AALTO -አዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
6.52K subscribers
467 photos
8 videos
119 files
25 links
Download Telegram
ቀን 13/08/2018 ዓ ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዛሬዉ ቀን ለግብር ከፋዮች በኢ-ከሊራንስ ላይ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በኢ ክሊራንስ ላይ ስልጠናዉን የሰጡት የመረጃ ቴክኖሎጂ አስተዳደር ድጋፍ ሰጪ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ ትዕዛዙ መንገሻ ሲሆኑ በዚሁ ወቅት ግብር ከፋዩ ይህንን ቴክኖሎጂ በአግባቡ በመጠቀም ካለበት ሆኖ ክሊራንሱን መጨረስ እንደሚችልና ጊዜዉን መቆጠብ እንደሚገባ አስገንዝቧል፡፡
በሌላ በኩል ለግብር ከፋዮች በስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ገበየሁ አካለወልድ ግብር ከፋዩ ሊኖረዉና ሊከተለዉ ስለሚገባ ስነምግባር እንዲሁም መብትና ግዴታ አጭር ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡
በመድረኩም ከሰልጣኞች የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን ምላሽም ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ስልጠናዉ አስፈላጊ እና ወቅቱን የጠበቀ በመሆኑ ለስራቸዉ በጣም ጠቃሚ እንደሆነ ሰልጣኞቹ በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል፡፡

የላቀ ገቢ አሰባሰብ ለአዲስ አበባ ብልጽግና!