በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ኅብረተሰቡ እየተቀላቀሉ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤን) ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች የያዙት የትጥቅ ትግል በጫካ ውስጥ ተደብቆ ንፁሃንን ከመግደል እና ከመዝረፍ የዘለለ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ግብ የሌለው መሆኑን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ጦርነት እና ግጭት አውዳሚ መሆናቸውን በመገንዘብ በየዕለቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ኅብረተሰቡ እየተቀላቀሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
መንግሥት ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ያለው ቁርጠኝነት አሁንም ያልተለወጠ መሆኑን ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ማንኛውም አካል በሰላማዊ መንገድ ሀሳቡን ይዞ ለመታገል እስከፈለገ ድረስ የመንግሥት የሰላም በር መቼም ቢሆን እንደማይዘጋ አስገንዝበዋል።
የኦሮሞን ሕዝብ ትግል በዋናነት የጀመሩ እና ያደራጁ አንጋፋ ፖለቲከኞች በአሁኑ ወቅት ሀገር ቤት ገብተው በፓርላማ እና በተለያዩ የንግድ ሥራዎች ላይ በሰላም እየተሳተፉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በአንፃሩም፣ አሁን የትጥቅ ትግሉን ከሚመሩት አካላት ጀርባ ያለውን ተቃርኖ አንስተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን ላይ በጫካ ውስጥ የሚገኙት ኃይሎች የማንን አጀንዳ እያስፈፀሙ እንደሆነ ሕዝቡና ወጣቱ ቆም ብሎ ሊጠይቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በጠመንጃ ኃይል ሊገነባ እንደማይችል ያመላከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ብልፅግና ፓርቲ በብቁ ሀሳብ እና በአሸናፊ ፖለቲካ ላይ የተመሠረተ እንጂ በዘር ላይ የተንጠለጠለ አደረጃጀት አለመሆኑን አብራርተዋል።
የትኛውም የፖለቲካ ቡድን ፍላጎቱን ማሳካት የሚችለው ሕዝብን አሳምኖ በምርጫ ሲያሸንፍ ብቻ መሆኑን በአፅንዖት ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (ኦቢኤን) ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ኃይሎች የያዙት የትጥቅ ትግል በጫካ ውስጥ ተደብቆ ንፁሃንን ከመግደል እና ከመዝረፍ የዘለለ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ግብ የሌለው መሆኑን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ጦርነት እና ግጭት አውዳሚ መሆናቸውን በመገንዘብ በየዕለቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ኅብረተሰቡ እየተቀላቀሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
መንግሥት ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ለመፍታት ያለው ቁርጠኝነት አሁንም ያልተለወጠ መሆኑን ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ማንኛውም አካል በሰላማዊ መንገድ ሀሳቡን ይዞ ለመታገል እስከፈለገ ድረስ የመንግሥት የሰላም በር መቼም ቢሆን እንደማይዘጋ አስገንዝበዋል።
የኦሮሞን ሕዝብ ትግል በዋናነት የጀመሩ እና ያደራጁ አንጋፋ ፖለቲከኞች በአሁኑ ወቅት ሀገር ቤት ገብተው በፓርላማ እና በተለያዩ የንግድ ሥራዎች ላይ በሰላም እየተሳተፉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በአንፃሩም፣ አሁን የትጥቅ ትግሉን ከሚመሩት አካላት ጀርባ ያለውን ተቃርኖ አንስተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን ላይ በጫካ ውስጥ የሚገኙት ኃይሎች የማንን አጀንዳ እያስፈፀሙ እንደሆነ ሕዝቡና ወጣቱ ቆም ብሎ ሊጠይቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በጠመንጃ ኃይል ሊገነባ እንደማይችል ያመላከቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ብልፅግና ፓርቲ በብቁ ሀሳብ እና በአሸናፊ ፖለቲካ ላይ የተመሠረተ እንጂ በዘር ላይ የተንጠለጠለ አደረጃጀት አለመሆኑን አብራርተዋል።
የትኛውም የፖለቲካ ቡድን ፍላጎቱን ማሳካት የሚችለው ሕዝብን አሳምኖ በምርጫ ሲያሸንፍ ብቻ መሆኑን በአፅንዖት ተናግረዋል።
የኦሮሞ ሕዝብ ትግል የእኩልነት እንጂ የበላይነት አይደለም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በወቅታዊ የሀገራችን የፖለቲካ ትርክቶች ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም፣ የኦሮሞ ሕዝብ የፖለቲካ ተሳትፎን በተመለከተ የሚንፀባረቁ ሁለት ጽንፈኛ እና ተቃራኒ ሀሳቦች፣ ፖለቲካዊ ብስለት የጎደላቸው ናቸው ብለዋል።
የመጀመሪያው ቡድን "ኦሮሞ ተረኛ ሆኗል" የሚል ትርክት የሚያራምድ መሆኑን አንስተው፣ ይህ ቡድን ከዚህ ቀደም ሀብት እና ንብረት ሲዘርፍ የነበረና አሁን ያ አድሏዊ የጥቅም መረቡ በመበጠሱ ምክንያት የሚያለቅስ መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል፣ "ኦሮሞ የሚገባውን አላገኘም" የሚል ትርክት የሚያራምደው ሁለተኛው ቡድን፣ "እኔ ካልመራሁ" በሚል አግላይ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተጠመደ እና የሌሎችን ኦሮሞነት ጭምር በጥርጣሬ የሚመለከት መሆኑን አብራርተዋል።
አያይዘውም፣ የሚገርመው ጉዳይ ግን እነዚህ እርስ በርስ የሚቃረን ሀሳብ ያላቸው ሁለት የተለያዩ ቡድኖች፣ መንግሥትን በማፍረስ እና ሀገርን በማተራመስ ዓላማ ላይ በአንድነት እየሠሩ መሆናቸው ነው ብለዋል።
ይህም፣ ተነሳሽነታቸው ከግል ጥቅም እንጂ ከሕዝብ እውነተኛ ጥያቄ የመነጨ አለመሆኑን በግልጽ ያሳያል ነው ያሉት።
የኦሮሞ ሕዝብ መቼም ቢሆን የሰውን ሀብት ቀምቶ እንደማያውቅ እና ይልቁንም ለጋስ መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የትግሉ ዋና ዓላማም ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በእኩልነት እና በጋራ በሕግ የበላይነት ስር መኖር እንጂ የሌላውን ነጥቆ የበላይነትን ለማረጋገጥ አለመሆኑን አስምረውበታል።
በማጠቃለያቸውም፣ ማንም አካል የኦሮሞን ሀብት በጉልበት ሊቀማ እንደማይችል በማስጠንቀቅ፣ አሁን ላይ ያለው መንግሥት የጋራ ሀብትን በሕግ አግባብ፣ የራስን ደግሞ በፍቅር እና በፈቃደኝነት ላይ በተመሰረተ መንገድ የማካፈል ፖለቲካን እንደሚከተል አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በወቅታዊ የሀገራችን የፖለቲካ ትርክቶች ዙሪያ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም፣ የኦሮሞ ሕዝብ የፖለቲካ ተሳትፎን በተመለከተ የሚንፀባረቁ ሁለት ጽንፈኛ እና ተቃራኒ ሀሳቦች፣ ፖለቲካዊ ብስለት የጎደላቸው ናቸው ብለዋል።
የመጀመሪያው ቡድን "ኦሮሞ ተረኛ ሆኗል" የሚል ትርክት የሚያራምድ መሆኑን አንስተው፣ ይህ ቡድን ከዚህ ቀደም ሀብት እና ንብረት ሲዘርፍ የነበረና አሁን ያ አድሏዊ የጥቅም መረቡ በመበጠሱ ምክንያት የሚያለቅስ መሆኑን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል፣ "ኦሮሞ የሚገባውን አላገኘም" የሚል ትርክት የሚያራምደው ሁለተኛው ቡድን፣ "እኔ ካልመራሁ" በሚል አግላይ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተጠመደ እና የሌሎችን ኦሮሞነት ጭምር በጥርጣሬ የሚመለከት መሆኑን አብራርተዋል።
አያይዘውም፣ የሚገርመው ጉዳይ ግን እነዚህ እርስ በርስ የሚቃረን ሀሳብ ያላቸው ሁለት የተለያዩ ቡድኖች፣ መንግሥትን በማፍረስ እና ሀገርን በማተራመስ ዓላማ ላይ በአንድነት እየሠሩ መሆናቸው ነው ብለዋል።
ይህም፣ ተነሳሽነታቸው ከግል ጥቅም እንጂ ከሕዝብ እውነተኛ ጥያቄ የመነጨ አለመሆኑን በግልጽ ያሳያል ነው ያሉት።
የኦሮሞ ሕዝብ መቼም ቢሆን የሰውን ሀብት ቀምቶ እንደማያውቅ እና ይልቁንም ለጋስ መሆኑን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የትግሉ ዋና ዓላማም ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በእኩልነት እና በጋራ በሕግ የበላይነት ስር መኖር እንጂ የሌላውን ነጥቆ የበላይነትን ለማረጋገጥ አለመሆኑን አስምረውበታል።
በማጠቃለያቸውም፣ ማንም አካል የኦሮሞን ሀብት በጉልበት ሊቀማ እንደማይችል በማስጠንቀቅ፣ አሁን ላይ ያለው መንግሥት የጋራ ሀብትን በሕግ አግባብ፣ የራስን ደግሞ በፍቅር እና በፈቃደኝነት ላይ በተመሰረተ መንገድ የማካፈል ፖለቲካን እንደሚከተል አብራርተዋል።
በዚህ ዘመን የትጥቅ ትግል ማድረግ ፋሽን ያለፈበት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በትጥቅ ትግል በኃይል ሥልጣን ለመያዝ ወይም ፍላጎትን ለመጫን የሚደረግ ሙከራ እንደማይሳካ ገልጸው፤ በዚህ ዘመን የትጥቅ ትግል ማድረግ ፋሽን ያለፈበት ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች የታጠቁ ቡድኖች በርካታ ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ መንገድ መመለሳቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በጫካ የቀሩትም ቢሆኑ በሂደት ነገሩ እየገባቸው ይመጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
መንግሥት በርካታ የፖለቲካ እስረኞችን ፈትቶ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ያሰፋ ቢሆንም፣ የተወሰኑ አካላት ግን ትናንት ካሰሯቸው እና ከገረፏቸው አካላት ጋር ድብቅ ጥምረት ፈጥረው ወደ ጫካ መግባታቸው አሳዝኖናል ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል ሰፊ የዴሞክራሲና የፖለቲካ ተሳትፎ ዕድል በመኖሩ በሰላማዊ መንገድ መታገል ይቻላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በጫካ የሚገኘው የሸኔ ቡድን ግልጽ ዓላማ እና ግብ የሌለው "ተቀጣሪ ኃይል" ነው ሲሉ ገልጸውታል።
ቡድኑ ሽፍታ ሆኖ ሰዎችን ከመግደልና ከመዝረፍ ውጭ የፖለቲካ ፍላጎቱን ማሳካት እንደማይችልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የኦነግ መስራች ታጋዮች በአሁኑ ወቅት በሰላማዊ መንገድ በሀገር ውስጥ እና በፓርላማ ተቀምጠው እየታገሉ ባሉበት ሁኔታ፣ በጫካ ያለው ቡድን የማንን አጀንዳ ይዞ እንደሚታገል ሕዝቡ ሊጠይቅ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ማንኛውም አካል ፍላጎቱንና ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ እና በምክክር ማሳካት እንደሚችል ያመላከቱት ጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ አሁንም ቢሆን የመንግሥት የሰላም በር ክፍት እንደሆነ አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ በትጥቅ ትግል በኃይል ሥልጣን ለመያዝ ወይም ፍላጎትን ለመጫን የሚደረግ ሙከራ እንደማይሳካ ገልጸው፤ በዚህ ዘመን የትጥቅ ትግል ማድረግ ፋሽን ያለፈበት ነው ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ከኦነግ ሸኔ እና ከሌሎች የታጠቁ ቡድኖች በርካታ ታጣቂዎች የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ሰላማዊ መንገድ መመለሳቸውን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በጫካ የቀሩትም ቢሆኑ በሂደት ነገሩ እየገባቸው ይመጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
መንግሥት በርካታ የፖለቲካ እስረኞችን ፈትቶ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ያሰፋ ቢሆንም፣ የተወሰኑ አካላት ግን ትናንት ካሰሯቸው እና ከገረፏቸው አካላት ጋር ድብቅ ጥምረት ፈጥረው ወደ ጫካ መግባታቸው አሳዝኖናል ብለዋል።
በኦሮሚያ ክልል ሰፊ የዴሞክራሲና የፖለቲካ ተሳትፎ ዕድል በመኖሩ በሰላማዊ መንገድ መታገል ይቻላል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በጫካ የሚገኘው የሸኔ ቡድን ግልጽ ዓላማ እና ግብ የሌለው "ተቀጣሪ ኃይል" ነው ሲሉ ገልጸውታል።
ቡድኑ ሽፍታ ሆኖ ሰዎችን ከመግደልና ከመዝረፍ ውጭ የፖለቲካ ፍላጎቱን ማሳካት እንደማይችልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
የኦነግ መስራች ታጋዮች በአሁኑ ወቅት በሰላማዊ መንገድ በሀገር ውስጥ እና በፓርላማ ተቀምጠው እየታገሉ ባሉበት ሁኔታ፣ በጫካ ያለው ቡድን የማንን አጀንዳ ይዞ እንደሚታገል ሕዝቡ ሊጠይቅ እንደሚገባም አሳስበዋል።
ማንኛውም አካል ፍላጎቱንና ጥያቄውን በሰላማዊ መንገድ እና በምክክር ማሳካት እንደሚችል ያመላከቱት ጠቅላይ ሚነስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ አሁንም ቢሆን የመንግሥት የሰላም በር ክፍት እንደሆነ አረጋግጠዋል።
🙈2
ተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
በተለያየ ማህበራዊ ችግር ውስጥ የነበሩ በየለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በ5ኛ ዙር የክህሎት እና የስብዕና ግንባታ የሰለጠኑ 858 እህቶቻችንን አስመርቀን ወደ ስራ አሰማርተናል።
በከተማችን ከምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አንዱ ትላንት በጎዳና፣ በችግር እና በተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶች ውስጥ የነበሩ ሴቶችን በሙያ ክህሎትና ስብዕና ገንብተን ከነበሩበት አስከፊ ህይወት በማውጣት ወደ ተሻለ ህይወት የምናሰማራበት ቀዳሚው ተግባር ነው።
አዲስ አበባችን ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት እንዲሁም ለዘመናት የከረሙ ስብራቶቿ የሚጠገኑባት ከተማ የማድረግ የተግባር ውጤት ፍሬ ማሳያዎች ከለነገዋ ተመርቀው አዲስ ህይወት እየመሩ ያሉት ሴቶች እህቶቻችን ናቸው።
የዛሬዎቹ ተመራቂዎችን ጨምሮ በማዕከሉ በድምሩ 3259 ሰልጣኞችን አስመርቀን ወደ ስራው ዓለም እንዲቀላቀሉ በማድረግ ህይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩና ለሌሎችም አርዓያ እንዲሆኑ አድርገናል።
ውድ ተመራቂዎች፤ አስከፊውን ትላንታችሁን አልፋችሁ፤ በማዕከሉ በነበራችሁ ቆይታ በቀሰማችሁት ክህሎት እና ባገኛችሁት የተሀድሶ ስልጠና ዛሬ ማሸነፍ ችላችኋል፤ ነገም በስራው ዓለም ስኬታማ ለመሆን የሚገጥማችሁን ማንኛውንም ፈተና አሸንፉችሁ ህይወታችሁን ይበልጥ ብሩህ እንደምታደርጉ እናምናለን።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
በተለያየ ማህበራዊ ችግር ውስጥ የነበሩ በየለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በ5ኛ ዙር የክህሎት እና የስብዕና ግንባታ የሰለጠኑ 858 እህቶቻችንን አስመርቀን ወደ ስራ አሰማርተናል።
በከተማችን ከምንሰራቸው ሰው ተኮር ስራዎች አንዱ ትላንት በጎዳና፣ በችግር እና በተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶች ውስጥ የነበሩ ሴቶችን በሙያ ክህሎትና ስብዕና ገንብተን ከነበሩበት አስከፊ ህይወት በማውጣት ወደ ተሻለ ህይወት የምናሰማራበት ቀዳሚው ተግባር ነው።
አዲስ አበባችን ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት እንዲሁም ለዘመናት የከረሙ ስብራቶቿ የሚጠገኑባት ከተማ የማድረግ የተግባር ውጤት ፍሬ ማሳያዎች ከለነገዋ ተመርቀው አዲስ ህይወት እየመሩ ያሉት ሴቶች እህቶቻችን ናቸው።
የዛሬዎቹ ተመራቂዎችን ጨምሮ በማዕከሉ በድምሩ 3259 ሰልጣኞችን አስመርቀን ወደ ስራው ዓለም እንዲቀላቀሉ በማድረግ ህይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩና ለሌሎችም አርዓያ እንዲሆኑ አድርገናል።
ውድ ተመራቂዎች፤ አስከፊውን ትላንታችሁን አልፋችሁ፤ በማዕከሉ በነበራችሁ ቆይታ በቀሰማችሁት ክህሎት እና ባገኛችሁት የተሀድሶ ስልጠና ዛሬ ማሸነፍ ችላችኋል፤ ነገም በስራው ዓለም ስኬታማ ለመሆን የሚገጥማችሁን ማንኛውንም ፈተና አሸንፉችሁ ህይወታችሁን ይበልጥ ብሩህ እንደምታደርጉ እናምናለን።
በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤3👏1