ዛሬ በቤኒን ሪፐብሊክ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና ኢኖቬሽን እና ፈጠራ ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋን የተመራውን የልዑክ ቡድን ተቀብለን በከተማችን እየተገበርነው ያለውን Smart City (ስሉጥ ከተማ) ግንባታ ልምድ አካፍለናል።
ቤኒን የጀመረችውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማሳካት በከተማችን ተግብረነው ውጤታማ እየሆነ ያለውን Smart City (ስሉጥ ከተማ) ግንባታ በተለይ በዋና ዋና ግቦች ( Smart Economy, Smart Environment, Smart Governance, Smart Living, Smart Mobility, Smart People) እና ለስኬቶቻችን መሰረት የሆኑት የተቋማት ቅንጅት፣ የህጎችና ደንቦች ትግበራ፣ የህዝብ ተሳትፎ፣ የመንግስትና የግል ዘርፍ ቅንጅታዊ ስራዎችን ለልዑክ ቡድኑ አካፍለናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ቤኒን የጀመረችውን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማሳካት በከተማችን ተግብረነው ውጤታማ እየሆነ ያለውን Smart City (ስሉጥ ከተማ) ግንባታ በተለይ በዋና ዋና ግቦች ( Smart Economy, Smart Environment, Smart Governance, Smart Living, Smart Mobility, Smart People) እና ለስኬቶቻችን መሰረት የሆኑት የተቋማት ቅንጅት፣ የህጎችና ደንቦች ትግበራ፣ የህዝብ ተሳትፎ፣ የመንግስትና የግል ዘርፍ ቅንጅታዊ ስራዎችን ለልዑክ ቡድኑ አካፍለናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
❤1
የኦሮሞ ሕዝብ በታሪኩ የተቃወመው የተበላሸ የአስተዳደር ሥርዓትን እንጂ ኢትዮጵያን አይደለም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የኦሮሞ ሕዝብ ነፃነት እና እኩልነት ታሪክ ከኢትዮጵያ ሀገር ግንባታ ጋር ያለውን ጥልቅ ቁርኝት በታሪካዊ ማሳያዎች እየጠቀሱ በስፋት አብራርተዋል።
የኦሮሞ ሕዝብ በታሪኩ የተቃወመው የተበላሸ የአስተዳደር ሥርዓትን እንጂ ሀገርን (ኢትዮጵያን) አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሀገርን በመገንባት ሂደትም ደሙን፣ አጥንቱን እና ላቡን ማፍሰሱን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ኦሮሞ ሕዝብ የረጅም ዘመን ትግል መነሻ ምክንያቶች እንዲሁም ትግሉ ግቡን ለመምታት ስለዘገየበት እና ስላጋጠሙት ተግዳሮቶች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም የኦሮሞ ሕዝብ የትግል ጥያቄዎች በዋናነት በሦስት መሠረታዊ ክፍሎች የሚከፈሉ መሆኑን እና እነዚህም የኢኮኖሚ፣ የማንነት እና የዴሞክራሲ ጥያቄ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኢኮኖሚ ጥያቄን በተመለከተ፦ ሕዝቡ የመሬት እና የሀብት ባለቤት የመሆን፣ በላቡ ሠርቶ የማደግ እና አካባቢውን የመቀየር ፍላጎት እንደነበረው ጠቁመዋል። መሬት ለኦሮሞ ሕይወቱ ቢሆንም፣ ይህ ሀብቱ ሲነጠቅ እና ሲበዘበዝ መቆየቱ እንዲሁም አራሹ አርሶ አምርቶ የመጠቀም መብት ማጣቱ ዋነኛ የትግል መነሻ ሆኗል ነው ያሉት።
የማንነት ጥያቄን በተመለከተ ደግሞ ይህ ጥያቄ አፋን ኦሮሞን ከመናገር ባለፈ ባህልን፣ ማንነትን፣ ሥነ-ምግባርን (ሰፉ)፣ ታላላቆችን፣ ፍጥረታትን እና ፈጣሪን ማክበርን በውስጡ ያካተተ ጥልቅ ጥያቄ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በኦሮሞነት ማንነት አድጎ ቋንቋን መናገር ብቻውን የማንነት ጥያቄን ሙሉ በሙሉ ይመልሳል ማለት አይቻልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ስለዚህ የቋንቋ፣ የባህል እና የማንነት ጥያቄዎች አሁንም እንዳሉ ጠቁመዋል።
ከዴሞክራሲ ጥያቄ አንጻር ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ የራሱ የሆነ አሳታፊ የገዳ ሥርዓት የነበረው ሕዝብ በመሆኑ፣ ራሱን በራሱ የማስተዳደር፣ የራሱን ሕግ የማውጣት እና በሕጉ የመተዳደር የረጅም ጊዜ ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ እንደነበረው ጠቁመዋል።
የመንግሥት አስተዳደር ደግሞ ሕዝቡ ከለመደው ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር አንፃር ተቃራኒ ሲሆንም ጥያቄዎችን ሲያነሣ እንደነበር ነው የገለጹት።
ይህ የኦሮሞ ሕዝብ ትግል ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ቢቆይም፣ በሚፈለገው ፍጥነት ድል ሳያመጣ የዘገየባቸውን ምክንያቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአራት ዋና ዋና ነጥቦች አስቀምጠዋል።
አንደኛው የስትራቴጂያዊ ሐሳብ እጥረት ነው፦ ምርት ለማግኘት ትራክተር ቢኖርም 'ምርጥ ዘር' ከሌለ ዋጋ እንደሌለው ሁሉ፣ የትግል ግብን ለማሳካት የሚያስችል ጥራት ያለው ስትራቴጂያዊ ሐሳብ አለመኖር ትልቁ ክፍተት ነበር ሲሉ በምሳሌ አስረድተዋል።
ሁለተኛው የአንድነት እጥረት ነው፡- ኦሮሞ በሰፊ መሬት ላይ የሚኖር እና የጋራ ማንነት ያለው ቢሆንም፣ በፖለቲካ ሴራዎች፣ በእምነት፣ በወንዝ እና በዞን በመከፋፈል ጠንካራ ውስጣዊ አንድነትን ማስቀጠል አለመቻሉን ጠቅሰዋል።
ሦስተኛ የግንኙነት አያያዝ ችግር፦ ከሌሎች ኃይሎች ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች በጊዜያዊ ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረቱ መሆናቸው እና የኦሮሞን ሕዝብ ፍላጎት ከማስከበር ይልቅ ለሌሎች ተገዢ ወይም አገልጋይ የሚያደርጉ በመሆናቸው በሂደቱ ላይ ትልቅ ጉዳት አምጥቷል ብለዋል።
አራተኛው የአመራር እጦት እና የአሸናፊነት ሥነ-ልቦና ማጣት ነው፦ ሕዝቡን አደራጅቶ እና አቅጣጫ አስይዞ ሊመራ የሚችል ትልቅ ዕይታ ያለው አመራር ማጣት እንቅፋት እንደነበር ነው አንሥተዋል።
ትግሉን ለማሸነፍ ልክ እንደ አንበሳ "የአሸናፊነት አስተሳሰብ" ይዞ መነሣት ሲገባው፣ ገና ከመጀመሪያው የመሸነፍ ስጋት ውስጥ መግባት የድል እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ነው የገለጹት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የኦሮሞ ሕዝብ ነፃነት እና እኩልነት ታሪክ ከኢትዮጵያ ሀገር ግንባታ ጋር ያለውን ጥልቅ ቁርኝት በታሪካዊ ማሳያዎች እየጠቀሱ በስፋት አብራርተዋል።
የኦሮሞ ሕዝብ በታሪኩ የተቃወመው የተበላሸ የአስተዳደር ሥርዓትን እንጂ ሀገርን (ኢትዮጵያን) አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሀገርን በመገንባት ሂደትም ደሙን፣ አጥንቱን እና ላቡን ማፍሰሱን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ኦሮሞ ሕዝብ የረጅም ዘመን ትግል መነሻ ምክንያቶች እንዲሁም ትግሉ ግቡን ለመምታት ስለዘገየበት እና ስላጋጠሙት ተግዳሮቶች ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በማብራሪያቸውም የኦሮሞ ሕዝብ የትግል ጥያቄዎች በዋናነት በሦስት መሠረታዊ ክፍሎች የሚከፈሉ መሆኑን እና እነዚህም የኢኮኖሚ፣ የማንነት እና የዴሞክራሲ ጥያቄ መሆናቸውን ተናግረዋል።
የኢኮኖሚ ጥያቄን በተመለከተ፦ ሕዝቡ የመሬት እና የሀብት ባለቤት የመሆን፣ በላቡ ሠርቶ የማደግ እና አካባቢውን የመቀየር ፍላጎት እንደነበረው ጠቁመዋል። መሬት ለኦሮሞ ሕይወቱ ቢሆንም፣ ይህ ሀብቱ ሲነጠቅ እና ሲበዘበዝ መቆየቱ እንዲሁም አራሹ አርሶ አምርቶ የመጠቀም መብት ማጣቱ ዋነኛ የትግል መነሻ ሆኗል ነው ያሉት።
የማንነት ጥያቄን በተመለከተ ደግሞ ይህ ጥያቄ አፋን ኦሮሞን ከመናገር ባለፈ ባህልን፣ ማንነትን፣ ሥነ-ምግባርን (ሰፉ)፣ ታላላቆችን፣ ፍጥረታትን እና ፈጣሪን ማክበርን በውስጡ ያካተተ ጥልቅ ጥያቄ እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በኦሮሞነት ማንነት አድጎ ቋንቋን መናገር ብቻውን የማንነት ጥያቄን ሙሉ በሙሉ ይመልሳል ማለት አይቻልም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ስለዚህ የቋንቋ፣ የባህል እና የማንነት ጥያቄዎች አሁንም እንዳሉ ጠቁመዋል።
ከዴሞክራሲ ጥያቄ አንጻር ደግሞ የኦሮሞ ሕዝብ የራሱ የሆነ አሳታፊ የገዳ ሥርዓት የነበረው ሕዝብ በመሆኑ፣ ራሱን በራሱ የማስተዳደር፣ የራሱን ሕግ የማውጣት እና በሕጉ የመተዳደር የረጅም ጊዜ ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ እንደነበረው ጠቁመዋል።
የመንግሥት አስተዳደር ደግሞ ሕዝቡ ከለመደው ዴሞክራሲያዊ አስተዳደር አንፃር ተቃራኒ ሲሆንም ጥያቄዎችን ሲያነሣ እንደነበር ነው የገለጹት።
ይህ የኦሮሞ ሕዝብ ትግል ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ቢቆይም፣ በሚፈለገው ፍጥነት ድል ሳያመጣ የዘገየባቸውን ምክንያቶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአራት ዋና ዋና ነጥቦች አስቀምጠዋል።
አንደኛው የስትራቴጂያዊ ሐሳብ እጥረት ነው፦ ምርት ለማግኘት ትራክተር ቢኖርም 'ምርጥ ዘር' ከሌለ ዋጋ እንደሌለው ሁሉ፣ የትግል ግብን ለማሳካት የሚያስችል ጥራት ያለው ስትራቴጂያዊ ሐሳብ አለመኖር ትልቁ ክፍተት ነበር ሲሉ በምሳሌ አስረድተዋል።
ሁለተኛው የአንድነት እጥረት ነው፡- ኦሮሞ በሰፊ መሬት ላይ የሚኖር እና የጋራ ማንነት ያለው ቢሆንም፣ በፖለቲካ ሴራዎች፣ በእምነት፣ በወንዝ እና በዞን በመከፋፈል ጠንካራ ውስጣዊ አንድነትን ማስቀጠል አለመቻሉን ጠቅሰዋል።
ሦስተኛ የግንኙነት አያያዝ ችግር፦ ከሌሎች ኃይሎች ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች በጊዜያዊ ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሠረቱ መሆናቸው እና የኦሮሞን ሕዝብ ፍላጎት ከማስከበር ይልቅ ለሌሎች ተገዢ ወይም አገልጋይ የሚያደርጉ በመሆናቸው በሂደቱ ላይ ትልቅ ጉዳት አምጥቷል ብለዋል።
አራተኛው የአመራር እጦት እና የአሸናፊነት ሥነ-ልቦና ማጣት ነው፦ ሕዝቡን አደራጅቶ እና አቅጣጫ አስይዞ ሊመራ የሚችል ትልቅ ዕይታ ያለው አመራር ማጣት እንቅፋት እንደነበር ነው አንሥተዋል።
ትግሉን ለማሸነፍ ልክ እንደ አንበሳ "የአሸናፊነት አስተሳሰብ" ይዞ መነሣት ሲገባው፣ ገና ከመጀመሪያው የመሸነፍ ስጋት ውስጥ መግባት የድል እንቅፋት ሆኖ መቆየቱን ነው የገለጹት።
የልደታ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለሶስት አቅመ ደካማ ወገኖች በአጭር ጊዜ ውስጥ ቤት ገንብቶ ለማስረከብ ወደ ስራ መግባቱን ገለፀ።
ነሀሴ 02/2018 (መልአ)
የልደታ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሦስት የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በአዲስ መልክ ገንብቶ ለማስረከብ ኃላፊነት ወስዶ ወደ ስራ ገብቷል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በ90 ቀን ዕቅዱ ከመደበኛ ተግባራት በተጓዳኝ ሰው ተኮር ስራዎችን አካቶ እየተገበረ መሆኑን የገለፁት የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን ጥላሁን
ከዚህም አንዱ የአቅመ ደካሞችን ቤት መገንባት ነው ብለዋል።
በዚህም ሜሪት ፕሮፐርቲስ ከተሰኝ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ሦስት የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ በአዲስ መልክ ገንብቶ ለማስረከብ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
ለበለጠ መረጃ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇👇👇👇👇👇
Website: - https://www.aalb.gov.et
https://linktr.ee/addisabababacityland
Email :-addisabababacityland@gmail.com
ነሀሴ 02/2018 (መልአ)
የልደታ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሦስት የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በአዲስ መልክ ገንብቶ ለማስረከብ ኃላፊነት ወስዶ ወደ ስራ ገብቷል።
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በ90 ቀን ዕቅዱ ከመደበኛ ተግባራት በተጓዳኝ ሰው ተኮር ስራዎችን አካቶ እየተገበረ መሆኑን የገለፁት የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ካሳሁን ጥላሁን
ከዚህም አንዱ የአቅመ ደካሞችን ቤት መገንባት ነው ብለዋል።
በዚህም ሜሪት ፕሮፐርቲስ ከተሰኝ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ሦስት የአቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በአጭር ጊዜ ውስጥ በአዲስ መልክ ገንብቶ ለማስረከብ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።
ለበለጠ መረጃ ትስስር ገፆቻችንን Like, Follow, subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
👇👇👇👇👇👇
Website: - https://www.aalb.gov.et
https://linktr.ee/addisabababacityland
Email :-addisabababacityland@gmail.com
❤2