶን ኮምፖስት ለከተማ ግብርና ይመረታል፡፡ እንዲሁም ከደረቅና ፈሻስ ቆሻሻ ለኃይል ማመንጫ መቅረቡ የቆሻሻ አስተዳደር ከመሰብሰብና ከመጣል ወደ ኡደት፣ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እና ኃይል ምንጭነት እየተሸጋገረ ከተማችንን ውብ እና ፅዱ ማድረግ ተችሏል።
ይህ የተቀናጀ የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት አዲስ አበባን ውብ፡ ጽዱ እንድትሆንና ዓለም አቀፍ እውቅናን እንድታገኝ አድርጓታል፡፡ ስኬቱ ከተማዋ ለአገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ሳቢ፣ ምቹና ጽዱ እንድትሆን ያስቻለ ሲሆን ይህም አዲስ አበባን በአፍሪካ ደረጃ ከ10 ጽዱ ከተሞች አንዷ አድርጓታል።
በመሆኑም የጽዳቱ ውጤት አዲስ አበባ የአህጉራችን የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን የሚያረጋግጥ የጽዳትና የመሰረተ ልማት ደረጃ ላይ መድረሷን ያረጋግጣል።
አስተዋፅኦ እያደረገ ያለው የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት!
አዲስ አበባ በደረቅ እና ፈሳሽ ቆሻሻ አስተዳደር የከተማዋን ገጽታ የለወጡ መጠነ ሰፊ ሥራዎችን አከናውናለች። ከተማ አስተዳደሩ የተገበረው የተቀናጀ የቆሻሻ አስተዳደር ሥርዓት ከተማዋን ለነዋሪዎቿ ጽዱና ተስማሚ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ የማህበረሰቡ ጤና እንዲጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ባለፉት አምስት አመታት የዘመነ የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት ተግባራዊ በመደረጉ እጅግ ከፍተኛ ቶን የደረቅ ቆሻሻ እና ፈሳሽ ቆሻሻ በመልሶ መጠቀም ኡደት ውስጥ ውሏል፡፡
የቆሻሻ አስተዳደር ሥርዓቱ ከንጽህና ባሻገር ለከተማዋ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት የማይናቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። በዘርፉ በተደራጁ ወጣቶች፣ ሴቶችና ማህበራት አማካይነት ሰፊ የሥራ እድል ከመፍጠሩም በላይ ቆሻሻን ወደ ሀብት የመቀየር (Recycling) አሰራር ተተግብሯል። ከዚህ በፊት ለከተማ ብክለትና ለጤና ስጋት የነበረው ቆሻሻ ዛሬ ሃብት እንዲሆን ተደርጓል፡፡ በየዓመቱ በከተማችን ከደረቅ ቆሻሻ በብዙ ቶን ኮምፖስት ለከተማ ግብርና ይመረታል፡፡ እንዲሁም ከደረቅና ፈሻስ ቆሻሻ ለኃይል ማመንጫ መቅረቡ የቆሻሻ አስተዳደር ከመሰብሰብና ከመጣል ወደ ኡደት፣ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እና ኃይል ምንጭነት እየተሸጋገረ ከተማችንን ውብ እና ፅዱ ማድረግ ተችሏል።
ይህ የተቀናጀ የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት አዲስ አበባን ውብ፡ ጽዱ እንድትሆንና ዓለም አቀፍ እውቅናን እንድታገኝ አድርጓታል፡፡ ስኬቱ ከተማዋ ለአገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ሳቢ፣ ምቹና ጽዱ እንድትሆን ያስቻለ ሲሆን ይህም አዲስ አበባን በአፍሪካ ደረጃ ከ10 ጽዱ ከተሞች አንዷ አድርጓታል።
በመሆኑም የጽዳቱ ውጤት አዲስ አበባ የአህጉራችን የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን የሚያረጋግጥ የጽዳትና የመሰረተ ልማት ደረጃ ላይ መድረሷን ያረጋግጣል።