አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በአሁኑ ወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደደው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ለማረጋገጥ ተችሏል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነ ሲሆን በህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ለማረጋገጥ መቻሉን አሳውቋል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት ነበረ።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ፦
- ወጣት በ97፣
- ወንድሜ ያዕቆብ፣
- ላውንድሪ ቦይ፣
- ማርትሬዛ፣
- ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣
- ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣
- አንድ ሁለት ፣
- ብር ርርር፣
- ወደው አይሰርቁ፣
- ወፌ ቆመች፣
- እንደ ቀልድ ፣
- ወቶ አደር ፣
- አባት ሀገር
- የሞግዚቷ ልጆች፣
- ይዋጣልን ፣
- ዋሻው፣
- ወሬ ነጋሪ እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል።
@tikvahethiopia
በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በአሁኑ ወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደደው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ለማረጋገጥ ተችሏል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነ ሲሆን በህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ለማረጋገጥ መቻሉን አሳውቋል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት ነበረ።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ፦
- ወጣት በ97፣
- ወንድሜ ያዕቆብ፣
- ላውንድሪ ቦይ፣
- ማርትሬዛ፣
- ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣
- ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣
- አንድ ሁለት ፣
- ብር ርርር፣
- ወደው አይሰርቁ፣
- ወፌ ቆመች፣
- እንደ ቀልድ ፣
- ወቶ አደር ፣
- አባት ሀገር
- የሞግዚቷ ልጆች፣
- ይዋጣልን ፣
- ዋሻው፣
- ወሬ ነጋሪ እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል።
@tikvahethiopia
#Update
የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ ፤ ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ ፤ በታዋቂው እና ተወዳጁ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ህልፈት ሀዘን እንደተሰማው ገልጿል።
በመግለጫው ፤ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) በህይወት በነበረበት ወቅት የዓይን ባንኩ አምባሳደር እንደነበርና ህልፈት በሚያጋጥምበት ጊዜ የዓይን ብሌኑን ለመለገስ ቃልገብቶ እንደነበር ጠቁሟል።
አርቲስቱ በገባው ቃል መሰረትም በቤተሰቦቹ እና በጓደኞቹ ቀና ትብብር ቃሉ ተፈፃሚ መሆኑን ባንኩ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ ፤ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) " ስሙንም ብርሃኑንም ከመቃብር በላይ ህያው አድርጎ ያለፈ መልካም አርቲስት " ሲል ጠርቶታል።
በሌላ በኩል ፤ የአርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ)ን ስርዓተ ቀብር ለማስፈፀም ኮሚቴ ተዋቅሮ እየሰራ ሲሆን ይኸው ኮሚቴ የአርቲስቱ ስርዓተ ቀብር ነገ ታህሳስ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት እንደሚፈፀም ገልጻል።
ከስርዓተ ቀብሩ ቀደም ብሎ ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮዽያ ብሔራዊ ቴአትር ሽኝት ይደረጋልም ተብሏል።
የኢትዮጵያ የዓይን ባንክ ፤ ዛሬ ከሰዓት ባወጣው መግለጫ ፤ በታዋቂው እና ተወዳጁ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ህልፈት ሀዘን እንደተሰማው ገልጿል።
በመግለጫው ፤ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) በህይወት በነበረበት ወቅት የዓይን ባንኩ አምባሳደር እንደነበርና ህልፈት በሚያጋጥምበት ጊዜ የዓይን ብሌኑን ለመለገስ ቃልገብቶ እንደነበር ጠቁሟል።
አርቲስቱ በገባው ቃል መሰረትም በቤተሰቦቹ እና በጓደኞቹ ቀና ትብብር ቃሉ ተፈፃሚ መሆኑን ባንኩ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ ፤ አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) " ስሙንም ብርሃኑንም ከመቃብር በላይ ህያው አድርጎ ያለፈ መልካም አርቲስት " ሲል ጠርቶታል።
በሌላ በኩል ፤ የአርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ)ን ስርዓተ ቀብር ለማስፈፀም ኮሚቴ ተዋቅሮ እየሰራ ሲሆን ይኸው ኮሚቴ የአርቲስቱ ስርዓተ ቀብር ነገ ታህሳስ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት እንደሚፈፀም ገልጻል።
ከስርዓተ ቀብሩ ቀደም ብሎ ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በኢትዮዽያ ብሔራዊ ቴአትር ሽኝት ይደረጋልም ተብሏል።
የወፍ መንገድ
(መዘክር ግርማ)
‹‹እንሂድ›› አለችኝ ፣ ተነስታ እንደ ዘበት
‹‹እንሂድ›› አለችኝ ፣ ወፍ ወደ ጮኸበት
‹‹እውነት?!
እንሂድ ምናሻኝ ፣ አሁኑ እንነሳ
ግን የምንደርበው ፣ ልብስ ብንይዝሳ?››
ይህችን ቃል ባወጣ
በቁጣ
‹‹ከመቼ ወዲህ ነው፣ ወፍ ልብስ የምታውቀው?
ይልቅ እሷን ምሰል፣ ልብስህን አውልቀው!››
ብላኝ ልብሷን ጥላ
ትታኝ ገሰገሰች ፣ ወፏን ተከትላ፡፡
‹‹እሽ ስንቅ እንያዝ?›› ልላት አሰብኩና
ተውኩት ሳልጀምረው
የትኛዋ ወፍ ነች፣ ስንቅ ይዛ ምትበረው?!
በቃ ተከተልኳት ፤
ጥብቅ አ’ረገችኝ ፣ ጥብቅ አደረኳት፡፡
አንደበቴ ሰላ ፣ ዝማሬ ጀመረው
ልቤ ክንፍ አወጣ ፣ መንሳፈፍ አማረው
ከመቼ ወዲህ ነው ፣ ወፍ የማትበረው?!
@write_event
@write_event
@write_event
(መዘክር ግርማ)
‹‹እንሂድ›› አለችኝ ፣ ተነስታ እንደ ዘበት
‹‹እንሂድ›› አለችኝ ፣ ወፍ ወደ ጮኸበት
‹‹እውነት?!
እንሂድ ምናሻኝ ፣ አሁኑ እንነሳ
ግን የምንደርበው ፣ ልብስ ብንይዝሳ?››
ይህችን ቃል ባወጣ
በቁጣ
‹‹ከመቼ ወዲህ ነው፣ ወፍ ልብስ የምታውቀው?
ይልቅ እሷን ምሰል፣ ልብስህን አውልቀው!››
ብላኝ ልብሷን ጥላ
ትታኝ ገሰገሰች ፣ ወፏን ተከትላ፡፡
‹‹እሽ ስንቅ እንያዝ?›› ልላት አሰብኩና
ተውኩት ሳልጀምረው
የትኛዋ ወፍ ነች፣ ስንቅ ይዛ ምትበረው?!
በቃ ተከተልኳት ፤
ጥብቅ አ’ረገችኝ ፣ ጥብቅ አደረኳት፡፡
አንደበቴ ሰላ ፣ ዝማሬ ጀመረው
ልቤ ክንፍ አወጣ ፣ መንሳፈፍ አማረው
ከመቼ ወዲህ ነው ፣ ወፍ የማትበረው?!
@write_event
@write_event
@write_event
ያፍ ዘመድ
ዝም ያለው ዘመዴ እኔ ሳጣጥር፣
ዝም ያለው ወንድሜ እኔ ሳጣጥር፣
ሞተ ቢሉት መጣ አልቅሶ ሊቀብር።
የልቤን እንዳደርስ የእግዚአብሄር ፈቃዱ፣
ሆኖ ተነስቼ እነሱ ሲያረግዱ፤
እንዲህ አልኩት ዘመድ የተባለውን፣
እንዲህ አልኩት ወንድም የተባለውን፣
"ታምሜ ነበረ ሳጣጥር ማዘን፤
አሁን ክንዴ ክንዴ ቀኝ እጄ ቢሉኝ፣
አሁን የናቴ ልጅ ወንድሜ ቢሉኝ፣
ከሞትኩኝ በኋላ ምንም አይገባኝ፣
ይልቅ ልተኛበት አታደንቁረኝ።"
ይህን ተናግሬ የልቤን አድርሼ፣
ወደመጣሁበት ሄድኩኝ ተመልሼ።
መንግሥቱ ለማ (ደማሙ ብዕረኛ)
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ዝም ያለው ዘመዴ እኔ ሳጣጥር፣
ዝም ያለው ወንድሜ እኔ ሳጣጥር፣
ሞተ ቢሉት መጣ አልቅሶ ሊቀብር።
የልቤን እንዳደርስ የእግዚአብሄር ፈቃዱ፣
ሆኖ ተነስቼ እነሱ ሲያረግዱ፤
እንዲህ አልኩት ዘመድ የተባለውን፣
እንዲህ አልኩት ወንድም የተባለውን፣
"ታምሜ ነበረ ሳጣጥር ማዘን፤
አሁን ክንዴ ክንዴ ቀኝ እጄ ቢሉኝ፣
አሁን የናቴ ልጅ ወንድሜ ቢሉኝ፣
ከሞትኩኝ በኋላ ምንም አይገባኝ፣
ይልቅ ልተኛበት አታደንቁረኝ።"
ይህን ተናግሬ የልቤን አድርሼ፣
ወደመጣሁበት ሄድኩኝ ተመልሼ።
መንግሥቱ ለማ (ደማሙ ብዕረኛ)
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ተወኝ
(ጸጋዬ ገብረ መድኅን)
ላታስታምም አትመመኝ
ላትወስደኝ አታንጠልጥለኝ
ይቅር፥ አንጀቴን ቁረጠኝ
ጋሽዬ፥ አልወድሽም በለኝ።
እጅ እጅ አልበል አታባክነኝ
ባክህ፥ ወንድ ነው ቆራጡ፥ እንትፍ-እርገህ ተወኝ።
አየህ፥ እንዳንተ አባት አለኝ
ሴት በወለድኩ ተዋረድኩ፥ ረከስኩ ቀለልኩ እሚለኝ፥
እኔም እንዳንተ እህት አለኝ
ሥጋሽን ሳይሆን ልብሽን፥ ከፍተሽ ጥለሽ ነው እምትለኝ
እና ተወኝ፥ ባክህ ተወኝ፤
እንዳንተ እኔም አለኝ እናት
የሴት ቁንጮ እምመስላት
ጐረቤት ፊት እምታፍር፥ እንዲህ ሆነችልሽ ሲሏት!
እና፥ አልሆንሽም በለኝ
ባክህ አንጀቴን ቁረጠኝ
ፍቅር እንደሁ የኔ ይበቃል፥ ላንተም ለኔም እኔው ልውደድ
ከዘመድ ግንባር ደብቄ፥ እኔ ለብቻዬ ልንደድ፥
ብቻ፥ ከወጥመድህ ለየኝ
አልችልህም፥ ንቀህ ማረኝ
ካንተም ከስሜም ከቤቴም፥ ያጣሁ ብኩን አታድርገኝ፥
ባክህ፥ አንጀቴን ቁረጠኝ
ተወኝ፥ ተወኝ፥ ተወኝ።
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
(ጸጋዬ ገብረ መድኅን)
ላታስታምም አትመመኝ
ላትወስደኝ አታንጠልጥለኝ
ይቅር፥ አንጀቴን ቁረጠኝ
ጋሽዬ፥ አልወድሽም በለኝ።
እጅ እጅ አልበል አታባክነኝ
ባክህ፥ ወንድ ነው ቆራጡ፥ እንትፍ-እርገህ ተወኝ።
አየህ፥ እንዳንተ አባት አለኝ
ሴት በወለድኩ ተዋረድኩ፥ ረከስኩ ቀለልኩ እሚለኝ፥
እኔም እንዳንተ እህት አለኝ
ሥጋሽን ሳይሆን ልብሽን፥ ከፍተሽ ጥለሽ ነው እምትለኝ
እና ተወኝ፥ ባክህ ተወኝ፤
እንዳንተ እኔም አለኝ እናት
የሴት ቁንጮ እምመስላት
ጐረቤት ፊት እምታፍር፥ እንዲህ ሆነችልሽ ሲሏት!
እና፥ አልሆንሽም በለኝ
ባክህ አንጀቴን ቁረጠኝ
ፍቅር እንደሁ የኔ ይበቃል፥ ላንተም ለኔም እኔው ልውደድ
ከዘመድ ግንባር ደብቄ፥ እኔ ለብቻዬ ልንደድ፥
ብቻ፥ ከወጥመድህ ለየኝ
አልችልህም፥ ንቀህ ማረኝ
ካንተም ከስሜም ከቤቴም፥ ያጣሁ ብኩን አታድርገኝ፥
ባክህ፥ አንጀቴን ቁረጠኝ
ተወኝ፥ ተወኝ፥ ተወኝ።
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
የመጀመሪያ ቀን
አየችው ተያዩ
አየና ወደዳት
ቀኑ ማታ ነበር
ወደ ሆቴል ሄዱ
ሁለት እራት መጣ
ብርጭቆው ተጋጨ
አየችው ተያዩ
አያት ተሳሳቁ
በጠረጴዛው ስር
ጭኗ ጭኑን ነካው
አየችው ፈገገ
እጇን በእጁ ያዘው
ጠበቅ አደረጋት
ጠበቅ አረገችው
ከፈሉና ወጡ
በከሰለው ሌሊት
ሁለቱ ነደዱ
ታፋቸው ጋለ
ቤቱ ተቃጠለ
ፍራሹ ነደደ
ፍቅር ተያያዘ፡፡
(ገብረክርስቶስ ደስታ)
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
አየችው ተያዩ
አየና ወደዳት
ቀኑ ማታ ነበር
ወደ ሆቴል ሄዱ
ሁለት እራት መጣ
ብርጭቆው ተጋጨ
አየችው ተያዩ
አያት ተሳሳቁ
በጠረጴዛው ስር
ጭኗ ጭኑን ነካው
አየችው ፈገገ
እጇን በእጁ ያዘው
ጠበቅ አደረጋት
ጠበቅ አረገችው
ከፈሉና ወጡ
በከሰለው ሌሊት
ሁለቱ ነደዱ
ታፋቸው ጋለ
ቤቱ ተቃጠለ
ፍራሹ ነደደ
ፍቅር ተያያዘ፡፡
(ገብረክርስቶስ ደስታ)
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
የ ገ ዢ ኪ ሳ ራ
ይህ ሰፊ ገበያ!
በመንፈስ ተሞልቶ በፍቅር ሲጣራ!
ሸማች የሚጋፋው ቅራቅንቦ ተራ።
“ያ ስንት ነው?” ይላል፣
“ይሄኛውስ?” ይላል፤
የብልጭልጭ አይነት ያነሳል ይጥላል።
ከመንፈስ ገበያ
የውበት ጥሬ እቃ ሞልቶ ተትረፍርፏል፤
ሸማች ግን ልብ የለው
ለኮልኮሌ ፍቅር ማልዶ ተስልፏል።
“ወዴት ነህ?" አይባል -
“ወዴትም! ነው መልሱ!
“ምን በላህ?" ይሉታል -
“ምንም! ልትል ነፍሱ።
እንዲያውም ካሰኘው!
ምን እንደሚፈልግ ፈፅሞ ይዘነጋና፤
“ፀሐይ ስጡኝ!” ብሎ ብቅ ይበል ማምሻውን!
ሰልፈኛ ነውና 'ከጨረቃ ቆርሶ' ይወስዳል ድርሻውን።
የሸማች ሕሊናን መምስል ከሸፈነው፤
ገበያ መታየት ከመግዛት እኩል ነው።
የጠየቀም ገዝቶ፣ የከፈለም ገዝቶ፣
የተላከም ገዝቶ፣ የላክም ሽምቶ፤
እዚያው ይሞታታል!
ያልሞላ ቅርጫቱን ለአምሳዮቹ ትቶ።
ይኸው መጨረሻው !
ሽማቹ ለገላው እየተጨነቀ፣
ገዢው ለብልጭልጭ እየተደነቀ፤
የመንፈስ ከፍታ ተሽርሽሮ አለቀ።
(በረከት በላይነህ - የመንፈስ ከፍታ)
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ይህ ሰፊ ገበያ!
በመንፈስ ተሞልቶ በፍቅር ሲጣራ!
ሸማች የሚጋፋው ቅራቅንቦ ተራ።
“ያ ስንት ነው?” ይላል፣
“ይሄኛውስ?” ይላል፤
የብልጭልጭ አይነት ያነሳል ይጥላል።
ከመንፈስ ገበያ
የውበት ጥሬ እቃ ሞልቶ ተትረፍርፏል፤
ሸማች ግን ልብ የለው
ለኮልኮሌ ፍቅር ማልዶ ተስልፏል።
“ወዴት ነህ?" አይባል -
“ወዴትም! ነው መልሱ!
“ምን በላህ?" ይሉታል -
“ምንም! ልትል ነፍሱ።
እንዲያውም ካሰኘው!
ምን እንደሚፈልግ ፈፅሞ ይዘነጋና፤
“ፀሐይ ስጡኝ!” ብሎ ብቅ ይበል ማምሻውን!
ሰልፈኛ ነውና 'ከጨረቃ ቆርሶ' ይወስዳል ድርሻውን።
የሸማች ሕሊናን መምስል ከሸፈነው፤
ገበያ መታየት ከመግዛት እኩል ነው።
የጠየቀም ገዝቶ፣ የከፈለም ገዝቶ፣
የተላከም ገዝቶ፣ የላክም ሽምቶ፤
እዚያው ይሞታታል!
ያልሞላ ቅርጫቱን ለአምሳዮቹ ትቶ።
ይኸው መጨረሻው !
ሽማቹ ለገላው እየተጨነቀ፣
ገዢው ለብልጭልጭ እየተደነቀ፤
የመንፈስ ከፍታ ተሽርሽሮ አለቀ።
(በረከት በላይነህ - የመንፈስ ከፍታ)
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
አንድ ሰው
እሁድ ማለዳ ላይ...
ገላዋን ታጠበች
ልብሶቿን ለበሰች
ሽቶ ተርከፍክፋ ከጎዳና ወጣች
በመንገድ ስትጓዝ...
የፀጉሯን መዘናፈል የጡቷን መኮፈስ
የረጨችው ሽቶ ካደባባይ ሲነፍስ
እሷን ያየ ሁሉ ወንዱ ተጨነቀ
በደም በውበቷ እየተደነቀ
ያስተዋላት ሁሉ ዓይኑ መንገድ ሳተ
ከዳሌ ከጡቷ ሔደ ተከተተ።
ከቦታው ስትደርስ...
ወዳጇ አልመጣም
ሰአት አልጠበቀም
ለውበቷ አልሳሳም።
ሠዓት ገላመጠች
ፊት ኋላዋን ቃኘች
ማኪያቶ ደገመች
ዙርያዋ ባለው ሰው እጅግ ተናደደች
እልህ ልቧን ሞላ
ፊቷ ከደም ቀላ
የሚመኛት ሁሉም
ወንዶቹ በሞላ
የርሷ ልቧ ሌላ።
ሠዓቱ ረፈደ...
የጠዋት ደስታዋ ከሷ ተሰደደ
አይኖቿ ረጠቡ
አንድ ሰው አሰቡ
አንድ ሰው ተራቡ።
አንድ ሰው ነበረ እርሷን የናፈቀው
ያን ያልመጣውን ሰው
ዓይኗ የተራበው
(ኤፍሬም ስዩም)
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
እሁድ ማለዳ ላይ...
ገላዋን ታጠበች
ልብሶቿን ለበሰች
ሽቶ ተርከፍክፋ ከጎዳና ወጣች
በመንገድ ስትጓዝ...
የፀጉሯን መዘናፈል የጡቷን መኮፈስ
የረጨችው ሽቶ ካደባባይ ሲነፍስ
እሷን ያየ ሁሉ ወንዱ ተጨነቀ
በደም በውበቷ እየተደነቀ
ያስተዋላት ሁሉ ዓይኑ መንገድ ሳተ
ከዳሌ ከጡቷ ሔደ ተከተተ።
ከቦታው ስትደርስ...
ወዳጇ አልመጣም
ሰአት አልጠበቀም
ለውበቷ አልሳሳም።
ሠዓት ገላመጠች
ፊት ኋላዋን ቃኘች
ማኪያቶ ደገመች
ዙርያዋ ባለው ሰው እጅግ ተናደደች
እልህ ልቧን ሞላ
ፊቷ ከደም ቀላ
የሚመኛት ሁሉም
ወንዶቹ በሞላ
የርሷ ልቧ ሌላ።
ሠዓቱ ረፈደ...
የጠዋት ደስታዋ ከሷ ተሰደደ
አይኖቿ ረጠቡ
አንድ ሰው አሰቡ
አንድ ሰው ተራቡ።
አንድ ሰው ነበረ እርሷን የናፈቀው
ያን ያልመጣውን ሰው
ዓይኗ የተራበው
(ኤፍሬም ስዩም)
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
በስብሐት ገብረእግዚያብሄር
ምንም ብታደርጉ ሰዎች ከማውራት ስለማይመለሱ ዝም
:
☞ ደሀ ብትሆን የመናጢ ልጅ ፤ ሀብታም ብትሆን ዶላር ያሳበጠው ይሉሀል።
☞ ከሴት ጋር ብትሄድ ሴሰኛ ፤ ብቻህን ብትሆን ወፈፌ ይሉሀል ።
☞ ብትፈጥን ቀዥቃዣ ፥ ብትዘገይ ዘገምተኛ ።
☞ ብታወራ ለፍላፊ ፥ ዝምብትል ዝጋታም ።
☞ ብትራመድ አርፎ አይቀመጥም ፥ አርፈህ ብትቀመጥ ዝፍዝፍ
☞ ብትማር አወቅሁ ባይ ፥ ባትማር የአቡጊዳ ሽፍታ ።
☞ ብትወፍር ጠብደል ፥ ብትከሳ በልቶ ማይጠረቃ ።
☞ ብትይዝ ቋጣሪ ፥ ብትለቅ መንዛሪ ። ...
እንደውም አንድ የሀገራችን ተረት አለ"ባልና ሚስት አህያ እየነዱ ሲሄዱ ተቺዎች አገኙዋቸውና ፦"እንከፎች አህያዋ ሳለች እንዴት አይሳፈሩባትም" ሲሉ ባል ሰማና ሚስቱን " በይ ፍጠኚና አህያዋ ላይ ተሳፈሪ" - አላት።
ትንሽ እንደሄዱ ሌሎች ተቺዎች ፦ "ይች ባለጌ ፥ ባል በእግር እየሄደ ሚስት በጋማ ከብት" ብለው ወረፏቸው።ባል ሚስቱን አስወርዶ አህያዋ ወገብ ላይ ቂብ አለ ፤ትንሽ እንደተጋዙ ሌሎች ተቺዎች አገኝዋቸው ፦ "የተረገመ ሚስቱን በእግር እያስኬደ እሱ በአህያዋ ብለው ወረዱባቸው ።
ባልና ሚስት ድንገት ቢተዉን ብለው አህያዋ ላይ ሲፈናጠጡ ሌሎች ተቺዎች ደም አገኙዋቸውና "ምን እንስሳ ብትሆን ለሁለት ይከመሩባታል ግፈኞች ..." የስድብ ናዳ ለቀቁባቸው ።
እንግዲህ ወዳጆቼ ፦ አህያዋን ቢሸከሙ ኖሮ ከዚህ አይብስምን ?
ስለዚህ ሰዎች ያሉትን ይበሉ አንተ አንተነትህን ሁንና ህሊናህ አውጥቶና አውርዶ ከተቀበለው ሀሳብ ጋር ተስማማ።
:
ለጮኸ ውሻ ሁላ ድንጋይ መወርወር ጊዜን ማባከን ነው፡፡
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ምንም ብታደርጉ ሰዎች ከማውራት ስለማይመለሱ ዝም
:
☞ ደሀ ብትሆን የመናጢ ልጅ ፤ ሀብታም ብትሆን ዶላር ያሳበጠው ይሉሀል።
☞ ከሴት ጋር ብትሄድ ሴሰኛ ፤ ብቻህን ብትሆን ወፈፌ ይሉሀል ።
☞ ብትፈጥን ቀዥቃዣ ፥ ብትዘገይ ዘገምተኛ ።
☞ ብታወራ ለፍላፊ ፥ ዝምብትል ዝጋታም ።
☞ ብትራመድ አርፎ አይቀመጥም ፥ አርፈህ ብትቀመጥ ዝፍዝፍ
☞ ብትማር አወቅሁ ባይ ፥ ባትማር የአቡጊዳ ሽፍታ ።
☞ ብትወፍር ጠብደል ፥ ብትከሳ በልቶ ማይጠረቃ ።
☞ ብትይዝ ቋጣሪ ፥ ብትለቅ መንዛሪ ። ...
እንደውም አንድ የሀገራችን ተረት አለ"ባልና ሚስት አህያ እየነዱ ሲሄዱ ተቺዎች አገኙዋቸውና ፦"እንከፎች አህያዋ ሳለች እንዴት አይሳፈሩባትም" ሲሉ ባል ሰማና ሚስቱን " በይ ፍጠኚና አህያዋ ላይ ተሳፈሪ" - አላት።
ትንሽ እንደሄዱ ሌሎች ተቺዎች ፦ "ይች ባለጌ ፥ ባል በእግር እየሄደ ሚስት በጋማ ከብት" ብለው ወረፏቸው።ባል ሚስቱን አስወርዶ አህያዋ ወገብ ላይ ቂብ አለ ፤ትንሽ እንደተጋዙ ሌሎች ተቺዎች አገኝዋቸው ፦ "የተረገመ ሚስቱን በእግር እያስኬደ እሱ በአህያዋ ብለው ወረዱባቸው ።
ባልና ሚስት ድንገት ቢተዉን ብለው አህያዋ ላይ ሲፈናጠጡ ሌሎች ተቺዎች ደም አገኙዋቸውና "ምን እንስሳ ብትሆን ለሁለት ይከመሩባታል ግፈኞች ..." የስድብ ናዳ ለቀቁባቸው ።
እንግዲህ ወዳጆቼ ፦ አህያዋን ቢሸከሙ ኖሮ ከዚህ አይብስምን ?
ስለዚህ ሰዎች ያሉትን ይበሉ አንተ አንተነትህን ሁንና ህሊናህ አውጥቶና አውርዶ ከተቀበለው ሀሳብ ጋር ተስማማ።
:
ለጮኸ ውሻ ሁላ ድንጋይ መወርወር ጊዜን ማባከን ነው፡፡
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
☑"የምትጓዝበት መንገድ ወደ ጥሩ አሊያም ወደ መጥፎ የሚመራው አንተን እንጂ ተመልካችህን አይደለም፤የምትለብሠው ልብስ የሚያሞቀውም ሆነ የሚያበርደው አንተኑ እንጂ የሚያይህን አይደለም፤የምትበላው ምግብ የሚጣፍጠው ወይም የሚመረው አንተን እንጂ ሌላውን አይደለም።
☑ ብዙ ውጫዊ ነገሮች አስደሳች ቢሆኑም ከጊዜ ጋር የተሳሰሩና ሃላፊ ናቸው። ዛሬ ያስደሰተን ጓደኛ ነገ ላይኖር ይችላል ዛሬ ያጌጥንበት ውበት ነገ ይረግፋል፤ ዛሬ የተመካንበት አስተሳሰብ ነገ በቆመበት አይጸናም። ከውጪ የምናገኘው ማንኛውም አይነት ደስታ በመጣበት እግሩ ጥሎን መሄዱ አይቀርም። ከዛም አልፎ ዋጋ ያስከፍለናል። ከጊዜ ጋር የማይለዋወጥ ደስታን ለማግኘት ብቸኛ መፍትሄው ደስታና ሰላምን በውስጣችን መፈለግ ነው። እንደ ኩሬ ውሃ ያነሰች፤ እንደ ኩራዝ መብራት የቀጨጨች፤ እንደ ሰናፍጭ ቅንጣት የደቀቀችም ብትሆንም እንኳን ውስጣዊ ደስታን በልባችን መትከል ነው። ይህ ነው ማንም ሊነካውና ሊደፍረው የማይገባው ስፍራ።
☑ በርግጠኝነት ለሰው ብለን የምንይዘው ማንነት፤ ለኛ በልክ እንዳልተሰፋ ልብስ አያምርብንም፤ ቀላሉ መፍትሄ እራሳችንን መሆን እና፤ መክሊታችንን መኖር ነው። በዚህ ስፍራ ውስጥ ሙሉ ነን፤ እውነተኛ እኛነታችን የሚታየው በዚህ ስፍራ ነው። ወደ ውስጣችን ዘልቀን በዚህ ስፍራ ላይ ቆመን ህይወታችንን ብናየው፤ እንደምናስበው ደካማ አይደለንም፤ የሚጎድለን ብዙ አይደለም፤ ከምንም በላይ በፈጠረን ፈጣሪ አይን ውስጥ ውብና ንጹህ ነን። ታዲያ ከዚህ በላይ ምን አለ? ደስታና ሰላማችን በሰው እጅ ፤ ፍርድና ቅጣታችን በሰው ወንበር ፈጽሞ አይሁን.!!
ከ ስብዕናችን
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
☑ ብዙ ውጫዊ ነገሮች አስደሳች ቢሆኑም ከጊዜ ጋር የተሳሰሩና ሃላፊ ናቸው። ዛሬ ያስደሰተን ጓደኛ ነገ ላይኖር ይችላል ዛሬ ያጌጥንበት ውበት ነገ ይረግፋል፤ ዛሬ የተመካንበት አስተሳሰብ ነገ በቆመበት አይጸናም። ከውጪ የምናገኘው ማንኛውም አይነት ደስታ በመጣበት እግሩ ጥሎን መሄዱ አይቀርም። ከዛም አልፎ ዋጋ ያስከፍለናል። ከጊዜ ጋር የማይለዋወጥ ደስታን ለማግኘት ብቸኛ መፍትሄው ደስታና ሰላምን በውስጣችን መፈለግ ነው። እንደ ኩሬ ውሃ ያነሰች፤ እንደ ኩራዝ መብራት የቀጨጨች፤ እንደ ሰናፍጭ ቅንጣት የደቀቀችም ብትሆንም እንኳን ውስጣዊ ደስታን በልባችን መትከል ነው። ይህ ነው ማንም ሊነካውና ሊደፍረው የማይገባው ስፍራ።
☑ በርግጠኝነት ለሰው ብለን የምንይዘው ማንነት፤ ለኛ በልክ እንዳልተሰፋ ልብስ አያምርብንም፤ ቀላሉ መፍትሄ እራሳችንን መሆን እና፤ መክሊታችንን መኖር ነው። በዚህ ስፍራ ውስጥ ሙሉ ነን፤ እውነተኛ እኛነታችን የሚታየው በዚህ ስፍራ ነው። ወደ ውስጣችን ዘልቀን በዚህ ስፍራ ላይ ቆመን ህይወታችንን ብናየው፤ እንደምናስበው ደካማ አይደለንም፤ የሚጎድለን ብዙ አይደለም፤ ከምንም በላይ በፈጠረን ፈጣሪ አይን ውስጥ ውብና ንጹህ ነን። ታዲያ ከዚህ በላይ ምን አለ? ደስታና ሰላማችን በሰው እጅ ፤ ፍርድና ቅጣታችን በሰው ወንበር ፈጽሞ አይሁን.!!
ከ ስብዕናችን
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
አንድ የስነ-ሰብ (Anthropology) ተመራማሪ ወደ ደቡብ አፍሪካ ገጠራማ መንደር ለስራ ያቀናል። በቆይታውም ከህጻናት ጋር መግባባትን ይፈጥራል። እናም ሕጻናቱን ለማስደሰት አንድ ሽልማት ያለው ጨዋታ ያዘጋጃል።
ጨዋታውም፣ በማንጎ የተሞላ አንድ ቅርጫት ከዛፍ ስር ያስቀምጣል፣ ህጻናቱን ከዛፉ አንድ መቶ ሜትር እንዲርቁ አደረገ፣ ከዛም እንዲህ አላቸው:-
"እኔ ጀምሩ ስል ቀድሞ ቅርጫቱ ጋ የደረሰ የፈለገውንና የሚችለውን ያህል ማንጎ ይበላል:: "
ጨዋታው ተጀመረ።
ህጻናቱ ግን ከጨዋታው ህግ ውጪ ያልተጠበቀ ነገር አደረጉ።
ይህም ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዘው እኩል ወደ ቅርጫቱ ሮጡ። ከዚያም አንድ ላይ በቅርጫቱ ውስጥ ያለውን ማንጎ በአሸናፊነት መንፈስ ተካፍለው መብላት ጀመሩ::
የስነ-ሰብ ተመራማሪውም በመገረም "ለምን እንዲህ አደረጋቹ?"ሲል ጠየቃቸው።
ሁሉም በአንድነት "ኡቡንቱ! " በማለት መለሱለት።
በመቀጠል አንዱ ህፃን እንዲህ አለው:-
"እንዴት ሌሎች ጓደኞቻችን ተከፍተው አንድ ልጅ ብቻውን ይደሰታል? ይሄ ባህላችን አይደለም::"
"ኡቡንቱ" የቃሉ መሠረት የደቡብ አፍሪቃው የዙሉ ማሕበረሰብ ሲሆን፤ ትርጓሜውም:-
“ለመኖሬ ምክንያት አንተ ነህ፤ ላንተም መኖር እኔ!” የሚል ሰብዓዊነትን ያዘለ ፍልስፍና ነው።
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ጨዋታውም፣ በማንጎ የተሞላ አንድ ቅርጫት ከዛፍ ስር ያስቀምጣል፣ ህጻናቱን ከዛፉ አንድ መቶ ሜትር እንዲርቁ አደረገ፣ ከዛም እንዲህ አላቸው:-
"እኔ ጀምሩ ስል ቀድሞ ቅርጫቱ ጋ የደረሰ የፈለገውንና የሚችለውን ያህል ማንጎ ይበላል:: "
ጨዋታው ተጀመረ።
ህጻናቱ ግን ከጨዋታው ህግ ውጪ ያልተጠበቀ ነገር አደረጉ።
ይህም ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዘው እኩል ወደ ቅርጫቱ ሮጡ። ከዚያም አንድ ላይ በቅርጫቱ ውስጥ ያለውን ማንጎ በአሸናፊነት መንፈስ ተካፍለው መብላት ጀመሩ::
የስነ-ሰብ ተመራማሪውም በመገረም "ለምን እንዲህ አደረጋቹ?"ሲል ጠየቃቸው።
ሁሉም በአንድነት "ኡቡንቱ! " በማለት መለሱለት።
በመቀጠል አንዱ ህፃን እንዲህ አለው:-
"እንዴት ሌሎች ጓደኞቻችን ተከፍተው አንድ ልጅ ብቻውን ይደሰታል? ይሄ ባህላችን አይደለም::"
"ኡቡንቱ" የቃሉ መሠረት የደቡብ አፍሪቃው የዙሉ ማሕበረሰብ ሲሆን፤ ትርጓሜውም:-
“ለመኖሬ ምክንያት አንተ ነህ፤ ላንተም መኖር እኔ!” የሚል ሰብዓዊነትን ያዘለ ፍልስፍና ነው።
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
ንጉሥ ሲጨንቀው
የአንዲት ደሃ ሃገር ዜጎቿ በሙሉ፣
መሄጃ ቢያሳጡት “ተራብን!” እያሉ፣
ምስኪን ንጉሣቸው እንዲህ ፀለየ አሉ፦
“እባክህ አምላኬ!
የተራበ ሕዝቤን ሲያሻህ በነጠላ፤
ካሰኘህ በጅምላ፣
ከፊቴ አርቅና ባህር ክተትልኝ፤
ከሃይቅ ጣልልኝ፡፡
ከዚያማ!
ያልቻሉት ሲሰምጡ፤
የቻሉት ለማምሻ ዓሣ ይዘው ይውጡ!"
ገጣሚ -በረከት በላይነህ
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event
የአንዲት ደሃ ሃገር ዜጎቿ በሙሉ፣
መሄጃ ቢያሳጡት “ተራብን!” እያሉ፣
ምስኪን ንጉሣቸው እንዲህ ፀለየ አሉ፦
“እባክህ አምላኬ!
የተራበ ሕዝቤን ሲያሻህ በነጠላ፤
ካሰኘህ በጅምላ፣
ከፊቴ አርቅና ባህር ክተትልኝ፤
ከሃይቅ ጣልልኝ፡፡
ከዚያማ!
ያልቻሉት ሲሰምጡ፤
የቻሉት ለማምሻ ዓሣ ይዘው ይውጡ!"
ገጣሚ -በረከት በላይነህ
---------------------------
Share & join
@write_event
@write_event
@write_event