Forwarded from ዓምደ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት በመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (Amde Haymanot Sunday School) (Mog)
በኦንላይን አማራጭ ካሉበት ሆነው ይማሩ፤ ሁልጊዜም ምዝገባ ሁልጊዜም ትምህርት አለ!
ይህን መልእክት ሌሎችም ያጋሩ !
በማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከተሉን
ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/AmdehaymanotSundayschool/
ዩትዩብ ፦ https://youtube.com/channel/UC_USHmHSlXg_-g0wwsPcQCg
ቲክ ቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZML9jVNJW/
ቴሌግራም፡ https://t.me/Amde_Haymanot_Sunday_School
ይህን መልእክት ሌሎችም ያጋሩ !
በማኅበራዊ ሚዲያዎቻችን ይከተሉን
ፌስቡክ ፦ https://www.facebook.com/AmdehaymanotSundayschool/
ዩትዩብ ፦ https://youtube.com/channel/UC_USHmHSlXg_-g0wwsPcQCg
ቲክ ቶክ፦ https://vm.tiktok.com/ZML9jVNJW/
ቴሌግራም፡ https://t.me/Amde_Haymanot_Sunday_School
◦◦●◉ የግጥም ጥም
ግጠም ግጠም ሲለኝ ስገጥም ስገጥም፣
ይኸው ደርሻለኹ እስከ... የግጥም ጥም።
አልገጥምም አልኩና ብቀመጥ አርፌ፣
ይወጋጋኝ ጀመር ውስጤ እንደ መርፌ።
ደግሞ ልጻፍ ብዬ አቅጄ ብነሣ፣
የትኛውን ትቼ የትኛውን ላንሣ?
ብዬ ስወላውል
ሳድር... ደግሞም ስውል
ግጥም ማ'ነሽ አንቺ ብዬ ብጠይቃት፣
ዝም አለችኝ...
ለካ ይህቺም ግ ጥ ም ናት
በዝምታም መልስ ያላት
ቢጽፉሽ ቢጽፉሽ አታልቂም እያልኳት።
ግጥምን እሷን ነው የጻፍኳት
ንገሯት ... ገጠምኳት
ለ ግ ጥ ም ግጥም ገጠምኩላት!
@Yoppoem
ግጠም ግጠም ሲለኝ ስገጥም ስገጥም፣
ይኸው ደርሻለኹ እስከ... የግጥም ጥም።
አልገጥምም አልኩና ብቀመጥ አርፌ፣
ይወጋጋኝ ጀመር ውስጤ እንደ መርፌ።
ደግሞ ልጻፍ ብዬ አቅጄ ብነሣ፣
የትኛውን ትቼ የትኛውን ላንሣ?
ብዬ ስወላውል
ሳድር... ደግሞም ስውል
ግጥም ማ'ነሽ አንቺ ብዬ ብጠይቃት፣
ዝም አለችኝ...
ለካ ይህቺም ግ ጥ ም ናት
በዝምታም መልስ ያላት
ቢጽፉሽ ቢጽፉሽ አታልቂም እያልኳት።
ግጥምን እሷን ነው የጻፍኳት
ንገሯት ... ገጠምኳት
ለ ግ ጥ ም ግጥም ገጠምኩላት!
@Yoppoem
!!!!
ፈገግ ብየ አልፌው ተታለለ ስንቱ
አሁን ግን ደከመኝ
ለጠየቀኝ ሁሉ ደህና ነኝ ማለቱ
አጣጥፎ ጥሎኛል ችሎ ባይሰብረኝም
ከመሞት በልጦብኝ መኖር አይስበኝም
እኔም ህልሜን አልተው እሱም አይደረስ
...ምናምን አትበለኝ
አይጥለኝም እንጂ እኔም ህመም አለኝ
ይልቅ እሱን ተወው..
አባብሎ ያቀፈህ ምቾትህን እርሳው
ብሶትህን ጣልና ብርታትህን አንሳው
ዳህ ተራመድ ሩጥ ህልምህን ብለጠው
ነገህ ላይ ለመቆም ትናንትን እርገጠው
በትልቁ አልመህ ትልቅ ነገር ሥራ
ከመውደቅህ በላይ ተስፋ መቁረጥ ፍራ
ግድየለም ሞክረው እንደው ባይመስልህም
መሮጥ እንደመቆም ቶሎ አያዝልህም🥵
ያስጎመዠ ሁሉ አይበላም ጣፍጦ
አንተ ህልምህን እመን
ማረፍ አያሾምም ከድካምህ በልጦ
ውደቅ ጣር ተነሳ ተጋጋጥ ይድከምህ
እንቅልፍህን እጣው ለነገ ላይጠቅምህ
ሚያባብልን ሙቀት
ሚሸፋፍን ምቾት ወደዛ ጣልና
ለራስህ አሳምን
አልችልም አትበለው ሞክር እንደገና
በብዙ ስትቆፍር ባንዱ ታገኛለህ
ድል የሚሰጥህን የህይወትን መፍቻ
ካንተ ሚጠበቀው
የላዩን ጌታ አምኖ መጣር መጋር ብቻ!
@Yoppoem
ፈገግ ብየ አልፌው ተታለለ ስንቱ
አሁን ግን ደከመኝ
ለጠየቀኝ ሁሉ ደህና ነኝ ማለቱ
አጣጥፎ ጥሎኛል ችሎ ባይሰብረኝም
ከመሞት በልጦብኝ መኖር አይስበኝም
እኔም ህልሜን አልተው እሱም አይደረስ
...ምናምን አትበለኝ
አይጥለኝም እንጂ እኔም ህመም አለኝ
ይልቅ እሱን ተወው..
አባብሎ ያቀፈህ ምቾትህን እርሳው
ብሶትህን ጣልና ብርታትህን አንሳው
ዳህ ተራመድ ሩጥ ህልምህን ብለጠው
ነገህ ላይ ለመቆም ትናንትን እርገጠው
በትልቁ አልመህ ትልቅ ነገር ሥራ
ከመውደቅህ በላይ ተስፋ መቁረጥ ፍራ
ግድየለም ሞክረው እንደው ባይመስልህም
መሮጥ እንደመቆም ቶሎ አያዝልህም🥵
ያስጎመዠ ሁሉ አይበላም ጣፍጦ
አንተ ህልምህን እመን
ማረፍ አያሾምም ከድካምህ በልጦ
ውደቅ ጣር ተነሳ ተጋጋጥ ይድከምህ
እንቅልፍህን እጣው ለነገ ላይጠቅምህ
ሚያባብልን ሙቀት
ሚሸፋፍን ምቾት ወደዛ ጣልና
ለራስህ አሳምን
አልችልም አትበለው ሞክር እንደገና
በብዙ ስትቆፍር ባንዱ ታገኛለህ
ድል የሚሰጥህን የህይወትን መፍቻ
ካንተ ሚጠበቀው
የላዩን ጌታ አምኖ መጣር መጋር ብቻ!
@Yoppoem
የዜግነት ክብር
ተምሬ ያደግሁት...
የዜግነት ክብር በማለት ዘምሬ
class የምገባ...
ስለ ሰንደቅ ክብር ብዙ ተመክሬ
ከክላስ ውስጥ ደግሞ...
የቀለሙን ትርጉም በ civics ተምሬ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
ሶስቱንም ቀለም...
በወርድ እና እርዝመት በእኩል ቀምሬ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
.ልዩነታችንን እንደ ጌጥ ቆጥሬ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
የክልልን ትርጉም
ብዙውን ሳላውቀው ብዙ ሳልረዳ
አስራ አንዱን ክልል
ሁሉንም አይቼ እንደ እናቴ ጓዳ
ሁሉን ቋንቋ ልወርስ
ሀሳቤን ስሸክፍ ምኞቴን ስነዳ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
በሶስቱ ቀለም በአንድ ሰንደቅ ታጥሬ አረንጓዴ...ቢጫ...ቀይ
በልቤ ዙፋን ላይ በእኩል ቀምሬ
ታድያ ምነው ዛሬ
አረንጓዴ ቢጫው ቀለሙ እየጠፋ
ቀዩ ቀለም ብቻ ከሰንደቁ ሠፋ
የዜግነት ክብር...
@Yoppoem
ተምሬ ያደግሁት...
የዜግነት ክብር በማለት ዘምሬ
class የምገባ...
ስለ ሰንደቅ ክብር ብዙ ተመክሬ
ከክላስ ውስጥ ደግሞ...
የቀለሙን ትርጉም በ civics ተምሬ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
ሶስቱንም ቀለም...
በወርድ እና እርዝመት በእኩል ቀምሬ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
.ልዩነታችንን እንደ ጌጥ ቆጥሬ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
የክልልን ትርጉም
ብዙውን ሳላውቀው ብዙ ሳልረዳ
አስራ አንዱን ክልል
ሁሉንም አይቼ እንደ እናቴ ጓዳ
ሁሉን ቋንቋ ልወርስ
ሀሳቤን ስሸክፍ ምኞቴን ስነዳ
እንዲህ ነው ያደግሁት...
በሶስቱ ቀለም በአንድ ሰንደቅ ታጥሬ አረንጓዴ...ቢጫ...ቀይ
በልቤ ዙፋን ላይ በእኩል ቀምሬ
ታድያ ምነው ዛሬ
አረንጓዴ ቢጫው ቀለሙ እየጠፋ
ቀዩ ቀለም ብቻ ከሰንደቁ ሠፋ
የዜግነት ክብር...
@Yoppoem
ሊዘጉብኝ ሲታገሉ ለማመንመን የኔን
መክሊት
በቀን ፀሀይ ያበረቱኝ በሩን ገፉ ያው
በለሊት
ፍሙን እሳት አመድ ሊያሹ ወዳጅ
መስለው ሲጠጋጉኝ
በድን አርገው ለመጣሉን የዋሁ እኔ
መች አወኩኝ !
ግን ባነንኩኝ
ሊሰብሩኝ ሲል ደነደንኩኝ
ማን አለው ብለው በድቅድቅ ሲርቁኝ
ጋኑን ከርችመው
ከፍቶታል የልቤን መስኮት እምነትን ከስሬ
አክርመው !
@Yoppoem
መክሊት
በቀን ፀሀይ ያበረቱኝ በሩን ገፉ ያው
በለሊት
ፍሙን እሳት አመድ ሊያሹ ወዳጅ
መስለው ሲጠጋጉኝ
በድን አርገው ለመጣሉን የዋሁ እኔ
መች አወኩኝ !
ግን ባነንኩኝ
ሊሰብሩኝ ሲል ደነደንኩኝ
ማን አለው ብለው በድቅድቅ ሲርቁኝ
ጋኑን ከርችመው
ከፍቶታል የልቤን መስኮት እምነትን ከስሬ
አክርመው !
@Yoppoem
አምላክን አመስግን
በምግብ እጦት ቢገረጣ ፊትህ
ልክ እንደአውሬ ሰው ሁሉ ቢሸሽህ
ቤተሰቤ ያልከው እንደባዳ ቢያይ
የልብ ጓደኛ ቢሆንም ገዳይ
የለበስከው ልብስህ ከብርድ ባያድንም
የምቆጥረው ገንዘብ ከኪስህ ባይኖርም
ምትመኘው ነገር ሆኖቢቀር ቅዠት
ያፈቀርካት ላንተ ክብር ባይኖራት
ሞላውትም ያልከው ሁሌም ቢጎልብ
በጎ ያልከው ነገር ክፋ ቢመዝብ
እጅ ስትዘረጋ ሰጪ ባታገኝም
የሰጠከው ሁሉ ምላሽ ባይሰጥህም
ጊዜ ያንተ ጠላት ሆኖ ቢዋጋህ
አምላክ ነው ብለህ አትዘን በድልህ
ይቺን እንድታነብ እድል የሰጠህን
ጎንበስ በልና አምላክን አመስግን
ተ መ ስ ገn
@Yoppoem
በምግብ እጦት ቢገረጣ ፊትህ
ልክ እንደአውሬ ሰው ሁሉ ቢሸሽህ
ቤተሰቤ ያልከው እንደባዳ ቢያይ
የልብ ጓደኛ ቢሆንም ገዳይ
የለበስከው ልብስህ ከብርድ ባያድንም
የምቆጥረው ገንዘብ ከኪስህ ባይኖርም
ምትመኘው ነገር ሆኖቢቀር ቅዠት
ያፈቀርካት ላንተ ክብር ባይኖራት
ሞላውትም ያልከው ሁሌም ቢጎልብ
በጎ ያልከው ነገር ክፋ ቢመዝብ
እጅ ስትዘረጋ ሰጪ ባታገኝም
የሰጠከው ሁሉ ምላሽ ባይሰጥህም
ጊዜ ያንተ ጠላት ሆኖ ቢዋጋህ
አምላክ ነው ብለህ አትዘን በድልህ
ይቺን እንድታነብ እድል የሰጠህን
ጎንበስ በልና አምላክን አመስግን
ተ መ ስ ገn
@Yoppoem