ሰሞኑን ለምርመራ ወደ አንድ የግል ክሊኒክ ሄድኩኝ። ዶክተሩን ሳየው ድሮ አብረን የተማርነው ዮሐንስን መሰለኝ። "ዮሐንስ ደግሞ እንዲህ ሊያረጅ አይችልም" ብዬ እያሰብኩ ተራዬ ደረሰና ገባሁ።
እንደገባሁ ጠየቅሁት፣
"አንተ ዮሐንስ ነህ እንዴ?"
"አዎ ነኝ" ሲለኝ በጣም በማርጀቱ ደነገጥኩና
"ዩኒቨርስቲ አውቅሃለሁ"
"ዋው! የምን አስተማሪያችን ነበርክ?"
ባሻዬ! ጠላትህ ይደንግጥ። እኔ ከሱ በላይ አርጅቻለሁ ማለት ነው? ሰው እኮ እንደ ዝንጀሮ ነው። የራሱ ቂጥ አይታየውም።
ⓒተስፋዬ ሃ/ማርያም
ከማዕደ ጥበብ ገፅ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
እንደገባሁ ጠየቅሁት፣
"አንተ ዮሐንስ ነህ እንዴ?"
"አዎ ነኝ" ሲለኝ በጣም በማርጀቱ ደነገጥኩና
"ዩኒቨርስቲ አውቅሃለሁ"
"ዋው! የምን አስተማሪያችን ነበርክ?"
ባሻዬ! ጠላትህ ይደንግጥ። እኔ ከሱ በላይ አርጅቻለሁ ማለት ነው? ሰው እኮ እንደ ዝንጀሮ ነው። የራሱ ቂጥ አይታየውም።
ⓒተስፋዬ ሃ/ማርያም
ከማዕደ ጥበብ ገፅ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
የዘመናችን የብሔረሰብ አለቆች በተወለዱበት ከተማ ውስጥ ሆስፒታል ለመስራት አምስት ሳንቲም አያወጡም ።ይሁን እንጂ የጀርመን ተራድኦ ድርጅት ሆስፒታል ቢያቆም በየትኛው ቋንቋ የተፃፈው ስሙ ይቅደም የትኛው ይከተል በሚለው ዙርያ ዱላ ቀረሽ ክርክር ሊያደርጉ ይችላሉ።
ምንጭ -ከአሜን ባሻገር መፅሐፍ
ደራሲ -በዕውቀቱ ሥዩም
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
ምንጭ -ከአሜን ባሻገር መፅሐፍ
ደራሲ -በዕውቀቱ ሥዩም
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
Book for ALL |
የትንሽ ነገር ... ከሲኣት ትንሿ እህቴ ከሩቅ እየተጣራች መጣች “እማዬ፣ እማዬ፣ እማዬ”
እናታችን ለጨረሩ መከላከያ መዳፏን ግንባሯ ላይ አጋድማ “ምነው? ምን ሆንሽ?” አለች “ዱላ ስጪኝ ዱላ ስጪኝ” “ምነው? ለምንሽ?” “አለቃ ተመረጥኩ” ዱላ አሳጥራ ሰጠቻት። . . . አመሻሽ ትንሿ እህቴ እያለቀሰች “እማዬ፣ እማዬ፣ እማዬ” እናታችን “ምነው? ምን ሆንሽ?” “ከአለቃነት ተሻርኩ”
¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤
ርዕስ፡ውልብታ"
ደራሲ፡አለማየሁ ገላጋይ ገጽ፡፶
---------------------------
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
የትንሽ ነገር ... ከሲኣት ትንሿ እህቴ ከሩቅ እየተጣራች መጣች “እማዬ፣ እማዬ፣ እማዬ”
እናታችን ለጨረሩ መከላከያ መዳፏን ግንባሯ ላይ አጋድማ “ምነው? ምን ሆንሽ?” አለች “ዱላ ስጪኝ ዱላ ስጪኝ” “ምነው? ለምንሽ?” “አለቃ ተመረጥኩ” ዱላ አሳጥራ ሰጠቻት። . . . አመሻሽ ትንሿ እህቴ እያለቀሰች “እማዬ፣ እማዬ፣ እማዬ” እናታችን “ምነው? ምን ሆንሽ?” “ከአለቃነት ተሻርኩ”
¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤¤
ርዕስ፡ውልብታ"
ደራሲ፡አለማየሁ ገላጋይ ገጽ፡፶
---------------------------
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
---------ላንመለስ
እንሂድ ብላኝ ተከትያት ፣
ቃል ስትሰጠኝ ቃል አምኛት ፣
ስትጎትተኝ ስጎተታት ፣
ስመናተል ሳባብላት ።
ኼዴን ኼዴን ኼዴን...
ላንመለስ መንገድ ጠፋን ።
---------------------------
"አሁንም አይደል ወደ ማታ.."
ገፅ - 100
ደራሲ - ሔኖክ ደመቀ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
እንሂድ ብላኝ ተከትያት ፣
ቃል ስትሰጠኝ ቃል አምኛት ፣
ስትጎትተኝ ስጎተታት ፣
ስመናተል ሳባብላት ።
ኼዴን ኼዴን ኼዴን...
ላንመለስ መንገድ ጠፋን ።
---------------------------
"አሁንም አይደል ወደ ማታ.."
ገፅ - 100
ደራሲ - ሔኖክ ደመቀ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
🎉🎉💥💥ቤተሰብ 💥💥🎉🎉
👏👏👏1K💎 ገብተናል👏👏👏
🎉🎉እንኳን ደስ አለን🎉🎉
አብሮነታችሁ አይለየን ተያይዘን ወደ 2K እንዘልቃለን
Share 🤩 በማድረግ ላገዛችሁን ፈጣሪ ያክብርልን ያላደረጋችሁ ደግሞ የ2K ጉዞ ላይ አሻራችሁ ያስፈልገናል። በብዙ ክበሩ🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
💥🎉🔥🎉💥🎉🏵🎉🔥💥
ኪነ - ቃል❤
👏👏👏1K💎 ገብተናል👏👏👏
🎉🎉እንኳን ደስ አለን🎉🎉
አብሮነታችሁ አይለየን ተያይዘን ወደ 2K እንዘልቃለን
Share 🤩 በማድረግ ላገዛችሁን ፈጣሪ ያክብርልን ያላደረጋችሁ ደግሞ የ2K ጉዞ ላይ አሻራችሁ ያስፈልገናል። በብዙ ክበሩ🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
💥🎉🔥🎉💥🎉🏵🎉🔥💥
ኪነ - ቃል❤
ስልጣንሽ ያልገባኝ
ልረሳሽ አስቤ . . .
ፎቶሽን ቀደድኩኝ
አንቺን ማስታወሻ
ሁሉን አቃጠልኩኝ
ልነግርሽ ያልኩትን
ከምላሴ ጣልኩኝ።
ሞከርኩኝ።
አንቺን ላለማሰብ
ልቤን አተጋሁኝ
ስምሽን ከከንፈሬ
ቀፍፌ አነሳሁኝ።
ግና
የማራቅ ጉዞዬ
በማጣት ሲተካ
እንደ ላጲስ ገላ
ሳጠፋሽ ስጠፋ . . .
አንቺ እያለሽ ያለው ፥ ወጥተሽ ከቀረው ጋር
ህይወቴ ሲናጸር ፣ መኖር ሲለካ
ታወቀኝ. . .
እኔን ስል የኖርኹት ፥ አንቺን ነበር ለካ።
ከዘንባባ መፅሐፍ
ምግባር ሲራጅ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ልረሳሽ አስቤ . . .
ፎቶሽን ቀደድኩኝ
አንቺን ማስታወሻ
ሁሉን አቃጠልኩኝ
ልነግርሽ ያልኩትን
ከምላሴ ጣልኩኝ።
ሞከርኩኝ።
አንቺን ላለማሰብ
ልቤን አተጋሁኝ
ስምሽን ከከንፈሬ
ቀፍፌ አነሳሁኝ።
ግና
የማራቅ ጉዞዬ
በማጣት ሲተካ
እንደ ላጲስ ገላ
ሳጠፋሽ ስጠፋ . . .
አንቺ እያለሽ ያለው ፥ ወጥተሽ ከቀረው ጋር
ህይወቴ ሲናጸር ፣ መኖር ሲለካ
ታወቀኝ. . .
እኔን ስል የኖርኹት ፥ አንቺን ነበር ለካ።
ከዘንባባ መፅሐፍ
ምግባር ሲራጅ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
The Passion Of The Christ በአማርኛ "የክርስቶስ ጥልቅ ፍቅር" ማለት ሲሆን ይህ ፊልም እኤአ በ2004 በUnited States of አሜሪካ ከታላቁ መፅሐፍ ቅዱስ የሀዲስ ኪዳን ክፍል በሆኑት ማቴዎስ ወንጌል ፣ ማርቆስ ወንጌል እና ዮሐንስ ወንጌል ላይ ተመስርቶ የተሰራ የአንድ ሰዓት ከ34 ደቂቃ ርዝማኔ ያለው ፊልም ነው::
ፊልሙ በታዋቂው የሆሊውድ ፊልም ባለሞያ ሚል ጊብሰን ዳይሬክት እና ፕሮዲውስ የተደረገ ሲሆን እንዲሁም በፊልሙ ጂም ካቪዜል እንደ 'ናዝሬቱ ኢየሱስ' ሚያ ሞርገንስተር እንደ 'ድንግል ማርያም' ሞኒካ ቤሉቺ እንደ 'መቅደላዊት ማርያም' በመሆን በድንቅ በቃት ተውንውበታል::
__
ታዲያ የሚገርመው ይሄን ፊልም ሰርቶ ለመጨረስ ባለው ውጣ ውረድ ውስጥ ብዙ አስደንጋጭ እና አስገራሚ እውነታዎች ገጠሟቸው እንደነበር ጂም ካቪዚል እና ዳይሬክተሩ ሚል ጊብሰን የቴሌቭዥን ሾው ላይ ቀርበው አስረድተዋል
___
የኢየሱስ ክርስቶስን ገፀ-ባህሪ ተላብሶ የተወነው ጂም 130 ፓውንድ ወይም 68 ኪሎ ግራም የሚመዝነውን መስቀል ተሸክሞ በሚሄድበት ትዕይንት ወቅት መስቀሉ ጂም ላይ ወድቆበት የግራ ተከሻው ውልቃት ደርሶበታል:: ጂም ይህንን ክስተት ለጋዜጠኛ ሲያስረዳ "መስቀሉን ተሸክሜ ስሄድ በጣም ከብዶኝ ስለነበረ ፊቴ ላይ የሚታየው ስሜት እወነተኛ የስቃይ ስሜት ነበር" ብሏል::
ሌላው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅና እግሩ ታስሮ በአደባባይ ጲላጦስ ፊት የሚገረፍበትን ትዕይንት ለማሳየት እንደ ክርስቶስ ሆኖ የሚተውነው ጂም እጅና እግሩ ታስሮ ባለበት ገራፊው ድንገት በያዘው ጅራፍ ሁለቴ ሲገርፈው ጂም እጅግ በጣም የህመም ስሜት እንደተሰማው ይናገራል:: "እንደ ክርስቶስ ሆኜ እየሰራው በህመሙ ምክንያት ግን ገራፊዎቼ ላይ እንደ ሰይጣን ነበር የሆንኩባቸውም" ብሏል::
በዚህ ፊልም የጂም ጉዳት በዚህ ብቻ አላበቃም በቀረፃ ወቅት ሁለቴ በመብረቅ ተመቷል:: አንደኛው መስቀል ላይ ተሰቅሎ በሚቀረፅበት ሰዓት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በተራራ ላይ ሆኖ ደቀ መዝሙሮቹን እያስተማረ በሚቀረፅበት ሰዓት ነበር:: ጂም ሾው ላይ ቀርቦ ስለሁኔታው ሲያስረዳ "መብረቁ እንደሚመታኝ ታውቆኝ ነበር እናም ተራራ ላይ እያስተማርኩ ሳለ መታኝ ረዳት ዳይሬክተሩ መጥቶ Are you okay ሲለኝ መብረቁ ድጋሚ እሱንም መታው::
ሌላው አስገራሚው ነገር ደግሞ ይህን ፊልም ለመስራት የኢየሱስን ገፀ ባህሪ ተላብሶ የተወነው ጂም የጀርባውን ግርፋት እና አናቱ ላይ በተደረገው እሾህ አክሊል ምክንያት በፊቱ ላይ ይፈስ የነበረውን የደም ጎርፍ ለማሳየት በየቀኑ ለ10 ሰዓታት ያህል ቆሞ ሜካፕ ይሰራ ነበር :: ታዲያ ይህንን ሜካፕ ለመሰራት አስር ሰዓታትን በየቀኑ እርቃኑን ሰለሚቆም ለሳንባ ምች በሽታ ተዳርጎ ነበር::
_
ሌላኛው እውነታ ደግሞ ይህን ፊልም ለመስራት በገጠማቸው ገጠመኝ እና ባሳለፉት ሁነቶች ምክንያት አብዛኛው የፊልሙ ክሩ እምነታቸውን ወደ ክርስትና ሊቀይሩ ችለዋል:: ይሁዳን ሆኖ የተጫወተው ሉካ ሊኦኔል ፊልሙን ከመስራቱ በፊት በእግዚአብሔር መኖር የማያምን ሰው ነበር ነገር ግን ፊልሙን ሰርቶ ከጨረሰ በኋላ ከእነቤተሰቦቹ ጌታን ተቀብሎ ተጠመቀ:: ሌላም እንደዚሁ በፊልሙ ውስጥ ቴክኒካል ስራ የሚሰራ የነበረ ሰው እርሱም እንደዚሁ ተጠምቆ ጌታን ተቀብሏል
___
ሌላኛው ደግሞ ክርስቶስ በምድር መከራን በተቀበለበት ጊዜ ምንም አይነት የሙዚቃ መሳሪያ ባለመኖሩ ምክንያት የፊልሙ ዳይሬክተር ሜል ጊብሰን ምንም አይነት Musical Score ፊልሙ ላይ አይገባም ብሎ ነበር...ነገር ግን ምክትል ዳይሬክተሩ አንድ Musical Score ብቻ ይግባበት ብሎ ሃሳብ አስቀይሮት ገብቶ ነበር ያቺ አንድ Musical Scoreም በ2005 Oscar ላይ በቤስት Origional Sound ታጭታ አሸናፊ ሆናለች::
ሌላው አስደናቂ ነገር ይህን ሙሉ ፊልም ፕሮዲውስ ለማድርግ የትኛውም የፊልም ፕሮዳክሽን ስቱዲዮዎች ፈቃጀኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው የፊልሙ ዳይሬክተር ሚል ጊብሰን ከኪሱ 30ሚልየን ዶላር በማውጣት ነበር ፕሮዲውስ ያደረገው:: ታዲያ ፊልሙ ለዕይታ ከበቃ በኋላ ግን 18 ዕጥፍ ገቢ ማስገባት ችሏል ያ ማለት 611 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ነው::
____
ይህን አስደናቂ ፊልም ለህዝብ ዕይታ ሲወጣ ሲኒማ ቤቶች ደጃቸው በወረፋ ተጥለቅልቆ ነበር የሚገርመው በወረፋ ተጋፍተው ገብተው የኢየሱስን ግርፋትና ስቃይ ማየት አቅቷቸው አቋርጠው የወጡ ለመቁጠር የሚያታክቱ ቢሆኑም መከራና ስቃዩን በእንባ እየታጠቡ ያዩ ደግሞ እልፍ ነበሩ
አበቃሁ!
Yoakin bekele
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
👍1
ስልኬን አንስቼ ደወልኩለት. . .
"ሄሎ"
"ሄሎ ሰላም ነው?"
"አለሁ።"
"ምን እየሰራሽ ነው?"
"እኔ?.... እዚህ ተኝቼ አንተን አስባለሁ።"
"እኔም አንቺን እያሰብኩ ነበር።"
"ለምን አልደወልክም?"
"ፈርቼሽ።"
ለምን ፈራኸኝ?
"እውነት ስላሌሽ።"
"እውነቴ ከአንተ አይበልጥም።"
"ስልክህን ስጠብቅ ዛሬን አንድ ቀን አመታት ኖርኩኝ። ያረክብኝን ሳይሆን አለመደወልህን ሳንሰላስል ብዙ ብዙ አሰብኩ።"
"ምን አሰብሽ?"
"አንተን ማጣት፣
አንተን መተው፣
አንተን መርሳት፣
አንተን ነበረ ማለት፣
አንተን ድሮ ማለት፣
አንተን የበፊቱ ማለት፣
ከዛ ፈራሁ፣
አለቀስኩ፣
አልተፅናናሁም፣
ከራሴ ተጣላሁ፣
ከኔ በለጥክብኝ። ከኔ ገዘፍክብኝ።"
( እሱ ይሰማኛል እኔ አወራለሁ )
"አ ፈ ቅ ር ሃ ለ ው እኮ. . . . ስቅስቅታዬ ቃለን ቆረጠው።"
( በደረቀ ቆፈናም ድምፀት)
"በድዬሻለሁ እኮ አለኝ።"
"ቶሎ ብዬ ይቅር ብየሃለው አልኩት. . . ."
"ፀጥ አለ። እረጭ። እረጅም ዝምታ. . . . .ዝም አለ።"
( እንባዬ ይወርዳል ቃሉን ጠብቃለሁ. . . .)
( በተሰበረ ድምፅ )
"አይገባኝም። አለኝ"
"እሱን የመወሰን መብት የለህም። አልኩት ቆጣ ብዬ"
(የመተው ዋዜማ ላይ እንዳለሁ ሲሰማኝ ነው የዋለው። እሱ በልቡ ያሰበውን በልቤ ሰምቼው ኖሯል። የማፍቀር ትልቁ ጥበብ ያፈቀሩትን ሰው ልብ ማድመጥ ነው መሰለኝ። ለካንስ እውነት ነበር።)
"ማሬ አልችልም። አለኝ"
ስፈራ ስተባ. . . ም ኑ ን? አልኩት
"ይሄን ተሸክሜ አብረሽ መሆን አልችልም። ይቅርታ ስልኩን ልዘጋው ነው።"
"ቆይ ቆይ ላስረዳህ. . . እንደዚህ አይደለም እኮ ፣ የኔ ፍቅር እንዳዘጋው በፈጠረህ"
"ማሬ አሁን ላወራሽ አልችልም።"
( ተ ዘ ጋ )
የጆሮዬ ታንቡር ላይ ኃይለኛ ፍንዳታ የጮኸብኝ አይነት ፣ ተሰማኝ ጭውውው.... አለብኝ ነገር አለሙ ዞረብኝ ፣ መላ ሰውነቴ ሲቀዘቅዝ ተሰማኝ። በረደኝ። ልቤ ስብርባሪው እስከማይገኝ ድረስ ተሰባበረ። መጮህ አማረኝ። በርግጥ መጮህ ያንስብኛል። በኃይል ማንባረቅ ፈለኩ። ትንፋሽ አጠረኝ። ልቤ ላይ አጥወለወለኝ። አንድ ሰው እንዴት በዳይም ጎጂም መሆን ይፈልጋል!? ብዬ ራሴን ጠየኩኝ። ግን እሱ ነው አይደል!? ያፈቅረኛል ብየ የማስበው ሰው ፣ ሁሉ ነገሬን አሳልፌ የሰጠሁት ሰው። አላውቀውም ነበር ማለት ነው!?. . . . ከበደለኝ በደል በላይ የጎዳኝ ይሄኛው ድርጊቱ ነበር። ልቤን ሀዘን ሲውጠው ይሰማኛል። በርግጥ ሀዘንና መጎዳት ራሱ ፣ አሁን እየተሰማኝ ያለውን ስሜት አይገልፀውም። ሌላ ቃል ያስፈልገዋል ፣ የሆነ ባዶነት ውስጥ እንዳለሁ እየተሰማኝ ነው።
✍ሰብለ ወንጌል(fb)
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
"ሄሎ"
"ሄሎ ሰላም ነው?"
"አለሁ።"
"ምን እየሰራሽ ነው?"
"እኔ?.... እዚህ ተኝቼ አንተን አስባለሁ።"
"እኔም አንቺን እያሰብኩ ነበር።"
"ለምን አልደወልክም?"
"ፈርቼሽ።"
ለምን ፈራኸኝ?
"እውነት ስላሌሽ።"
"እውነቴ ከአንተ አይበልጥም።"
"ስልክህን ስጠብቅ ዛሬን አንድ ቀን አመታት ኖርኩኝ። ያረክብኝን ሳይሆን አለመደወልህን ሳንሰላስል ብዙ ብዙ አሰብኩ።"
"ምን አሰብሽ?"
"አንተን ማጣት፣
አንተን መተው፣
አንተን መርሳት፣
አንተን ነበረ ማለት፣
አንተን ድሮ ማለት፣
አንተን የበፊቱ ማለት፣
ከዛ ፈራሁ፣
አለቀስኩ፣
አልተፅናናሁም፣
ከራሴ ተጣላሁ፣
ከኔ በለጥክብኝ። ከኔ ገዘፍክብኝ።"
( እሱ ይሰማኛል እኔ አወራለሁ )
"አ ፈ ቅ ር ሃ ለ ው እኮ. . . . ስቅስቅታዬ ቃለን ቆረጠው።"
( በደረቀ ቆፈናም ድምፀት)
"በድዬሻለሁ እኮ አለኝ።"
"ቶሎ ብዬ ይቅር ብየሃለው አልኩት. . . ."
"ፀጥ አለ። እረጭ። እረጅም ዝምታ. . . . .ዝም አለ።"
( እንባዬ ይወርዳል ቃሉን ጠብቃለሁ. . . .)
( በተሰበረ ድምፅ )
"አይገባኝም። አለኝ"
"እሱን የመወሰን መብት የለህም። አልኩት ቆጣ ብዬ"
(የመተው ዋዜማ ላይ እንዳለሁ ሲሰማኝ ነው የዋለው። እሱ በልቡ ያሰበውን በልቤ ሰምቼው ኖሯል። የማፍቀር ትልቁ ጥበብ ያፈቀሩትን ሰው ልብ ማድመጥ ነው መሰለኝ። ለካንስ እውነት ነበር።)
"ማሬ አልችልም። አለኝ"
ስፈራ ስተባ. . . ም ኑ ን? አልኩት
"ይሄን ተሸክሜ አብረሽ መሆን አልችልም። ይቅርታ ስልኩን ልዘጋው ነው።"
"ቆይ ቆይ ላስረዳህ. . . እንደዚህ አይደለም እኮ ፣ የኔ ፍቅር እንዳዘጋው በፈጠረህ"
"ማሬ አሁን ላወራሽ አልችልም።"
( ተ ዘ ጋ )
የጆሮዬ ታንቡር ላይ ኃይለኛ ፍንዳታ የጮኸብኝ አይነት ፣ ተሰማኝ ጭውውው.... አለብኝ ነገር አለሙ ዞረብኝ ፣ መላ ሰውነቴ ሲቀዘቅዝ ተሰማኝ። በረደኝ። ልቤ ስብርባሪው እስከማይገኝ ድረስ ተሰባበረ። መጮህ አማረኝ። በርግጥ መጮህ ያንስብኛል። በኃይል ማንባረቅ ፈለኩ። ትንፋሽ አጠረኝ። ልቤ ላይ አጥወለወለኝ። አንድ ሰው እንዴት በዳይም ጎጂም መሆን ይፈልጋል!? ብዬ ራሴን ጠየኩኝ። ግን እሱ ነው አይደል!? ያፈቅረኛል ብየ የማስበው ሰው ፣ ሁሉ ነገሬን አሳልፌ የሰጠሁት ሰው። አላውቀውም ነበር ማለት ነው!?. . . . ከበደለኝ በደል በላይ የጎዳኝ ይሄኛው ድርጊቱ ነበር። ልቤን ሀዘን ሲውጠው ይሰማኛል። በርግጥ ሀዘንና መጎዳት ራሱ ፣ አሁን እየተሰማኝ ያለውን ስሜት አይገልፀውም። ሌላ ቃል ያስፈልገዋል ፣ የሆነ ባዶነት ውስጥ እንዳለሁ እየተሰማኝ ነው።
✍ሰብለ ወንጌል(fb)
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
👍1
#ኤያስ_መልካ ………አበደ……!!!
ወደ 90 ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ላይ ኤሊያስ ከሚዲያውም ከምሽት ቤቶችም አካባቢ እራቀ እራሱንም ለመንፈሳዊነት አስገዝቶ ስራ እና ስራው ላይ ብቻ አተኮረ ታዲያ በኤሊያስ መጥፋት ላይ ወሬ እና አሉባልታው በረከተ ሙዚቃ አቁሞ ነው፣ታሞ ነው፣እና ከሁሉ የሚገርመው ደሞ አብዶ ነው የሚልም አሉባልታ ነበር ወሬ እና አሉባልታው በተወራበት ቦታ ብቻ አልቀረም ኤሊያስ ወዳጆች ጆሮ ገባ እና ስጋት የገባቸው ወዳጆቹ እየተወራ ስላለው ነገር መጥተው እንዲህ እየተወራ ነው አሉት …ትኩረቱን በስራው ላይ ያደረገው ኤሊያስ ጉዳዩን ሲነግሩት ወትሮም ግጥም ያለምክንያት ለማይፅፈው ኤሊያስ መልካ ትልቅ ግብአት ነበርና የተወረወረበትን ጠጠር ለቅሞ ለፍቅረኛ የተዜመ አስመስሎ እንደሚከተለው አርጎ ሙዚቃውን አስውቦ ገነባው…
"" ይዘባርቃሉ
ሳይገባቸው ነገሩ ሁሉ
ከቶ ለምን ፈራሽ
ማንነቴን በደንብ እያወቅሽ …………""
ከስጋታቸው መላቀቅ ያልቻሉ ወዳጆቹ ግን አሁንም ወሬው በእነሱ ይመጣ ጀመር ይሄኔ ኤሊያስ ወዳጆቹንም ገሰፅ ማድረግን አሰበና የሚከተለውን ጨመረበት ……
"" ፍቅርሽ ላይ ያንቺን ጉዳይ
ማን ያውቃል ካንቺ በላይ
አልፈርድም በማያውቁ
ላንቺ ነው ግልፅ የሆንኩ ""
ሳያዩ ለሚያወሩ እድል አትስጡ እናንተ በቅርብ ስለ እኔ ሁሉን እያያችሁ ሳለ በ እሩቅ ስለሚያወሩ አትጨነቁ ………
"" ውሎ ሲያድር ይረዱታል ""
እያለ ሞገተ አስከትሎም………
"" አታውሪ ደግመሽ ለእኔ
እያየሽ ሆነሽ ጎኔ
ሆድ ባሰኝ እያወቅሽኝ
መሰለኝ አንቺም ያልሽኝ ""
እነሱ የሚያወሩትን አትድገሙልኝ የእነሱን ባወራችሁ ቁጥር እናንተም ያላችሁኝ ነው የሚመስለኝ አለ …እሺ ቢያንስ በየሚዲያው እየወጣን እናስተባብል አይነት ምክር ተሰነዘረለት ………የኤሊያስም መልስ የሚከተለው ሆነ
""" ግድ የለብንም ማሳመር
ሌሎቹን ለማሳመን
ውሎ ሲያድር ይረዱታል
ኋላ ያፍሩበታል ""……
ይሄውላችሁ ኤሊያስ እንዲህ ያለ ጥበበኛ ሰው ነበር የ ኢዮብ መኮንን " ይዘባርቃሉ " track መነሻ ታሪኩ ይሄ ነው …!!!
ዘመን በይሻራቸው አድረው እንደወይን ጠጅ በሚጣፍጡ ስራዎቹ ሁሌም በልባችን ይኖራል 💖
#ኤሊያስ_መልካ_ኢዮብ_መኮንን የሁለቱንም ነፍስ ይማርልን 💔
✍ቤዛ አዲሱ !!!
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ወደ 90 ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ላይ ኤሊያስ ከሚዲያውም ከምሽት ቤቶችም አካባቢ እራቀ እራሱንም ለመንፈሳዊነት አስገዝቶ ስራ እና ስራው ላይ ብቻ አተኮረ ታዲያ በኤሊያስ መጥፋት ላይ ወሬ እና አሉባልታው በረከተ ሙዚቃ አቁሞ ነው፣ታሞ ነው፣እና ከሁሉ የሚገርመው ደሞ አብዶ ነው የሚልም አሉባልታ ነበር ወሬ እና አሉባልታው በተወራበት ቦታ ብቻ አልቀረም ኤሊያስ ወዳጆች ጆሮ ገባ እና ስጋት የገባቸው ወዳጆቹ እየተወራ ስላለው ነገር መጥተው እንዲህ እየተወራ ነው አሉት …ትኩረቱን በስራው ላይ ያደረገው ኤሊያስ ጉዳዩን ሲነግሩት ወትሮም ግጥም ያለምክንያት ለማይፅፈው ኤሊያስ መልካ ትልቅ ግብአት ነበርና የተወረወረበትን ጠጠር ለቅሞ ለፍቅረኛ የተዜመ አስመስሎ እንደሚከተለው አርጎ ሙዚቃውን አስውቦ ገነባው…
"" ይዘባርቃሉ
ሳይገባቸው ነገሩ ሁሉ
ከቶ ለምን ፈራሽ
ማንነቴን በደንብ እያወቅሽ …………""
ከስጋታቸው መላቀቅ ያልቻሉ ወዳጆቹ ግን አሁንም ወሬው በእነሱ ይመጣ ጀመር ይሄኔ ኤሊያስ ወዳጆቹንም ገሰፅ ማድረግን አሰበና የሚከተለውን ጨመረበት ……
"" ፍቅርሽ ላይ ያንቺን ጉዳይ
ማን ያውቃል ካንቺ በላይ
አልፈርድም በማያውቁ
ላንቺ ነው ግልፅ የሆንኩ ""
ሳያዩ ለሚያወሩ እድል አትስጡ እናንተ በቅርብ ስለ እኔ ሁሉን እያያችሁ ሳለ በ እሩቅ ስለሚያወሩ አትጨነቁ ………
"" ውሎ ሲያድር ይረዱታል ""
እያለ ሞገተ አስከትሎም………
"" አታውሪ ደግመሽ ለእኔ
እያየሽ ሆነሽ ጎኔ
ሆድ ባሰኝ እያወቅሽኝ
መሰለኝ አንቺም ያልሽኝ ""
እነሱ የሚያወሩትን አትድገሙልኝ የእነሱን ባወራችሁ ቁጥር እናንተም ያላችሁኝ ነው የሚመስለኝ አለ …እሺ ቢያንስ በየሚዲያው እየወጣን እናስተባብል አይነት ምክር ተሰነዘረለት ………የኤሊያስም መልስ የሚከተለው ሆነ
""" ግድ የለብንም ማሳመር
ሌሎቹን ለማሳመን
ውሎ ሲያድር ይረዱታል
ኋላ ያፍሩበታል ""……
ይሄውላችሁ ኤሊያስ እንዲህ ያለ ጥበበኛ ሰው ነበር የ ኢዮብ መኮንን " ይዘባርቃሉ " track መነሻ ታሪኩ ይሄ ነው …!!!
ዘመን በይሻራቸው አድረው እንደወይን ጠጅ በሚጣፍጡ ስራዎቹ ሁሌም በልባችን ይኖራል 💖
#ኤሊያስ_መልካ_ኢዮብ_መኮንን የሁለቱንም ነፍስ ይማርልን 💔
✍ቤዛ አዲሱ !!!
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ጠቃሚ ትምህርት!
በጃፓን ይማር የነበረ አንድ አፍሪካዊ ወጣት በአንድ ወቅት በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዲህ ሲል ጽፏል።
በጃፓን ባለ ፣ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል እንግዳ ነበርኩ ፣ እና እኔ በምኖርበት ሆቴል መዋኛ ገንዳ ውስጥ እያለሁ ፣ ገንዳው ውስጥ ከእኔ በቀር ማንም አልነበረም ፣ ውሃው ስር ሽንቴ አመለጠኝ ፣ እናም ድንገት... ውሃው ወደ ሮዝ ተለወጠ።
አላርም (ማንቂያው) ጮኸ ወዲያው ሰራተኞቹ መጥተው ከገንዳው ውስጥ አወጡኝ። ከዚያም ውሃውን ባዶ እንደሚያደርጉት እና ገንዳውን እንደሚያጸዱ ነገሩኝ። የሆቴሉን አስፈላጊ ህግና ደንብ እንደጣስኩም ነገሩኝ።
ከዚያ በኋላ ጠሩኝና እንግዳ ተቀባይዋ ፓስፖርቴን ሰጠችኝና ከሆቴሉ እንድወጣ ጠየቀችኝ።
ከሆቴሉ ወጥቼ ሌላ አማራጭ ፈለግሁ ፣ እና ሆቴል በገባሁ ቁጥር እንግዳ ተቀባዩ ፓስፖርቴን እያየ “ይቅርታ ፣ አንተ ነህ…!?… እኛ ስላልተቀበልንህ ይቅርታ…! ሌሎች ሆቴሎችም ስሄድ ተመሳሳይ ነው… በየትኛውም ሆቴል እንዳላርፍ ስለተከለከልኩ ወደ ኤምባሲው ሄድኩ።
ኤምባሲዬ የመዋኛ ገንዳ የሌለው ሆቴል እንድይዝ መከሩኝ...።
ከጃፓን ስወጣ የፓስፖርት ሹሟ ፓስፖርቴን ስታረጋግጥ ‹ ትምህርቱን እንደተማርክ ተስፋ አደርጋለሁ› አለችኝ።
ማጠቃለያ፡- ሁሉም ጃፓናዊ ሽንቴን በመዋኛ ገንዳ ውስጥ እንደሸናሁ ያውቅ ነበር ፤ እኔ የመጣሁባት አፍሪካዊት ሀገሬ ላይ ግን እስካሁን ድረስ መንግስታችን ከመንግስት ግምጃ ቤት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሰረቀ ማን እንደሆነ አያውቅም።
#ምንጭ:Tales Of Africa
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
በጃፓን ይማር የነበረ አንድ አፍሪካዊ ወጣት በአንድ ወቅት በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዲህ ሲል ጽፏል።
በጃፓን ባለ ፣ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል እንግዳ ነበርኩ ፣ እና እኔ በምኖርበት ሆቴል መዋኛ ገንዳ ውስጥ እያለሁ ፣ ገንዳው ውስጥ ከእኔ በቀር ማንም አልነበረም ፣ ውሃው ስር ሽንቴ አመለጠኝ ፣ እናም ድንገት... ውሃው ወደ ሮዝ ተለወጠ።
አላርም (ማንቂያው) ጮኸ ወዲያው ሰራተኞቹ መጥተው ከገንዳው ውስጥ አወጡኝ። ከዚያም ውሃውን ባዶ እንደሚያደርጉት እና ገንዳውን እንደሚያጸዱ ነገሩኝ። የሆቴሉን አስፈላጊ ህግና ደንብ እንደጣስኩም ነገሩኝ።
ከዚያ በኋላ ጠሩኝና እንግዳ ተቀባይዋ ፓስፖርቴን ሰጠችኝና ከሆቴሉ እንድወጣ ጠየቀችኝ።
ከሆቴሉ ወጥቼ ሌላ አማራጭ ፈለግሁ ፣ እና ሆቴል በገባሁ ቁጥር እንግዳ ተቀባዩ ፓስፖርቴን እያየ “ይቅርታ ፣ አንተ ነህ…!?… እኛ ስላልተቀበልንህ ይቅርታ…! ሌሎች ሆቴሎችም ስሄድ ተመሳሳይ ነው… በየትኛውም ሆቴል እንዳላርፍ ስለተከለከልኩ ወደ ኤምባሲው ሄድኩ።
ኤምባሲዬ የመዋኛ ገንዳ የሌለው ሆቴል እንድይዝ መከሩኝ...።
ከጃፓን ስወጣ የፓስፖርት ሹሟ ፓስፖርቴን ስታረጋግጥ ‹ ትምህርቱን እንደተማርክ ተስፋ አደርጋለሁ› አለችኝ።
ማጠቃለያ፡- ሁሉም ጃፓናዊ ሽንቴን በመዋኛ ገንዳ ውስጥ እንደሸናሁ ያውቅ ነበር ፤ እኔ የመጣሁባት አፍሪካዊት ሀገሬ ላይ ግን እስካሁን ድረስ መንግስታችን ከመንግስት ግምጃ ቤት በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሰረቀ ማን እንደሆነ አያውቅም።
#ምንጭ:Tales Of Africa
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
#ውሉድ ወወላድ*
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም ! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ ! ምግባሩ ካለየ ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መሆን ክብር በከንቱ አይሰጥም !
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም !
እፍኝትን እይዋት . . .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣ በፍትወት መቃጠል ።
አንበሳም ደቦሉን . . .
በጊዜው ካልቀጣ ንግስናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል ።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ ፣
ካልተነፃፀረ ፤
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ ።
#የሞት ጥቁር ወተት
#ተስፋሁን ከበደ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
የወለደች ኹሉ . . .
እናት አትባልም ! ግብሯ ካልተለየ ፤
የተወለደ ልጅ . . .
አይባልም ጧሪ ! ምግባሩ ካለየ ።
ዘር ስላካፈለ . . .
የአባት መሆን ክብር በከንቱ አይሰጥም !
ከልጅ ስም ቀጥሎ ስሙ አይቀመጥም !
እፍኝትን እይዋት . . .
እናት ትሞታለች ፣ ትውልድ ለማስቀጠል
አባትም ይሠዋል ፣ በፍትወት መቃጠል ።
አንበሳም ደቦሉን . . .
በጊዜው ካልቀጣ ንግስናው ይቀማል ፤
የልጅነት ሥሥት ፣
የአባትነት ድርሻ ለክብር ይወድማል ።
አዎ !
እናት ክብሯን ይዛ ፣
ልጅ ግብሩን ተላብሶ ፣
አባት በስም ነግሦ ፣
ካልተነፃፀረ ፤
የመዳን ምሳሌው ትንቢቱ ተሻረ ።
#የሞት ጥቁር ወተት
#ተስፋሁን ከበደ
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
#ኅብር ሕይወቴ
ስነ ጽሑፍ በፊደላት አበቦች ያማረ እጅግ ሠፊና ጥልቅ ፍጥረተ ዓለም ነው! አይሞላም። ፀሐዩ መጽሐፍ ነው። አማልክቱ ደራሲያኑ ናቸው። ፍጥረታቱ ደግሞ ተደራሲያን። እንደየዕምነታቸው ያድሩበታል። ባመኑት ልክ ያገኛሉ። የሰናፍጭ ቅንጣት ያህል በመጽሐፍ ያመኑ ይድናሉ የሚሉ ሰባኪያንም በዚያ ስፍራ አሉ።
ደራሲ ጋሽ ዘነበ ወላ አንዱ የመጽሐፍ ቄስ ነው። ከዕለታት በአንዱ ቀን 'ከፀሐይ በታች' በተሰኘ ጉባኤው ላይ ስለ ስነ ጽሑፍ ሲያስተምር ሰምቼዋለሁ። ከአትሮኑሱ ላይ የተናገረውን ላጋራችሁ።
#ዓለም እንዲህም ናት ለካ
"ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ (ከጉሬዛ ማርያም እስከ አዲስ አበባ) የመጀመርያ ፍላጎቱ ሽፍታ መሆን ነበር። ትምህርት ቤት ሳለ ግን የታላላቅ ደራሲዎችን የስነ ጽሑፍ ሥራ ማለትም የነ ቻርለስ ዲከንስን፣ የነ ቶልስቶይን፣ የነ ዶስቶቭስኪ የመሣሠሉ መጻሕፍትን አነበበ።
'አሃ ዓለም እንዲህም ናት ለካ!' ብሎ የሽፍትነት ሃሳቡን ቀየረ። ይኸው ዛሬ ላይ ታላቅ ለሀገርና ለዓለም የሚበቃ ምሁር ሆነ።"
#440 ምን አላት?!
የመጽሐፍ ትርፍ ከተገዛበት አንጻር እልል በቅምጤ የሚያሰኝ ኪሳራ የለሽ ቅዱስ ንግድ ነው። ይህንን ከላይ ያለ ማባበያ የጻፍኩት ትናንት ማምሻዬን ሳልገዛ አላድርም ያልኩት የባሕሩ ዘውዴ (ፕ/ር) የ'ኅብር ሕይወቴ' የመጽሐፍ ጉዳይ ነው። ዋጋው ብር 440 ነው። በአጋጣሚ የያዝኩት ገንዘብ ብር አምስት መቶ ብቻ ነበር።
ትራንስፖርት ስይዝ ነው የታወቀኝ... ያለ(ው) የመሠለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ። የ50 ብር የምሽት መንገዴን በሰቀቀን ጨርሼ ቤት ገባሁ።
ኪሴ ጸጥ ያለበት የትናንቱ ምሽት ዛሬ ማለዳ ላይ ይህቺን የመጽናኛ ሐሳብ ወልዶ አደረ።
ቢሆንም ቢሆንም ጋሽ ዘኔ እንዳለው "ንባብ ውስጣችን ያለውን ዓመጽ ያረግባል። ንባብ ተሰጥኦችንን ያስገኛል። ለተስፋችንም ማረፊያ ነው። የእንባችን ማበሻ፣ የብስጭታችን ማረፊያ ነው። የተራበ ሳቅም በመጽሐፍ ገጽ ውስጥ ካለው ማሳ ይመላለስ። እነሆ መከፋትን ይተዋል፤ እርሱም ሃሴትን ይጠግባል።"
©ከ "ሆሄ"
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ስነ ጽሑፍ በፊደላት አበቦች ያማረ እጅግ ሠፊና ጥልቅ ፍጥረተ ዓለም ነው! አይሞላም። ፀሐዩ መጽሐፍ ነው። አማልክቱ ደራሲያኑ ናቸው። ፍጥረታቱ ደግሞ ተደራሲያን። እንደየዕምነታቸው ያድሩበታል። ባመኑት ልክ ያገኛሉ። የሰናፍጭ ቅንጣት ያህል በመጽሐፍ ያመኑ ይድናሉ የሚሉ ሰባኪያንም በዚያ ስፍራ አሉ።
ደራሲ ጋሽ ዘነበ ወላ አንዱ የመጽሐፍ ቄስ ነው። ከዕለታት በአንዱ ቀን 'ከፀሐይ በታች' በተሰኘ ጉባኤው ላይ ስለ ስነ ጽሑፍ ሲያስተምር ሰምቼዋለሁ። ከአትሮኑሱ ላይ የተናገረውን ላጋራችሁ።
#ዓለም እንዲህም ናት ለካ
"ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ (ከጉሬዛ ማርያም እስከ አዲስ አበባ) የመጀመርያ ፍላጎቱ ሽፍታ መሆን ነበር። ትምህርት ቤት ሳለ ግን የታላላቅ ደራሲዎችን የስነ ጽሑፍ ሥራ ማለትም የነ ቻርለስ ዲከንስን፣ የነ ቶልስቶይን፣ የነ ዶስቶቭስኪ የመሣሠሉ መጻሕፍትን አነበበ።
'አሃ ዓለም እንዲህም ናት ለካ!' ብሎ የሽፍትነት ሃሳቡን ቀየረ። ይኸው ዛሬ ላይ ታላቅ ለሀገርና ለዓለም የሚበቃ ምሁር ሆነ።"
#440 ምን አላት?!
የመጽሐፍ ትርፍ ከተገዛበት አንጻር እልል በቅምጤ የሚያሰኝ ኪሳራ የለሽ ቅዱስ ንግድ ነው። ይህንን ከላይ ያለ ማባበያ የጻፍኩት ትናንት ማምሻዬን ሳልገዛ አላድርም ያልኩት የባሕሩ ዘውዴ (ፕ/ር) የ'ኅብር ሕይወቴ' የመጽሐፍ ጉዳይ ነው። ዋጋው ብር 440 ነው። በአጋጣሚ የያዝኩት ገንዘብ ብር አምስት መቶ ብቻ ነበር።
ትራንስፖርት ስይዝ ነው የታወቀኝ... ያለ(ው) የመሠለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ። የ50 ብር የምሽት መንገዴን በሰቀቀን ጨርሼ ቤት ገባሁ።
ኪሴ ጸጥ ያለበት የትናንቱ ምሽት ዛሬ ማለዳ ላይ ይህቺን የመጽናኛ ሐሳብ ወልዶ አደረ።
ቢሆንም ቢሆንም ጋሽ ዘኔ እንዳለው "ንባብ ውስጣችን ያለውን ዓመጽ ያረግባል። ንባብ ተሰጥኦችንን ያስገኛል። ለተስፋችንም ማረፊያ ነው። የእንባችን ማበሻ፣ የብስጭታችን ማረፊያ ነው። የተራበ ሳቅም በመጽሐፍ ገጽ ውስጥ ካለው ማሳ ይመላለስ። እነሆ መከፋትን ይተዋል፤ እርሱም ሃሴትን ይጠግባል።"
©ከ "ሆሄ"
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
👍1
🔅ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?
(በሌቭ ቶልስቶይ)
ከረዥም ዘመን በፊት በአንድ ትንሽ የደቡብ ኤዥያ አገር የሚኖሩ ብልህ ንጉሥ ነበሩ። ግዛታቸውን ለመገንጠል የተነሳ አንድ የውስጥ ወንበዴ ቡድን አስቸግሯቸው ስለነበር በጦርነት ሊያጠፏቸው ወሰኑ፤
ለጦር አዛዡም ይህን ጦርነት በድል ፈፅሞ ከተመለሰ ከፍተኛ የሆነ ሀብትና መሬት እንደሚሰጡት ቃል ገቡለት። በዚህም የተነሳ የንጉሡ ጦር በከፍተኛ ቆራጥነት ተዋግቶ የወንበዴው ጦር ተደመሰሰ። የሞተው ሞቶ የቀረው ቆስሎም ተማረከ፤
ንጉሡ ቃል እንደገቡት ለጦር አዛዡ ብዙ ሀብት ከመደቡለት በኋላ "በእግሩ ቀኑን ሙሉ ፀሀይ እስክትጠልቅ የሄደበትን የግዛቴን መሬት ለክታችሁ ስጡት።" ብለው ሸለሙት።
የጦር አዛዡም ተደሰተ፤ ብዙ ለም የሆነ መሬት መያዝ ይፈልግ ስለነበር በተዘጋጀበት ቀን በጣም በማለዳ ተነስቶ ስንቅ አዘጋጅቶ መጓዝ ጀመረ። በመጀመሪያ ጉልበቱ የቻለውን ያህል በለሙ መሬት ላይ ሮጠ። መሬት ለኪዎችም በፈረስ ይከተሉት ነበር፤
ከዚያም በፍጥነት ቀኑ ሳይመሽ ይራመድ ጀመር። ብዙ ከሄደ በኋላ ወደ ከሰአት ምሳውን ሳይቀር እየሄደ በላ።
ሆኖም ከበላ በኋላ ጥቂት መሬት ሄዶ ስለደከመው እየተራመደ ውሃ ጠጣ። ዘጠኝ ሰአት ያለእረፍት ተጉዞ በመጨረሻ እገሩ በጣም ዛለ፤
ቢሆንም አንድም እርምጃ ቢሆን ለም መሬት ነውና መራመዱን ቀጠለ። ሲል ሲል እግሩ መራመድ አቅቶት ዝሎ ወደቀ።
አሁን ለኪዎቹ ምልክት ሊያደርጉ ሲሉ "ቆዩ ... ቆዩ" ብሎ መዳኽ ጀመረ። ከዚያም ጥቂት ሄዶ በልቡም መሳብ ጀመረ፤
በመጨረሻ ፀሃይ ገና ሳትጠልቅ የቻለውን ተንጠራርቶ ሲሳብ ልቡ ቀጥ አለችና ትንፋሹ ቆሞ ሞተ። የንጉሡ ቦታ ለኪዎችም ደነገጡ።
የጦር አዛዡን ከሞተበት ሳያነሱ በፈረስ መልእክተኛ ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ላኩ፤
መልክተኞቹም የአዛዡን ሲጓዝ ውሎ ልቡ ደክሞ መሞቱን ነግረው "ምን ያህል መሬት እንስጠው?" ብለው ጠየቁ። ንጉሡም እጅግ አዝነው "ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?" ብለው ተከዙ፤
"እንግዲህ ይህ ሰው የወደቀበትን ቦታ ብቻ ከእግሩ ጫፍ እስከ ራሱ ጫፍ ብቻ ለክታችሁ ስጡት። ሬሳውንም እዚያው ቦታ ቆፍራችሁ በክብር ቅበሩትና የጀግና ሃውልት አቁሙለት።" አሏቸው፤
በተባለው መሰረት የጦር አዛዡ በመጨረሻ በሞተባት ቦታ በክብር ተቀበረ። በመቃብሩም ሀውልት ላይ
"ለሰው የሚበቃው መሬት ይህ ነው።" ተብሎ ተፃፈ።
#share and join for more👍
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
(በሌቭ ቶልስቶይ)
ከረዥም ዘመን በፊት በአንድ ትንሽ የደቡብ ኤዥያ አገር የሚኖሩ ብልህ ንጉሥ ነበሩ። ግዛታቸውን ለመገንጠል የተነሳ አንድ የውስጥ ወንበዴ ቡድን አስቸግሯቸው ስለነበር በጦርነት ሊያጠፏቸው ወሰኑ፤
ለጦር አዛዡም ይህን ጦርነት በድል ፈፅሞ ከተመለሰ ከፍተኛ የሆነ ሀብትና መሬት እንደሚሰጡት ቃል ገቡለት። በዚህም የተነሳ የንጉሡ ጦር በከፍተኛ ቆራጥነት ተዋግቶ የወንበዴው ጦር ተደመሰሰ። የሞተው ሞቶ የቀረው ቆስሎም ተማረከ፤
ንጉሡ ቃል እንደገቡት ለጦር አዛዡ ብዙ ሀብት ከመደቡለት በኋላ "በእግሩ ቀኑን ሙሉ ፀሀይ እስክትጠልቅ የሄደበትን የግዛቴን መሬት ለክታችሁ ስጡት።" ብለው ሸለሙት።
የጦር አዛዡም ተደሰተ፤ ብዙ ለም የሆነ መሬት መያዝ ይፈልግ ስለነበር በተዘጋጀበት ቀን በጣም በማለዳ ተነስቶ ስንቅ አዘጋጅቶ መጓዝ ጀመረ። በመጀመሪያ ጉልበቱ የቻለውን ያህል በለሙ መሬት ላይ ሮጠ። መሬት ለኪዎችም በፈረስ ይከተሉት ነበር፤
ከዚያም በፍጥነት ቀኑ ሳይመሽ ይራመድ ጀመር። ብዙ ከሄደ በኋላ ወደ ከሰአት ምሳውን ሳይቀር እየሄደ በላ።
ሆኖም ከበላ በኋላ ጥቂት መሬት ሄዶ ስለደከመው እየተራመደ ውሃ ጠጣ። ዘጠኝ ሰአት ያለእረፍት ተጉዞ በመጨረሻ እገሩ በጣም ዛለ፤
ቢሆንም አንድም እርምጃ ቢሆን ለም መሬት ነውና መራመዱን ቀጠለ። ሲል ሲል እግሩ መራመድ አቅቶት ዝሎ ወደቀ።
አሁን ለኪዎቹ ምልክት ሊያደርጉ ሲሉ "ቆዩ ... ቆዩ" ብሎ መዳኽ ጀመረ። ከዚያም ጥቂት ሄዶ በልቡም መሳብ ጀመረ፤
በመጨረሻ ፀሃይ ገና ሳትጠልቅ የቻለውን ተንጠራርቶ ሲሳብ ልቡ ቀጥ አለችና ትንፋሹ ቆሞ ሞተ። የንጉሡ ቦታ ለኪዎችም ደነገጡ።
የጦር አዛዡን ከሞተበት ሳያነሱ በፈረስ መልእክተኛ ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ላኩ፤
መልክተኞቹም የአዛዡን ሲጓዝ ውሎ ልቡ ደክሞ መሞቱን ነግረው "ምን ያህል መሬት እንስጠው?" ብለው ጠየቁ። ንጉሡም እጅግ አዝነው "ለሰው ምን ያህል መሬት ይበቃዋል?" ብለው ተከዙ፤
"እንግዲህ ይህ ሰው የወደቀበትን ቦታ ብቻ ከእግሩ ጫፍ እስከ ራሱ ጫፍ ብቻ ለክታችሁ ስጡት። ሬሳውንም እዚያው ቦታ ቆፍራችሁ በክብር ቅበሩትና የጀግና ሃውልት አቁሙለት።" አሏቸው፤
በተባለው መሰረት የጦር አዛዡ በመጨረሻ በሞተባት ቦታ በክብር ተቀበረ። በመቃብሩም ሀውልት ላይ
"ለሰው የሚበቃው መሬት ይህ ነው።" ተብሎ ተፃፈ።
#share and join for more👍
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
❤1👍1
ኬቨን ሃርት የተባለው ኮሜዲያን። እዚህ የስኬት ጫፍ ላይ ከመድረሱ በፊት ብዙ መከራ ያሳለፈና አትችልም ተብሎ የተገፋ ሰው ሲሆን፣ ከሲንግል እናቱ ቤት ሥራ ፍለጋ ሲወጣ እናቱ የሰጡት ስጦታ መጽሐፍ ቅዱስ ነበር። ኬቨን አንድ ቀን የሚመገበው አጥቶ በጣም ቸግሮት ለእናቱ ይደውላል፣ ማሚ ስራ ማግኘት አልቻልኩም እባክሽ እርጂኝ አላቸው? እናቱም የሰጠሁህን መጽሐፍ ቅዱስ አንበብክ ወይ ? እርሱም ራበኝ እያልኩሽ የምን መጻሕፍ ነው የምትይው አላቸው። ልጄ አሉት የሰጠሁህን መጻሕፍ ቅዱስን አንብበህ ቢሆን ኖሮ እኮ አይርብህም ነበር አሉት።
ኬቨን እናቱ አንብብ ያሉትን መጻሕፍ ቅዱስ ሳያነብ እናቱ በማኅፀን በር ካንሰር ያርፋሉ፣ እርሱም በዓለም ምርጡ ኮሜዲያን ውዱ አከተርም ከሆነ በኃላ፣ አንድ ቀን የልጅነት ፎቶግራፎቹን ለፊልም ፈልጎ ሲበረብር ያንን እናቱ የሰጡትን መጻሕፍ ቅዱስንም ገለጠው፣ ውስጡ እናቱ ለስራ መፈለጊያና መጠነኛ ቤት መከራያ እንዲሆነው የተውለትን 1ሺ ዶላር አገኘ። ገንዘቡ ለአሁኑ ኬቨን ምንም ብትሆንም እናቱ ግን ንብረታቸውን ሸጠው ነበር ለልጃቸው የሰጡት። መጻሕፍት ውስጥ ብዙ መልሶች አሉና መጻሕፍትን እናንብብ። ቀና ብሎ በዕውቀት ለማውራት ብዙ አጎንብሶ ማንበብን ይጠይቃል።
ፍፁም አብርሃም✍️✍️
#share and join for more👍
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ኬቨን እናቱ አንብብ ያሉትን መጻሕፍ ቅዱስ ሳያነብ እናቱ በማኅፀን በር ካንሰር ያርፋሉ፣ እርሱም በዓለም ምርጡ ኮሜዲያን ውዱ አከተርም ከሆነ በኃላ፣ አንድ ቀን የልጅነት ፎቶግራፎቹን ለፊልም ፈልጎ ሲበረብር ያንን እናቱ የሰጡትን መጻሕፍ ቅዱስንም ገለጠው፣ ውስጡ እናቱ ለስራ መፈለጊያና መጠነኛ ቤት መከራያ እንዲሆነው የተውለትን 1ሺ ዶላር አገኘ። ገንዘቡ ለአሁኑ ኬቨን ምንም ብትሆንም እናቱ ግን ንብረታቸውን ሸጠው ነበር ለልጃቸው የሰጡት። መጻሕፍት ውስጥ ብዙ መልሶች አሉና መጻሕፍትን እናንብብ። ቀና ብሎ በዕውቀት ለማውራት ብዙ አጎንብሶ ማንበብን ይጠይቃል።
ፍፁም አብርሃም✍️✍️
#share and join for more👍
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
👏1
''እናትዬ''
''ወዬ አባትዬ''
''አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር። መጀመሪያ ግን እንደማትናደጅብኝ ቃል ግብልኝ''
''የሚያናድድ ነው ምጠይቀኝ?''
(ከደረቱ ላይ ቀና ብላ እያዬችው ጠየቀች)
''እ አ..ይ...አዎ! ማለቴ ይሄ ጥያቄ አንቺን ያናድድሻል ብዬ ነው ማሬ''
(ጭንቅ ብሎታል ምን ብሎ እንደምጀምርላት ግራ ገብቶታል። በጭራሽ የማትወደው ጥያቄ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። ግን ደሞ መልስ ካላገኘለት በጭራሽ እንቅልፍ አይወስደውም። መወሰን አቃተው።)
(ንግግሩ አሳቃት እና ሳቅ ብላ።)
''ደሞ ምን ማለት ነው ይሄ!? አይ! አዎ! አንዱን ምረጥ አባትዬ። እሺ በቃ ጠይቀኝ ፈቅጀልሃለው። መቼም አንዴ አንተን ጥሎብኛል አቃጥላት ብሎ ሃሃ. . . ጠይቀኝና ካናደደኝ ልናደዳ እንግዲህ።''
(አለችው እየቀለደችበትና እየሳቀች አይን አይኑን በፈገግታ እያየች)
''ግን ይሄን ጠየኩሽ ማለት እኔ አላምንሽም ማለት አይደለም እሺ?''
(አላት በልምምጥ። የነገሩ አካሄድ የገባት እሷ ደረቱ ላይ ተደግፋ ከተቀመጠችበት ቀና ብላ ተቀመጠች። ልታስጨርሰው ስለፈለገች ዝም ብላ መስማቱን ቀጠለች። ፈራት። አንዴ ጀምሮታል ያለው አማራጭ መቀጠል ብቻ ነው። ባለፈው እንደዚህ ባለ ተመሳሳይ ጉዳይ የመለያየት ጫፍ ላይ ደርሰው እንደተመለሱ ያውቃል። በጭራሽ ሊያጣት አይፈልግም። በጣም ይወዳታል። እንደዚህ ያለ ነገር ውስጥም የሚገባው እሷን ላለማጣት ካለው ፍራቻ የተነሳ ነው።)
''ይሄውልሽ ምን መሰለሽ ከያሬድ ጋ ያላቹህ ቀረበታ ብዙም ምቾት አይሰጠኝም። ባለፈው ብሮሽ ሄጄ ሳለሁ ፡ ምን አይነት አስተያየት ስያይሽ እንደ ነበር ማስተዋል ችያለሁ። ደሞ አስር ጊዜ ነው ወደ ብሮው የምጠራሽ። በዚህ ላይ ደሞ ቁልምጫው. . .''
(እያለ ሊቀጥል ሲል አቋረጠችው። በወሬው ላለመበሳጨት ጥረት እያረገች)
''እንደ አባትዬ እንዴት እንደዚህ ታስባለህ? እሱ እኮ አለቃዬ ነው። በማንኛውም ሰዓት ለስራ ወደ ብሮው ሊጠራኝ ይችላል። ሰውዬው ለራሱ ባለትዳር ነው። በጣም የምወዳት ሚስት አለችው። እና ደሞ እኔን ብቻ አይደለም በቁልምጫ የሚጠራኝ። ይመስለኛል እንደልምድ ሆኖበታል። ሙሉ እስታፍ ውስጥ ያሉ ሰራተኞችን እንደዛ ነው የምጠራው። ሰውየው እንዴትም ሊያዬኝ አይችልም ይሄ በአእምሮህ እየፈጠርክ የምታስበው ነገር ነው። ዋ! እንዳትጀምረኝ ደሞ''
(ነገሩን ቀለል ለማድረግ እየሞከረች ሳቅ ብላ)
''ምን ማለት ነው በአእምሮህ እየፈጠርክ ነው ምታስበው ማለት!? ያላየሁትን ነገር እንዴት ፈጥሬ ላስብና ላወራ እችላለሁ? አንቺ ራሱ ሆን ብለሽ እንዳልገባሽ ለመምሰል ካልጣርሽ በስተቀር ፡ ማየት ለሚፈልግ ሰው ፡ ግልፅ የሆነ የሽፍደት አስተያየት ነው የሚያይሽ።''
(ሳያውቀው በጣም ስሜታዊ ሆኖ ስለነበር ፡ በኃይሌ ቃል የነበር የሚያወራት። ቃላት መምረጡን እረሳ። እሷም ፊቷ እየተቀየረ ነው። ብስጭቷ ሳትፈልገው እየገነፈለ ይመጣል። እንደምንም ልትቆጣጠረው እየሞከረች።)
''ሽፍደት? ምን ማለት ይሆን ደሞ ይሄ? ደሞ መስሎህ ነው እንጂ : እኔ ሆን ብዬ እንዳልገባኝ እያስመሰልኩ አይደለም። ይልቅስ ምንም ያላሰበውን ሰውዬ እየፈረድክበት እንደሆነ ሊገባህ የሚገባው አንተ ነህ። አዬህ አይደል ለዚህ ነው አታምነኝም የሚልህ።''
''እና ይሄ አንቺን ካለማመን ጋር ምን ያገናኘዋል? የሃለቃሽ አስተያየት ደስ አላለኝም ማለት። አንቺን አላምንሽም ማለት አይደለም።''
''ነው እንጂ። በደንብ ነው። ብታምነኝማ ኖሮ መቼ ሁልጊዜ እንዲህ ያለ አተካራ ውስጥ እንገባ ነበር። ብታምነኝማ ሺህ ጊዜ የሃለቃዬ አስተያዬት ደስ ባይልህ : በእኔ ከተማመንክ ምንም ባላስፈራህ ነበር። ለምን እንደዚህ ታረገኛለህ ግን? እንደ ማፈቅርህ ታውቃለህ። አማራጭ አጥቼ አንተን እንዳልመረጥኩህም ጠንቅቀህ ታውቃለህ። ልምረጥ ቢል ብዙ ሰዎች በዙሪያዬ እንደነበሩ ታውቃለህ አይደል?''
(አሁን አኮረፈች)
''አዎ አውቃለሁ የኔ እናት እሺ በቃ ትቸዋለሁ። አሁን አታኩርፊ'' (እጇን ይዞ በእጆቹ እያሻሼ አባበላት)
''እና እንዲህ ያለ ሁኔታ ውስጥ እንድሆን ለምን ታደርጋለህ!? አላሳዝንህም? አንተ እኔን እንድታምነኝ ፡ ያላረኩት ምን አለ? እስኪ ንገረኝ ምንድነው ያላረኩት!? በእናትህ ዳጊ እንደዚህ አታድርገኝ በእናትህ ልለምንህ''
(አሁንም እንዳኮረፈች ሳግ በሚተናነቀው ድምፅ።)
''እናትዬ እውነተን ነው ሚልሽ። በፍቅራችን እምልልሻለሁ ፡ ከራሴ በላይ ነው የማምንሽ።''
''እና ካመንከኝ ለምን ትጠራጠራለህ? እኔን ብታምነኝ ይሄ ሁሉ ነገር ባልተፈጠረ ነበር። ባንተ ምክንያት ብቻ በጣም የተሻሉ ስራዎቼን ትቻለሁ። በጣም መልካም የሆኑ የሴትም ሆነ የወንድም ጓደኞቼን ርቂያለሁ። አንተ ስለማትፈልግ ብቻ ማድረግ እየፈለኩ ማላደርጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ። ህልሜን : የምወደውን ስራ : ቤተሰቤን ሳይቀር ላንተ ሲል ትቻለሁ። ታውቃለህ!? የሚኖረው ህይወት መኖር የምፈልገውንና እኖራለሁ ብዬ ስመኝ የኖርኩትን ህይወት አይደለም። መኖር ያለብኝን ህይወት ሁሉ ፍቅራችን ይበልጣል ብዬ ተውኩ። ሳገባህ ከተሻለህ ብዬ አገባሁሁ። ግን አንተ ጭራሽ ባሰብህ። ስራ ቦታዬ ድረስ እየድክ ሰላም ትነሳኛለህ። ለራስህም ሰላም ታጣለህ። በቅናት ምክንያት እኔን ከነ መፈጠሬ እረስተህ ገና ለገና አስተያየቱ አላማረኝም ብለህ ከመንገደኛ ጋር ሁሉ ሳይቀር ፀብ ውስጥ ትገባለህ። ከሰው ጋር ተቀምጠን ስንጫወት ነገሩን በሌላ ተርጉመህ ጥል ውስጥ ስለምትገባ : ካሁን አሁን እንድህ ይፈጠራል እያልኩ ነፍሴን አስጨንቃታለሁ። ሰውነቴ በሰቀቀን ያልቃል። ትላንት በመጣሁበት መንገድ ታክሲ ሳይቀናኝ ቀርቶ መንገድ ቀይሬ በቀናኝ በኩል ቢመጣ : ደሞ በዛ በኩል ምን ተገኘ ትለኛለህ። ከማን ጋር ነው የመጣሽው? ታክሲ ውስጥ አብሮሽ የተቀመጠው ወንድ ነው አይደል? ሆንብለሽ ነው ከወንድ ጋ የተቀመጥሽው ትለኛለህ። አሁንስ እኔ ድክም ስልችት ነው ያለኝ።''
''በነገሩ ስትንገሸገሽ አይቶ ደነገጠ። ግን አሁንም ብሆን የመቀጠል እንጂ ነገሩን የማብረድ አላማ ያለው አይመስልም።''
''እናትዬ አሁን ምትይኝን ነገር ሁሉ የማደርገው እኮ ለፍቅራችን ብዬ ነው።''
''ለፍቅራችን ብዬ!? ምን ማለት ነው ለፍቅራችን ብዬ? እኮ እንዴት ሆኖ ነው እንደዚህ ያለ አቅል የሚያስት ቅናት ለፍቅራችን የሚጠቅም የመሰለህ? ይሄውል ብገባህ ቅናትህ ቀን በቀን ፍቅራችንን እየገደለው ነው''
''ይሄ በጭራሽ ቅናት አይደለም።''
''እሺ ባክህ እና ምንድነው!? ባልዋልኩበት : ባልነበርኩበት እያነበርከኝ : ባልተኛሁበት እያስተኛኸኝ : ባልሄድኩበት : ባልተቀመጥኩበት እያስቀመጥከኝ : ያልተፈጠረ ነገር ፈጥረህ እያወራህ : ጭራሽ እያበድክ እስክመስለኝ ድረስ : ሁሉንም ሰው በጥርጣሬ ዓይን እያየህ። እና ይሄ ቅናት ካልተባለ ምን አይነት ስም ልትሰጠው ነው? ይሄ ለኔ ከቅናትም በላይ ነው። ይሄ በሽታ ነው። የለየለት እብደትም ጭምር ነው የሚመስለኝ''
(ብላ ከአጠገቡ ተነስታ ሌላ ቦታ ቁጭ አለች)
''ኧረ ባክሽ እና አብደሀል እያልሽኝ ነው? እብድም መሰልኩሽ!? ታዲያ ለምን ፀበል አትወስጅኝም እ? እንደሱ አይሻልሽም?''
(አላት በንዴት ጦፎ ነገሮች ወደጭቅጭቅ መቀየራቸውም ንግግሯም ከጎኑ ተነስታ ቦታ ቀይራ መቀመጧም አበሳጨው።)
''ወዬ አባትዬ''
''አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር። መጀመሪያ ግን እንደማትናደጅብኝ ቃል ግብልኝ''
''የሚያናድድ ነው ምጠይቀኝ?''
(ከደረቱ ላይ ቀና ብላ እያዬችው ጠየቀች)
''እ አ..ይ...አዎ! ማለቴ ይሄ ጥያቄ አንቺን ያናድድሻል ብዬ ነው ማሬ''
(ጭንቅ ብሎታል ምን ብሎ እንደምጀምርላት ግራ ገብቶታል። በጭራሽ የማትወደው ጥያቄ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። ግን ደሞ መልስ ካላገኘለት በጭራሽ እንቅልፍ አይወስደውም። መወሰን አቃተው።)
(ንግግሩ አሳቃት እና ሳቅ ብላ።)
''ደሞ ምን ማለት ነው ይሄ!? አይ! አዎ! አንዱን ምረጥ አባትዬ። እሺ በቃ ጠይቀኝ ፈቅጀልሃለው። መቼም አንዴ አንተን ጥሎብኛል አቃጥላት ብሎ ሃሃ. . . ጠይቀኝና ካናደደኝ ልናደዳ እንግዲህ።''
(አለችው እየቀለደችበትና እየሳቀች አይን አይኑን በፈገግታ እያየች)
''ግን ይሄን ጠየኩሽ ማለት እኔ አላምንሽም ማለት አይደለም እሺ?''
(አላት በልምምጥ። የነገሩ አካሄድ የገባት እሷ ደረቱ ላይ ተደግፋ ከተቀመጠችበት ቀና ብላ ተቀመጠች። ልታስጨርሰው ስለፈለገች ዝም ብላ መስማቱን ቀጠለች። ፈራት። አንዴ ጀምሮታል ያለው አማራጭ መቀጠል ብቻ ነው። ባለፈው እንደዚህ ባለ ተመሳሳይ ጉዳይ የመለያየት ጫፍ ላይ ደርሰው እንደተመለሱ ያውቃል። በጭራሽ ሊያጣት አይፈልግም። በጣም ይወዳታል። እንደዚህ ያለ ነገር ውስጥም የሚገባው እሷን ላለማጣት ካለው ፍራቻ የተነሳ ነው።)
''ይሄውልሽ ምን መሰለሽ ከያሬድ ጋ ያላቹህ ቀረበታ ብዙም ምቾት አይሰጠኝም። ባለፈው ብሮሽ ሄጄ ሳለሁ ፡ ምን አይነት አስተያየት ስያይሽ እንደ ነበር ማስተዋል ችያለሁ። ደሞ አስር ጊዜ ነው ወደ ብሮው የምጠራሽ። በዚህ ላይ ደሞ ቁልምጫው. . .''
(እያለ ሊቀጥል ሲል አቋረጠችው። በወሬው ላለመበሳጨት ጥረት እያረገች)
''እንደ አባትዬ እንዴት እንደዚህ ታስባለህ? እሱ እኮ አለቃዬ ነው። በማንኛውም ሰዓት ለስራ ወደ ብሮው ሊጠራኝ ይችላል። ሰውዬው ለራሱ ባለትዳር ነው። በጣም የምወዳት ሚስት አለችው። እና ደሞ እኔን ብቻ አይደለም በቁልምጫ የሚጠራኝ። ይመስለኛል እንደልምድ ሆኖበታል። ሙሉ እስታፍ ውስጥ ያሉ ሰራተኞችን እንደዛ ነው የምጠራው። ሰውየው እንዴትም ሊያዬኝ አይችልም ይሄ በአእምሮህ እየፈጠርክ የምታስበው ነገር ነው። ዋ! እንዳትጀምረኝ ደሞ''
(ነገሩን ቀለል ለማድረግ እየሞከረች ሳቅ ብላ)
''ምን ማለት ነው በአእምሮህ እየፈጠርክ ነው ምታስበው ማለት!? ያላየሁትን ነገር እንዴት ፈጥሬ ላስብና ላወራ እችላለሁ? አንቺ ራሱ ሆን ብለሽ እንዳልገባሽ ለመምሰል ካልጣርሽ በስተቀር ፡ ማየት ለሚፈልግ ሰው ፡ ግልፅ የሆነ የሽፍደት አስተያየት ነው የሚያይሽ።''
(ሳያውቀው በጣም ስሜታዊ ሆኖ ስለነበር ፡ በኃይሌ ቃል የነበር የሚያወራት። ቃላት መምረጡን እረሳ። እሷም ፊቷ እየተቀየረ ነው። ብስጭቷ ሳትፈልገው እየገነፈለ ይመጣል። እንደምንም ልትቆጣጠረው እየሞከረች።)
''ሽፍደት? ምን ማለት ይሆን ደሞ ይሄ? ደሞ መስሎህ ነው እንጂ : እኔ ሆን ብዬ እንዳልገባኝ እያስመሰልኩ አይደለም። ይልቅስ ምንም ያላሰበውን ሰውዬ እየፈረድክበት እንደሆነ ሊገባህ የሚገባው አንተ ነህ። አዬህ አይደል ለዚህ ነው አታምነኝም የሚልህ።''
''እና ይሄ አንቺን ካለማመን ጋር ምን ያገናኘዋል? የሃለቃሽ አስተያየት ደስ አላለኝም ማለት። አንቺን አላምንሽም ማለት አይደለም።''
''ነው እንጂ። በደንብ ነው። ብታምነኝማ ኖሮ መቼ ሁልጊዜ እንዲህ ያለ አተካራ ውስጥ እንገባ ነበር። ብታምነኝማ ሺህ ጊዜ የሃለቃዬ አስተያዬት ደስ ባይልህ : በእኔ ከተማመንክ ምንም ባላስፈራህ ነበር። ለምን እንደዚህ ታረገኛለህ ግን? እንደ ማፈቅርህ ታውቃለህ። አማራጭ አጥቼ አንተን እንዳልመረጥኩህም ጠንቅቀህ ታውቃለህ። ልምረጥ ቢል ብዙ ሰዎች በዙሪያዬ እንደነበሩ ታውቃለህ አይደል?''
(አሁን አኮረፈች)
''አዎ አውቃለሁ የኔ እናት እሺ በቃ ትቸዋለሁ። አሁን አታኩርፊ'' (እጇን ይዞ በእጆቹ እያሻሼ አባበላት)
''እና እንዲህ ያለ ሁኔታ ውስጥ እንድሆን ለምን ታደርጋለህ!? አላሳዝንህም? አንተ እኔን እንድታምነኝ ፡ ያላረኩት ምን አለ? እስኪ ንገረኝ ምንድነው ያላረኩት!? በእናትህ ዳጊ እንደዚህ አታድርገኝ በእናትህ ልለምንህ''
(አሁንም እንዳኮረፈች ሳግ በሚተናነቀው ድምፅ።)
''እናትዬ እውነተን ነው ሚልሽ። በፍቅራችን እምልልሻለሁ ፡ ከራሴ በላይ ነው የማምንሽ።''
''እና ካመንከኝ ለምን ትጠራጠራለህ? እኔን ብታምነኝ ይሄ ሁሉ ነገር ባልተፈጠረ ነበር። ባንተ ምክንያት ብቻ በጣም የተሻሉ ስራዎቼን ትቻለሁ። በጣም መልካም የሆኑ የሴትም ሆነ የወንድም ጓደኞቼን ርቂያለሁ። አንተ ስለማትፈልግ ብቻ ማድረግ እየፈለኩ ማላደርጋቸው ብዙ ነገሮች አሉ። ህልሜን : የምወደውን ስራ : ቤተሰቤን ሳይቀር ላንተ ሲል ትቻለሁ። ታውቃለህ!? የሚኖረው ህይወት መኖር የምፈልገውንና እኖራለሁ ብዬ ስመኝ የኖርኩትን ህይወት አይደለም። መኖር ያለብኝን ህይወት ሁሉ ፍቅራችን ይበልጣል ብዬ ተውኩ። ሳገባህ ከተሻለህ ብዬ አገባሁሁ። ግን አንተ ጭራሽ ባሰብህ። ስራ ቦታዬ ድረስ እየድክ ሰላም ትነሳኛለህ። ለራስህም ሰላም ታጣለህ። በቅናት ምክንያት እኔን ከነ መፈጠሬ እረስተህ ገና ለገና አስተያየቱ አላማረኝም ብለህ ከመንገደኛ ጋር ሁሉ ሳይቀር ፀብ ውስጥ ትገባለህ። ከሰው ጋር ተቀምጠን ስንጫወት ነገሩን በሌላ ተርጉመህ ጥል ውስጥ ስለምትገባ : ካሁን አሁን እንድህ ይፈጠራል እያልኩ ነፍሴን አስጨንቃታለሁ። ሰውነቴ በሰቀቀን ያልቃል። ትላንት በመጣሁበት መንገድ ታክሲ ሳይቀናኝ ቀርቶ መንገድ ቀይሬ በቀናኝ በኩል ቢመጣ : ደሞ በዛ በኩል ምን ተገኘ ትለኛለህ። ከማን ጋር ነው የመጣሽው? ታክሲ ውስጥ አብሮሽ የተቀመጠው ወንድ ነው አይደል? ሆንብለሽ ነው ከወንድ ጋ የተቀመጥሽው ትለኛለህ። አሁንስ እኔ ድክም ስልችት ነው ያለኝ።''
''በነገሩ ስትንገሸገሽ አይቶ ደነገጠ። ግን አሁንም ብሆን የመቀጠል እንጂ ነገሩን የማብረድ አላማ ያለው አይመስልም።''
''እናትዬ አሁን ምትይኝን ነገር ሁሉ የማደርገው እኮ ለፍቅራችን ብዬ ነው።''
''ለፍቅራችን ብዬ!? ምን ማለት ነው ለፍቅራችን ብዬ? እኮ እንዴት ሆኖ ነው እንደዚህ ያለ አቅል የሚያስት ቅናት ለፍቅራችን የሚጠቅም የመሰለህ? ይሄውል ብገባህ ቅናትህ ቀን በቀን ፍቅራችንን እየገደለው ነው''
''ይሄ በጭራሽ ቅናት አይደለም።''
''እሺ ባክህ እና ምንድነው!? ባልዋልኩበት : ባልነበርኩበት እያነበርከኝ : ባልተኛሁበት እያስተኛኸኝ : ባልሄድኩበት : ባልተቀመጥኩበት እያስቀመጥከኝ : ያልተፈጠረ ነገር ፈጥረህ እያወራህ : ጭራሽ እያበድክ እስክመስለኝ ድረስ : ሁሉንም ሰው በጥርጣሬ ዓይን እያየህ። እና ይሄ ቅናት ካልተባለ ምን አይነት ስም ልትሰጠው ነው? ይሄ ለኔ ከቅናትም በላይ ነው። ይሄ በሽታ ነው። የለየለት እብደትም ጭምር ነው የሚመስለኝ''
(ብላ ከአጠገቡ ተነስታ ሌላ ቦታ ቁጭ አለች)
''ኧረ ባክሽ እና አብደሀል እያልሽኝ ነው? እብድም መሰልኩሽ!? ታዲያ ለምን ፀበል አትወስጅኝም እ? እንደሱ አይሻልሽም?''
(አላት በንዴት ጦፎ ነገሮች ወደጭቅጭቅ መቀየራቸውም ንግግሯም ከጎኑ ተነስታ ቦታ ቀይራ መቀመጧም አበሳጨው።)
''ተው ግን ዳጊ ተው ትዕግስተን እየጨረስኩ እንደሆነ ለምን አይታይህም ግን።''
(አሁን እንባዋ መውረድ ጀመረ። እንዲህ ስትለው ይፈራል። ነፍሱ ትሸበራለች። ደንግጦ ከተቀመጠበት ተነስቶ የተቀመጠችበት ሄዶ አቅፎ ሊያባብላት ስሞክር : እንዳያቅፋት ተከላከለች። ታግሎ አቀፋት። ትወደዋለች መጨከን አትችልም ተሸነፈችለት።)
(ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ እየገነፈለ ያስቸገረውን ንዴቱን ለመቆጣጠር ብሞክርም አልቻለምና ይሄው እንደለመደው አስለቀሳት። ሳያስበው በልምምጥ የጀመረው ወሬ ቅርፁን እየቀየረ እየቀየረ ሄዶ ምልልሳቸው ወደ ጭቅጭቅ ተቀየረ። የእሱም ልምምጥ በቁጣ ተተካ። ላይ ላዩን እንደዚህ እየተቆጣ ቢያወራም ፡ ውስጡን ግን አንዳች የፍርሀት ስሜት ሰቅዞ ይዞታል። ቢትሄድብኝስ : እንደ ባለፈው : በቃ የኔና ያንተ ነገር አብቅቷል ቢትለኝስ!? የሚል ሃሳብ አእምሮው ላይ ስመጣ ፈራ። አጥብቆ አቀፋት። ልቡ ይታወክ ጀመር። ጨነቀው። ምድር ላይ የሚያስፈራህ ነገር ምንድነው? ተብሎ ቢጠየቅ ሁለት ጊዜ ሳያስብ ማርቲን ማጣት ነው ብሎ ይመልሳል። ግን ደሞ ሁልጊዜ ነገሮችን የሚያበላሸው ራሱ ነው። በዚህ ምክንያት አንድ ቀን ጥላው እንደምትሄድ ያውቃል።
የሆነ ቀን በዚሁ ጉዳይ ተጣልተው ብዙ ብዙ ተጨቃጭቀው : እቤት ተቀምጣ ምርር ብላ ስታለቅስ : እሱ ጭንቅላቱን ይዞ ሶፋው ላይ አጎንብሶ እንደ ተቀመጠ ጓደኛው ድንገት ይመጣል። ምን ሆናችሁ ነው ብለው ፡ ትንሽ ተጋጭተን ነው አለው። ታዲያ የዛን እለት ጓደኛው ሚስቱን አባብሎ ልሸመግላቸው ተቀመጠ። እናም ጓደኛው ነገር ለማለዘብ ብሎ : ለሚስቱ ለሰነዘረላት ጥያቄ እንዲህ ብላ መመለሷ አስደነገጠው። ይሄውልህ አሴ የጎደኛው ስም አሰግድ ነው። ባሏ ስጠራው በሰማችው እሷም አሴ እያለች ነው ምጠራው። ''በህይወቴ ውስጥ ከምንም በላይ ለፍቅራችን ግዴታዬን ተወጥቻለሁ . . . . . ካልሆነ መሄድ እችላለሁ።'' ነበር ያለችው።
ታዲያ ይሄን ስትል ቀዝቃዛ ውሃ የተቸለሰበት ይመስል ከተቀመጠበት ብትት ብሎ ብድግ አለ። እሱ በተራው ማልቀስ ጀመረ። የዛን እለት አሳር ፍዳውን በልቶ ጓደኛው አስታርቋቸው ሄደ። ታዲያ ሁልጊዜም ቢሆን እንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ስገቡ ያንቀን የተናገረችው ነገር በጆሮው እያስተጋባ ያርደዋል። ቢሆንም ግን ክፉ አመል የሆነበት እና መቼ እንደተፀናወተው የማያውቀው አደገኛ ቅናት አለበት ለመዳን ቢታገልም መፈወስ ያልቻለበት ደዌ። ልክ እንደ {ታምራት ደስታ ሙዚቃ ወድጄ አይደለም ምቀናው ጥሎብኝ ነው የኔ ፍቅር} እንደሚለው። እሱ ራሱ ጭንቅ ስለው ከፍቶ የሚሰማው ይሄን ሙዚቃ ነው። በነገሩ ተበሳጭታ አላናግርህ ስትለውና ስታኮርፍ ይሄን ሙዚቃ በምትወድለት ድምፁ ሲያንጎራጉርላት አንጀቷ አይችልም። አቅፋ ትስመውና ማውራት ይጀምራሉ።
ግን አሁን አሁን ይሄን ፍቅር ልታድን እንደማትችል እየገባት መጥቷል። ልጅ በጣም ብትወድም በዚሁ ፍራቻዋ ምክንያት ነው የመውለድ ፍላጎቷን ያዘገየችው። እዚህ ትዳር ውስጥ ልጅ ማምጣት የልጁን ህይወት ማበላሸት ነው ብላ ነው ምታስበው። ምክንያቱም ይሄ ትዳር በፍቺ እንደሚጠናቀቅ ልቧ ያውቀዋል። እናም ከምታፈቅረው ሰው ልጅ መውለድ ፡ ብትፈታው እንኳን ለትዳሯ እና ለፍቅሯ ለከፈለችው መስዋዕትነት ሁሉ መታሰቢያ ነው ብላ ብታስብም ፡ ልጇን ያለአባት ማሳደግ ግን ልክ አይደለም ብላ ታምናለች። ባሏ ሁልጊዜ የእንውለድ ጥያቄ ያነሳል። ግን ለእሱም ቢሆን ቅናት የለብኝም እያለ ብከራከራትም መቅናትህን አቁመህ እኔን በሙሉ ልብህ አምነህ እንደሰው ማህበራዊ ህይወት ኖሮን ጤናማ ህይወት መኖር ስንጀምር ያኔ እወልዳለሁ ትለዋለች። ደሞ ሁልጊዜም ቢሆን ስላም ሆነው ስለችግሮቻቸው ሲያወሩ : ቅናት እንዳለብህ ማመን ካልቻልክ መዳንም አትችልም ትለዋለች። ካልታረምክ አልወልድልህም ማለቷ ለሱም ባህሪውን ለማስተካከል ጉልበት ይሆነዋል ብላ ታስባለች። የባሏን አስቸጋሪ አመል ለማረቅ ብዙ ነገር ታደርጋለች። ይሄን ትዳር ከተወች ምድር ላይ ብቻዋን እንደምትቀር ታውቃች። እሱ እንዳይቀና ለማድረግ ከህይወቷ ያላስወጣችው ሰው የለም ከወንድ ጓደኞቿ ጋር ብጠረጥራትና ብቀና ከሴት ጓደኞቿ ጋር ደሞ ከማን ጋር ልታገናኝሽ ነው እያለ ቁም ስቅሏን ያሳያታል። ከዚህ ሁሉ ብቀርስ ብላ ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ተወችለት። አሁን ግን ትዳርዋን ፡ ፍቅሯን ለማዳን መሞከር እና ማድረግ ያለባትን ሁሉ አድርጋ ጨርሳለች። እሱን ካጣች እንደምትጎዳ እንደምትሰበር ታውቃለች። ከሁሉ በላይ ግን እሱ እሷን ስያጣት የሚሆነውን ነገር ማሰብ ይከብዳታል። በጭራሽ ተጎድቶ ልታየው አትችልም። የሱን ጉዳት የማየት አቅም የላትም። ከራሷ በላይ የሱ ህመም ያማታል። በትዳሯ በኩል ያልተሰማ ብዙ ፀሎት : ያልሰመረ ብዙ ስዕለት አላት። አንዳንዴ አምላኳን እንዲህ ብላ ትጠይቀዋለች። የማያልቅ ፍቅር ሰጥተሄን ስታበቃ : ቅናት ይሉት ስሌት ፍቅራችንን ገዝግዞ ስቆርጠው እያየህ እንዴት ዝም ብለህ ታያለህ!? እንዴት አንድ የማርያም ምህረት ለፍቅራችን አጣህ!?)
✍ሰብለ ወንጌል
#share and join for more👍
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
(አሁን እንባዋ መውረድ ጀመረ። እንዲህ ስትለው ይፈራል። ነፍሱ ትሸበራለች። ደንግጦ ከተቀመጠበት ተነስቶ የተቀመጠችበት ሄዶ አቅፎ ሊያባብላት ስሞክር : እንዳያቅፋት ተከላከለች። ታግሎ አቀፋት። ትወደዋለች መጨከን አትችልም ተሸነፈችለት።)
(ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ እየገነፈለ ያስቸገረውን ንዴቱን ለመቆጣጠር ብሞክርም አልቻለምና ይሄው እንደለመደው አስለቀሳት። ሳያስበው በልምምጥ የጀመረው ወሬ ቅርፁን እየቀየረ እየቀየረ ሄዶ ምልልሳቸው ወደ ጭቅጭቅ ተቀየረ። የእሱም ልምምጥ በቁጣ ተተካ። ላይ ላዩን እንደዚህ እየተቆጣ ቢያወራም ፡ ውስጡን ግን አንዳች የፍርሀት ስሜት ሰቅዞ ይዞታል። ቢትሄድብኝስ : እንደ ባለፈው : በቃ የኔና ያንተ ነገር አብቅቷል ቢትለኝስ!? የሚል ሃሳብ አእምሮው ላይ ስመጣ ፈራ። አጥብቆ አቀፋት። ልቡ ይታወክ ጀመር። ጨነቀው። ምድር ላይ የሚያስፈራህ ነገር ምንድነው? ተብሎ ቢጠየቅ ሁለት ጊዜ ሳያስብ ማርቲን ማጣት ነው ብሎ ይመልሳል። ግን ደሞ ሁልጊዜ ነገሮችን የሚያበላሸው ራሱ ነው። በዚህ ምክንያት አንድ ቀን ጥላው እንደምትሄድ ያውቃል።
የሆነ ቀን በዚሁ ጉዳይ ተጣልተው ብዙ ብዙ ተጨቃጭቀው : እቤት ተቀምጣ ምርር ብላ ስታለቅስ : እሱ ጭንቅላቱን ይዞ ሶፋው ላይ አጎንብሶ እንደ ተቀመጠ ጓደኛው ድንገት ይመጣል። ምን ሆናችሁ ነው ብለው ፡ ትንሽ ተጋጭተን ነው አለው። ታዲያ የዛን እለት ጓደኛው ሚስቱን አባብሎ ልሸመግላቸው ተቀመጠ። እናም ጓደኛው ነገር ለማለዘብ ብሎ : ለሚስቱ ለሰነዘረላት ጥያቄ እንዲህ ብላ መመለሷ አስደነገጠው። ይሄውልህ አሴ የጎደኛው ስም አሰግድ ነው። ባሏ ስጠራው በሰማችው እሷም አሴ እያለች ነው ምጠራው። ''በህይወቴ ውስጥ ከምንም በላይ ለፍቅራችን ግዴታዬን ተወጥቻለሁ . . . . . ካልሆነ መሄድ እችላለሁ።'' ነበር ያለችው።
ታዲያ ይሄን ስትል ቀዝቃዛ ውሃ የተቸለሰበት ይመስል ከተቀመጠበት ብትት ብሎ ብድግ አለ። እሱ በተራው ማልቀስ ጀመረ። የዛን እለት አሳር ፍዳውን በልቶ ጓደኛው አስታርቋቸው ሄደ። ታዲያ ሁልጊዜም ቢሆን እንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ስገቡ ያንቀን የተናገረችው ነገር በጆሮው እያስተጋባ ያርደዋል። ቢሆንም ግን ክፉ አመል የሆነበት እና መቼ እንደተፀናወተው የማያውቀው አደገኛ ቅናት አለበት ለመዳን ቢታገልም መፈወስ ያልቻለበት ደዌ። ልክ እንደ {ታምራት ደስታ ሙዚቃ ወድጄ አይደለም ምቀናው ጥሎብኝ ነው የኔ ፍቅር} እንደሚለው። እሱ ራሱ ጭንቅ ስለው ከፍቶ የሚሰማው ይሄን ሙዚቃ ነው። በነገሩ ተበሳጭታ አላናግርህ ስትለውና ስታኮርፍ ይሄን ሙዚቃ በምትወድለት ድምፁ ሲያንጎራጉርላት አንጀቷ አይችልም። አቅፋ ትስመውና ማውራት ይጀምራሉ።
ግን አሁን አሁን ይሄን ፍቅር ልታድን እንደማትችል እየገባት መጥቷል። ልጅ በጣም ብትወድም በዚሁ ፍራቻዋ ምክንያት ነው የመውለድ ፍላጎቷን ያዘገየችው። እዚህ ትዳር ውስጥ ልጅ ማምጣት የልጁን ህይወት ማበላሸት ነው ብላ ነው ምታስበው። ምክንያቱም ይሄ ትዳር በፍቺ እንደሚጠናቀቅ ልቧ ያውቀዋል። እናም ከምታፈቅረው ሰው ልጅ መውለድ ፡ ብትፈታው እንኳን ለትዳሯ እና ለፍቅሯ ለከፈለችው መስዋዕትነት ሁሉ መታሰቢያ ነው ብላ ብታስብም ፡ ልጇን ያለአባት ማሳደግ ግን ልክ አይደለም ብላ ታምናለች። ባሏ ሁልጊዜ የእንውለድ ጥያቄ ያነሳል። ግን ለእሱም ቢሆን ቅናት የለብኝም እያለ ብከራከራትም መቅናትህን አቁመህ እኔን በሙሉ ልብህ አምነህ እንደሰው ማህበራዊ ህይወት ኖሮን ጤናማ ህይወት መኖር ስንጀምር ያኔ እወልዳለሁ ትለዋለች። ደሞ ሁልጊዜም ቢሆን ስላም ሆነው ስለችግሮቻቸው ሲያወሩ : ቅናት እንዳለብህ ማመን ካልቻልክ መዳንም አትችልም ትለዋለች። ካልታረምክ አልወልድልህም ማለቷ ለሱም ባህሪውን ለማስተካከል ጉልበት ይሆነዋል ብላ ታስባለች። የባሏን አስቸጋሪ አመል ለማረቅ ብዙ ነገር ታደርጋለች። ይሄን ትዳር ከተወች ምድር ላይ ብቻዋን እንደምትቀር ታውቃች። እሱ እንዳይቀና ለማድረግ ከህይወቷ ያላስወጣችው ሰው የለም ከወንድ ጓደኞቿ ጋር ብጠረጥራትና ብቀና ከሴት ጓደኞቿ ጋር ደሞ ከማን ጋር ልታገናኝሽ ነው እያለ ቁም ስቅሏን ያሳያታል። ከዚህ ሁሉ ብቀርስ ብላ ሁሉንም እርግፍ አድርጋ ተወችለት። አሁን ግን ትዳርዋን ፡ ፍቅሯን ለማዳን መሞከር እና ማድረግ ያለባትን ሁሉ አድርጋ ጨርሳለች። እሱን ካጣች እንደምትጎዳ እንደምትሰበር ታውቃለች። ከሁሉ በላይ ግን እሱ እሷን ስያጣት የሚሆነውን ነገር ማሰብ ይከብዳታል። በጭራሽ ተጎድቶ ልታየው አትችልም። የሱን ጉዳት የማየት አቅም የላትም። ከራሷ በላይ የሱ ህመም ያማታል። በትዳሯ በኩል ያልተሰማ ብዙ ፀሎት : ያልሰመረ ብዙ ስዕለት አላት። አንዳንዴ አምላኳን እንዲህ ብላ ትጠይቀዋለች። የማያልቅ ፍቅር ሰጥተሄን ስታበቃ : ቅናት ይሉት ስሌት ፍቅራችንን ገዝግዞ ስቆርጠው እያየህ እንዴት ዝም ብለህ ታያለህ!? እንዴት አንድ የማርያም ምህረት ለፍቅራችን አጣህ!?)
✍ሰብለ ወንጌል
#share and join for more👍
SHARE🌼
=ኪ==ነ==ቃ==ል=
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event