"እጅህ የሚያገኘውን ስራ ሁሉ በሙሉ ሀይልህ ስራው ፣ልትሄድበት ባለው መቃብር ውስጥ መስራትም ሆነ ማቀድም የለምና"።
⚜️ ጠቢቡ ሰለሞን⚜️
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
⚜️ ጠቢቡ ሰለሞን⚜️
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
😂😂ለፈገግታ😂😂
‹‹ቲማቲም ወርውሮ ትላንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው››
(አሌክስ አብርሃም)
🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅
የሆነ ጊዜ ሃላፊየ ወክለውኝ ሃላፊ ሁኘ ስሰራ . . . ሁለት ወጣቶች ቢሮየ መጡ . . .💃🕺
ሴትና ወንድ ናቸው ! ሁለቱም መስሪያ ቤቴ አካባቢ ካለ
የሃብታም ልጆች ትምህርት🏢 ቤት ነበር አመጣጣቸው . . .
የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪወች ሲሆኑ የሴቷ አለባበስ ያለማጋነን የኦስካር እጩ
አስመስሏታል . . .በዛ ላይ ኑሮ ምችት ያላት ቆንጆ . . .በእንግሊዝኛ አፏን ስለፈታች ነው መሰል አማረኛ ገደል ሁኖባት ቃላትን እየፈለገች ነው
የምትናገረው …ወንዱም እንደልጅቱ ባይሆንም ሽክ ብሏል ….
👱♀‹‹ የመጣነው ላሰብነው ፕሮግራም ስፖ….ንሰር እንድትሆኑን ነው ››
አለች
ልጅቱ ብዙ ጊዜ ወደቢሮ ብቅ እያሉ ስፖንሰርየሚጠይቁን የቀበሌ
የወጣቶች ..የሴቶች …የምንትስ ሰወች ወይም የተቸገሩ ሚስኪኖች ስለነበሩ ‹‹ስፖንሰር ›› የሚለው ፅንሰሃሳቡ ወይ የድሆች ወይ
የፖለቲከኞች እየመሰለኝ ከመጣ ቆይቷል . . . እነዚህ ምቾት ያሰቃያቸው ልጆች እንዴት ‹‹ስፖንሰር ሁኑን ›› እንዳሉ ገርሞኝ ጉደዩን ጠየኩ
👱♀‹‹ ዩ ኖ . . . በትምህርት ቤታችን ‹የቲማቲም ቀን🍅› ልናከብር አስበናል . . . ዛት ማች ብዙ ብር ምናምን የሚፈልግ አይደለም …››
👨💼‹‹የቲማቲም ቀን 🍅? ›› ስል ጠየኩ
👱♀‹‹ያ …በቃ ተማወች የሆነ ሰአት ይወስኑና ግቢ ውስጥ ቲማቲም መወራወር ምናምን በጣም ያዝናናል ...ውጭ ምናምን የተለመደ ነው
..እናም በጎ ነገሮችን ወደሃገራችን ብናስገባ ቀስ እያለ ከትምህርት ቤት ወደሁሉም ትምህርት ቤቶች ከዛ በአገር ደረጃ በቃ የቲማቲም ቀን
ተብሎ በአመት አንዴ ይከበራል . . . ››
ሁለቱም ገርመውኝ ተራ በተራ እያየኋቸው
👨💼‹‹እና ቲማቲም🍅 እየተወራወራችሁ ቀኑን ልታከብሩ ነው . . ?>>
👱♀<<YAp>>
👨💼<<.አላማው ግን ምንድነው ?››
👱‹‹ ጀስት ፈን! …እና ደግሞ አለ አይደል ሌላው <ወርል ድ> በፋሚን ድሮውውት ምናምን ነው ኢትዮጲያን የሚያውቃት ..የቲማቲም ቀን
በማክበር ግን አገራችን ጀስት ከእርሃብ እንደወጣች ለማሳየት … በዛ ላይ ቦንብ ምናምን ድንጋይ የሚወረወርበት ጊዜ እንዳለፈና ፒስ
መሆናችንን ለማሳየት ››
አለ ወንዱ ልጅ
👱♀‹‹በተጨማሪም ›› አለች ሴቷ ‹‹በተጨማሪም አሁን ያለንን የአበላል ሃቢት አለ አይደል ፒፕሉ ስጋ ቁርጥ ምናምን ያበዛል .. ይሄ ለብዙ በሽታ
ስለሚያጋልጥ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲመገብ ፕሮሞት ማድረግም ይቻላል
›› ስትል አብራራችልኝ !
👨💼ጎበዝ ተበላን ! እነዚህ የሃብታም ትምህርት ቤቶች ባለራእይ ትውልድ እያመረቱ ነው . . . ትክዝ ብየ አየኋቸው . . . ደመወዝ ጨምሩልኝ እያለ
ሁለት ወር ቢሮየ የተመላለሰው የአራት ልጆች አባት ጋሽ ወጋየሁ ቢሮየ በር ላይ ቁሞ ይታየኛል ልጆቹ እስኪወጡ እየጠበቀ . . . ሁለት መቶ
ብር ጨምሩልኝ ብሎ ሁለት ገፅ ማመልከቻ ፅፏል …ሚስኪን የቲማቲም ቀን ሲከበር ይሄ ሰውየ ‹‹የአበላል ሃቢቱን ያስተካክል ይሆን ? ››
እላለሁ . . .
👱♀‹‹ አስር ሽ ብር ምናምን ስፖንሰር ብትሆኑን . . . ›› ልጅቱ ቀጥላለች . . .
እኔም በዓሉ ላይ ብገኝ እና ቲማቲም እነዚህ ልጆች ላይ እንዲሁም መምህራኖቻቸው ላይ ብወረውር ብየ ተመኘሁ ...እና በተለይ
ወላጆቻቸው ላይ ....ግን እኔ የምወረውረው ቲማቲም በጣሳ የታሸገ መሆን አለበት . . . ግንባር ግንባራቸውን !
ቲማቲም ወርውሮ ትላንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው
ደነገጥኩ አይቸ ሲንዠቀዠቅ ደሙ
በጣሳ ውስጥ ነበር ለካስ ቲማቲሙ …..እንዲል ገጣሚው !
*
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
*
‹‹ቲማቲም ወርውሮ ትላንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው››
(አሌክስ አብርሃም)
🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅
የሆነ ጊዜ ሃላፊየ ወክለውኝ ሃላፊ ሁኘ ስሰራ . . . ሁለት ወጣቶች ቢሮየ መጡ . . .💃🕺
ሴትና ወንድ ናቸው ! ሁለቱም መስሪያ ቤቴ አካባቢ ካለ
የሃብታም ልጆች ትምህርት🏢 ቤት ነበር አመጣጣቸው . . .
የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪወች ሲሆኑ የሴቷ አለባበስ ያለማጋነን የኦስካር እጩ
አስመስሏታል . . .በዛ ላይ ኑሮ ምችት ያላት ቆንጆ . . .በእንግሊዝኛ አፏን ስለፈታች ነው መሰል አማረኛ ገደል ሁኖባት ቃላትን እየፈለገች ነው
የምትናገረው …ወንዱም እንደልጅቱ ባይሆንም ሽክ ብሏል ….
👱♀‹‹ የመጣነው ላሰብነው ፕሮግራም ስፖ….ንሰር እንድትሆኑን ነው ››
አለች
ልጅቱ ብዙ ጊዜ ወደቢሮ ብቅ እያሉ ስፖንሰርየሚጠይቁን የቀበሌ
የወጣቶች ..የሴቶች …የምንትስ ሰወች ወይም የተቸገሩ ሚስኪኖች ስለነበሩ ‹‹ስፖንሰር ›› የሚለው ፅንሰሃሳቡ ወይ የድሆች ወይ
የፖለቲከኞች እየመሰለኝ ከመጣ ቆይቷል . . . እነዚህ ምቾት ያሰቃያቸው ልጆች እንዴት ‹‹ስፖንሰር ሁኑን ›› እንዳሉ ገርሞኝ ጉደዩን ጠየኩ
👱♀‹‹ ዩ ኖ . . . በትምህርት ቤታችን ‹የቲማቲም ቀን🍅› ልናከብር አስበናል . . . ዛት ማች ብዙ ብር ምናምን የሚፈልግ አይደለም …››
👨💼‹‹የቲማቲም ቀን 🍅? ›› ስል ጠየኩ
👱♀‹‹ያ …በቃ ተማወች የሆነ ሰአት ይወስኑና ግቢ ውስጥ ቲማቲም መወራወር ምናምን በጣም ያዝናናል ...ውጭ ምናምን የተለመደ ነው
..እናም በጎ ነገሮችን ወደሃገራችን ብናስገባ ቀስ እያለ ከትምህርት ቤት ወደሁሉም ትምህርት ቤቶች ከዛ በአገር ደረጃ በቃ የቲማቲም ቀን
ተብሎ በአመት አንዴ ይከበራል . . . ››
ሁለቱም ገርመውኝ ተራ በተራ እያየኋቸው
👨💼‹‹እና ቲማቲም🍅 እየተወራወራችሁ ቀኑን ልታከብሩ ነው . . ?>>
👱♀<<YAp>>
👨💼<<.አላማው ግን ምንድነው ?››
👱‹‹ ጀስት ፈን! …እና ደግሞ አለ አይደል ሌላው <ወርል ድ> በፋሚን ድሮውውት ምናምን ነው ኢትዮጲያን የሚያውቃት ..የቲማቲም ቀን
በማክበር ግን አገራችን ጀስት ከእርሃብ እንደወጣች ለማሳየት … በዛ ላይ ቦንብ ምናምን ድንጋይ የሚወረወርበት ጊዜ እንዳለፈና ፒስ
መሆናችንን ለማሳየት ››
አለ ወንዱ ልጅ
👱♀‹‹በተጨማሪም ›› አለች ሴቷ ‹‹በተጨማሪም አሁን ያለንን የአበላል ሃቢት አለ አይደል ፒፕሉ ስጋ ቁርጥ ምናምን ያበዛል .. ይሄ ለብዙ በሽታ
ስለሚያጋልጥ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲመገብ ፕሮሞት ማድረግም ይቻላል
›› ስትል አብራራችልኝ !
👨💼ጎበዝ ተበላን ! እነዚህ የሃብታም ትምህርት ቤቶች ባለራእይ ትውልድ እያመረቱ ነው . . . ትክዝ ብየ አየኋቸው . . . ደመወዝ ጨምሩልኝ እያለ
ሁለት ወር ቢሮየ የተመላለሰው የአራት ልጆች አባት ጋሽ ወጋየሁ ቢሮየ በር ላይ ቁሞ ይታየኛል ልጆቹ እስኪወጡ እየጠበቀ . . . ሁለት መቶ
ብር ጨምሩልኝ ብሎ ሁለት ገፅ ማመልከቻ ፅፏል …ሚስኪን የቲማቲም ቀን ሲከበር ይሄ ሰውየ ‹‹የአበላል ሃቢቱን ያስተካክል ይሆን ? ››
እላለሁ . . .
👱♀‹‹ አስር ሽ ብር ምናምን ስፖንሰር ብትሆኑን . . . ›› ልጅቱ ቀጥላለች . . .
እኔም በዓሉ ላይ ብገኝ እና ቲማቲም እነዚህ ልጆች ላይ እንዲሁም መምህራኖቻቸው ላይ ብወረውር ብየ ተመኘሁ ...እና በተለይ
ወላጆቻቸው ላይ ....ግን እኔ የምወረውረው ቲማቲም በጣሳ የታሸገ መሆን አለበት . . . ግንባር ግንባራቸውን !
ቲማቲም ወርውሮ ትላንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው
ደነገጥኩ አይቸ ሲንዠቀዠቅ ደሙ
በጣሳ ውስጥ ነበር ለካስ ቲማቲሙ …..እንዲል ገጣሚው !
*
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
*
ማንም ሰው በዛ ቦታ ቢሆን ተመሣሣዩን ላለማድረጉ በፍፁም ታማኝነት ራሱን እስካልጠየቀ ድረስ መፍረድ የለበትም!
-- Viktor Frankl --
JOIN US 🙏
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
-- Viktor Frankl --
JOIN US 🙏
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
እምነት - ክህደት - እውነት
┈┈┈•✦•┈┈┈
✍ ኤፍሬም ስዩም
'
የምናምን ዕለት
ፀሐይ ትዞራለች
ባስራ-ሁለቱ መስኮት ገብታ ትወጣለች
•
የምንጠይቅ ወራት
መሬት ትዞራለች
ያማኝን ልቦና.. ሽፍታ ታደርጋለች
•
በገጣሚ ምናብ
ከንቱ የ'ምነት ዓይን ከንቱ ፍልስፍና
ሰማይ ነው የሚዞረው። ...
ምክንያቱም..
የትላንቱን ኮከብ ከትላንቱ ቦታው
ዛሬ ላይ መች አየው? ...
════════
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
┈┈┈•✦•┈┈┈
✍ ኤፍሬም ስዩም
'
የምናምን ዕለት
ፀሐይ ትዞራለች
ባስራ-ሁለቱ መስኮት ገብታ ትወጣለች
•
የምንጠይቅ ወራት
መሬት ትዞራለች
ያማኝን ልቦና.. ሽፍታ ታደርጋለች
•
በገጣሚ ምናብ
ከንቱ የ'ምነት ዓይን ከንቱ ፍልስፍና
ሰማይ ነው የሚዞረው። ...
ምክንያቱም..
የትላንቱን ኮከብ ከትላንቱ ቦታው
ዛሬ ላይ መች አየው? ...
════════
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
════════
✍ ኤፍሬም ስዩም
ጊ ዜ
┈✦┈
እግዜር
በምድራችን የተከላት
ጊዜ የሚሏት - ጽጌረዳ
ገና እንኳን ሳታብብ ገና ሳትፈነዳ
ጨለማዋ እሾህ
ጨክኖ ቢወጋት
ወግቶ ቢያሸንፋት
የልቧን አወራች
እውነት ተናገረች ...
ነገ በማለዳ ... ዛሬ ሟች ነኝ አለች።
════════
📓 ኑ ግድግዳ እናፍርስ
join
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
✍ ኤፍሬም ስዩም
ጊ ዜ
┈✦┈
እግዜር
በምድራችን የተከላት
ጊዜ የሚሏት - ጽጌረዳ
ገና እንኳን ሳታብብ ገና ሳትፈነዳ
ጨለማዋ እሾህ
ጨክኖ ቢወጋት
ወግቶ ቢያሸንፋት
የልቧን አወራች
እውነት ተናገረች ...
ነገ በማለዳ ... ዛሬ ሟች ነኝ አለች።
════════
📓 ኑ ግድግዳ እናፍርስ
join
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
ውዴ!
ሂድ ባልሽኝ መንገድ
ቃልሽን አክብሬ ከፊትሽ ሄጃለሁ፤
ግን
የመውደዴን ቅኔ ለልብሽ ትቻለሁ ፤
እናም አንቺ
ለቅኔው ፍቺ ፈልገሽ፣
ሂድ ባልሽኝ መንገድ ና ያልሽኝ ለታ፣
ከመንገድ ቆሜያለሁ
ሌላ ቅኔ አግኝቼ ቅኔሽን ሳልፈታ።
==========
መላኩ ደምሴ
ከ"ገላ ና ገላ' የግጥም መድብል መፅሐፍ
2013
==========
https://t.me/write_event
ሂድ ባልሽኝ መንገድ
ቃልሽን አክብሬ ከፊትሽ ሄጃለሁ፤
ግን
የመውደዴን ቅኔ ለልብሽ ትቻለሁ ፤
እናም አንቺ
ለቅኔው ፍቺ ፈልገሽ፣
ሂድ ባልሽኝ መንገድ ና ያልሽኝ ለታ፣
ከመንገድ ቆሜያለሁ
ሌላ ቅኔ አግኝቼ ቅኔሽን ሳልፈታ።
==========
መላኩ ደምሴ
ከ"ገላ ና ገላ' የግጥም መድብል መፅሐፍ
2013
==========
https://t.me/write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
ዝሜን እጮኻለሁ
============
=======
ዲበኩሉ ጌታ
ከ"ነፍስ ቦታ"
========
JOIN & SHARE
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
============
ቃል እስከሚያልቅብኝ
ቃልን እስክኾነው...
የምጮኸው ኹሉ ፣ ታላቅ ጥሞና ነው።=======
ዲበኩሉ ጌታ
ከ"ነፍስ ቦታ"
========
JOIN & SHARE
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
ቅኝት
____
አንድ ነው ክራሩ...
የጅማት ነው ክሩ...
የሚወጣው ዜማ ለየቅል የሆነው
ቅኝቱን ስንቃኝ...
ያንተ አንቺ ሆዬ የኔ ትዝታ ነው።
========
በረከት አበበ
ከ"ሰው ከሆሳዕና እስከ ስቅለት " የግጥም መድብል።
___
JOIN & SHARE
___
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
____
አንድ ነው ክራሩ...
የጅማት ነው ክሩ...
የሚወጣው ዜማ ለየቅል የሆነው
ቅኝቱን ስንቃኝ...
ያንተ አንቺ ሆዬ የኔ ትዝታ ነው።
========
በረከት አበበ
ከ"ሰው ከሆሳዕና እስከ ስቅለት " የግጥም መድብል።
___
JOIN & SHARE
___
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
በሁለት ስሜት መሃል ፣ የተውሽኝ አግለሽ ፣
እንደ ጌታ ምጽአት ፣ "ብቻ ጠብቅ" ብለሽ ፣
ያልሽኝን ሰምቼ ፣ አለሁ እያነሱ ጋጠጥኹ፣
ያንቺን መምጣት ሳይኾን
የኔን ተስፋ መቁረጥ ፣ በቁሜ እየጠበቀኹ።
__________
ኤልያስ ሽታኹን
__________
ከ"ርዕስ የለውም "
__________
JOIN & SHARE
__________
@Write_event
@Write_event
@Write_event
__________
እንደ ጌታ ምጽአት ፣ "ብቻ ጠብቅ" ብለሽ ፣
ያልሽኝን ሰምቼ ፣ አለሁ እያነሱ ጋጠጥኹ፣
ያንቺን መምጣት ሳይኾን
የኔን ተስፋ መቁረጥ ፣ በቁሜ እየጠበቀኹ።
__________
ኤልያስ ሽታኹን
__________
ከ"ርዕስ የለውም "
ግጥም መድብል__________
JOIN & SHARE
__________
@Write_event
@Write_event
@Write_event
__________
እንዴት እንዴት ፣
_____________
አሸናፊ ተሾመ
ከ"ካፊያ ሆኖ ቀረ" የግጥም መድብል
____________
JOIN & SHARE
@Write_event
@Write_event
@Write_event
___________
እንዴት እችላለሁ
ከቅኝትሽ መውጣት
ከፍ ቢልም
ዝቅ ቢልም
ሸሽቼ ማልሸሸው
ወጥቼ የማልወጣው
ሁሉም ቅኝትሽ ነው።_____________
አሸናፊ ተሾመ
ከ"ካፊያ ሆኖ ቀረ" የግጥም መድብል
____________
JOIN & SHARE
@Write_event
@Write_event
@Write_event
___________
"ላይለ ኩሉ"
--------------
--------------
ዳን_አድማሱ
Dan_admasu
--------------
JOIN & SHARE
@Write_event
@Write_event
@Write_event
--------------
--------------
አደይ አዳዬ እማ ደብተራ ኦሪቷ
ሀዘን ገብቷት ዛሬ ላልቶ መቀነቷ
አስኬማውን ደፍቶ መንጋውን ካልመራ
መምሬ አያስብልም ጥምጣምና ጭራ
ፍሙ ቢንቀለቀል ምን ቢያነደው ንዳድ
ምነው አልሰማ አለ ለገመ ያ ምጣድ
ጋሞ ጪማ አዋቲ ተው ባይ ቢገኝባት
ፍቅር በረታው ልብ ሳር አብርዷል እሳት--------------
ዳን_አድማሱ
Dan_admasu
--------------
JOIN & SHARE
@Write_event
@Write_event
@Write_event
--------------
" ......ተገቢውን ፍርድ ለመስጠት የምትሹ እናንተ ዳኞች ሆይ ...በስጋው ታማኝ ቢሆንም በመንፈስ ሌባ ለሆነ ሰው ምን ፍርድ ትሰጡታላችሁ ?......በስጋው ለሚያርድ በመንፈሱ ግን እርሱ ራሱ ለታረደውስ ምን ቅጣት ትጥሉበታላችሁ ?......እናስ በተግባር አታላይና ጨቋኝ ቢሆንም እርሱ ራሱ የተጨቆነውን የተዋረደውንስ እንደምን ትዳኙታላችሁ ?.....ገና ሳይፈረድባቸው ፀፀታቸው ከመጥፎ ድርጊታቸው በእጅጉ በልጦ የተገኘውንስ እንዴት አድርጋችሁ ነው ቅጣት የምትጥሉባቸው ?.......በአግባቡ እያገለገላችሁት የምትገኙት ያ ህግ በራሱ የሚሰጠው ፍትሀዊ ብይንስ ፀፀት አይደለምን ? እንደዚያም ሆኖ በንፁሃን ላይ ፀፀት ልታሳድሩ ወይም ከጥፋተኞች ልብ ላይ ፀፀት ነቅላችሁ ልታወጡ አይቻላችሁም ። ...." ገፅ ( 38 / 39 )
".....ወዳጆቼ ሆይ በእምነቶችና በባዶ ሐይማኖቶች ለተሞላች ሀገር እዘኑላት ....በጥባጮችን እንደ ጀግና በእልልታ ለምትቀበል ፣ አንፀባራቂ ድል አድራጊዎችን እንደ ለጋስ ለምታሞካሽ ሀገር እዘኑላት ..... መሪው ቀበሮ ፈላስፋው ቀጣፊ ጥበቡም መኮረጅና መለጣጠፍ ለሆነ ህዝብ እዘኑለት ..... አዋቂዎቿ በእድሜ መግፋት ዲዳ ለሆኑባት ፣ ብርቱ ልጆችዋ ገና ከህፃን አልጋ ላይ ላልተነሱላት ሀገር እዘኑላት ..... ግዛቷ ለተበጣጠሰባትና እያንዳንዱ ብጥስጣሽ ራሱን እንደ አንድ ሀገር ለሚቆጥርባት ሀገር እዘኑላት .....
ገፅታዎች ( 153 )
የጠቢባን መንገድ@Write_event
@Write_event
@Write_event
💡ሕይወት በ’የኔ’ እና ‘የኛ’ የምናሳንሰው ነገር የላትም… ከጽንፍ አልባው ምልዓት ላይ በተገለጸልን ልክ የገባንን ሁሉ የእኔ/ኛ አንልም… እኛ ራሳችንን ያንን ምልዓት አይደለን? “You are not a drop in the ocean; you are the entire ocean in a drop” ይላል Rumi
❤️ ይህን ሁለንተና በግላዊነት መያዝ አይቻልም… የኔ ብሎ ማሳነስ አይቻልም… እኛው ራሳችን ሁለንተናውን ነንና ፣ ብዙ የአለማችን እሳቤዎች ከሕይወት በተናጥሎ የመኖርን ቅዠት ይሰብካሉ… ውቅያኖሱን ሆነህ ሳለ የውቅያኖሱን ‘አንድ ጠብታ ወስደህ’ የኔ ማለት ከራስም ያሳንሳል…ከራስህ ተነጥለህ ‘የራስህ’ ሊኖርህ አይችልም።
💡የግዙፍ ውቅያኖስ አካል ነን ፣ከኔ ቤት ላይ የረጨኸው እሳት ከሆነ ነበልባሉ ያንተን ቤት ይነካል ሽቶ ስትረጨኝ የመዓዛው ቅንጣቶች ለአፍንጫህ ውብ ጠረን ይለግሳል ሰው የዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳል ይህን ምስራቃውያኑ Karma ሲሉት ሌሎች ደግሞ Boomerang ይሉታል Boomerang አውስትራሊያኖቹ አቦርጂኒስቶች ከእንጨት የሚሰሩት ደጋን ቅርጽ ያለው የአደን መሳሪያ ሲሆን ወርዋሪው ዘንድ ተመልሶ እንዲመጣ ተደርጎ የሚነደፍ ነው… ለሃሳብ፣ ለስሜትና ድርጊትህ መጠንቀቅ የሚኖርብህ ወላፈኑ ‘ለእኔም’፣ ‘ለእርሷም’፣ ‘ለእነርሱም’ እንደሚተርፍ በማሰብ ነው ምክንያቱም We are all One!
💎በረከት በላይነህ "የመንፈስ ከፍታ" ላይ እንዲህ ይለናል
“የግልህ ወንዝ ስለሌለህ ብቻህን የምትሰራው ድልድይ የለም! የሰማዩ ርቀት፣ የምድሪቱ ስፋት በ’እኛ’ እንጂ በ’እኔ’ አይለካም፡፡ ውዱ ‘እኔ’ ከ’እኛ’ የተሰራው ነውና!”
✍ደምስ ሰይፉ
ውብ አሁን!!❤️@Write_event
@Write_event
@Write_event
የሰማያት ቁጣ!
(መዘክር ግርማ)
መብረቅ ብርሃን ጅራፍህ
ሰማይ ላይ ሲጦፍ ሲኖጋ
ያጮኽከው ሥውር እጅ ሆይ!
ያረ'ከው አፍታ እንዲነጋ
የት እንደወደቀ ባላ'ቅም
ለማን እንደሆን ይህ ቁጣ
ቤቴን ደርምሶ ባይገባም
ከሁሉ እኔን ነው የቀጣ!
ዐይኖቿን ጨፍና – ውበቷን ግን ገልጣ
እንደ መልአክ አምናኝ፣ ጎኔ ተሸጉጣ
ተኝታ የነበር ተነሳች ደንግጣ፡፡
@Write_event
@Write_event
@Write_event
(መዘክር ግርማ)
መብረቅ ብርሃን ጅራፍህ
ሰማይ ላይ ሲጦፍ ሲኖጋ
ያጮኽከው ሥውር እጅ ሆይ!
ያረ'ከው አፍታ እንዲነጋ
የት እንደወደቀ ባላ'ቅም
ለማን እንደሆን ይህ ቁጣ
ቤቴን ደርምሶ ባይገባም
ከሁሉ እኔን ነው የቀጣ!
ዐይኖቿን ጨፍና – ውበቷን ግን ገልጣ
እንደ መልአክ አምናኝ፣ ጎኔ ተሸጉጣ
ተኝታ የነበር ተነሳች ደንግጣ፡፡
@Write_event
@Write_event
@Write_event
አንድዬና አንድ ቀን
(አሌክስ አብርሃም)
አንድ ቀን ያልፋል እያለ
አንድ ነፍስ ስንት አመት ይልፋ፣
አንድ ቀን አይመጣ መስሎት
አንድስ ክንድ ስንት ጉድ ይግፋ...
አንድዬስ ለአንድ ምፅአት
ምነዉ ገደልከን በተስፋ ?
:
''አንድ አይነድ ፍርድም ባንድ አያምር''
ሰዉኛ ብሂል ተርተዉ
ባንድ ክንድ እየደቆሱ፣
ባንድ እሳት አገር ሲያምሱ...
አንድ ሰዉ ይጠይቀዉ ዘንድ
ያንድዬ ምን ይሆን መልሱ?
:
ኮሳሶች ደስ ይበላችሁ
ካንድ ብርቱ ልትበረቱ፣
ሁለት ኮሳሳ ይሻላል
ብሎ ብያፀናን ተረቱ፣
ሁለት ኮሳሶች በርትተዉ
ስለ አንድነት ቢዘምቱ፣
አንዱ አንዱን እያደባየ
መልሶ ያዉ አንድ ብርቱ!
:
ምንድነዉ አንድ አንቆ መጮህ
አንድዬ አንድ በለና፣
አንድ ወንዝ ስንቴ እንሻገር
ጠብ ለማይል መና...
:
ሕዝብህ ሁለት ባላ ተክሎ፣
አንዱ ሲቀል በአንዱ
ተፍገምግሞ ተንጠልጥሎ...
''አንድዬ አንተ ታዉቃለህ''
እያለህ ሲኖር በዘዴ፣
ላንዳንዶች እንደምንለዉ
''ት'ግስትህ አልበዛም እንዴ''
:
አንድ ለናቱ ለመባል የእናቱን ልጆች ጨርሶ፣
አንድ አይፈርድ ተረት ቢያሰማን
የአንድ ዓይን እንባ አልቅሶ...
እኛም አንድ ጸሎት አለን
አንድዬ አንዴ ስማና...
:
አንድነት እየሰበኩን-አንድነት የሚቀፋቸዉ ፣
አንድዬ አንድ አርገንና...አንድ ቀን አንድ በላቸዉ !!
:
(አንፈርስም አንታደስም ገፅ ፩፻፸፱)
@Write_event
@Write_event
@Write_event
(አሌክስ አብርሃም)
አንድ ቀን ያልፋል እያለ
አንድ ነፍስ ስንት አመት ይልፋ፣
አንድ ቀን አይመጣ መስሎት
አንድስ ክንድ ስንት ጉድ ይግፋ...
አንድዬስ ለአንድ ምፅአት
ምነዉ ገደልከን በተስፋ ?
:
''አንድ አይነድ ፍርድም ባንድ አያምር''
ሰዉኛ ብሂል ተርተዉ
ባንድ ክንድ እየደቆሱ፣
ባንድ እሳት አገር ሲያምሱ...
አንድ ሰዉ ይጠይቀዉ ዘንድ
ያንድዬ ምን ይሆን መልሱ?
:
ኮሳሶች ደስ ይበላችሁ
ካንድ ብርቱ ልትበረቱ፣
ሁለት ኮሳሳ ይሻላል
ብሎ ብያፀናን ተረቱ፣
ሁለት ኮሳሶች በርትተዉ
ስለ አንድነት ቢዘምቱ፣
አንዱ አንዱን እያደባየ
መልሶ ያዉ አንድ ብርቱ!
:
ምንድነዉ አንድ አንቆ መጮህ
አንድዬ አንድ በለና፣
አንድ ወንዝ ስንቴ እንሻገር
ጠብ ለማይል መና...
:
ሕዝብህ ሁለት ባላ ተክሎ፣
አንዱ ሲቀል በአንዱ
ተፍገምግሞ ተንጠልጥሎ...
''አንድዬ አንተ ታዉቃለህ''
እያለህ ሲኖር በዘዴ፣
ላንዳንዶች እንደምንለዉ
''ት'ግስትህ አልበዛም እንዴ''
:
አንድ ለናቱ ለመባል የእናቱን ልጆች ጨርሶ፣
አንድ አይፈርድ ተረት ቢያሰማን
የአንድ ዓይን እንባ አልቅሶ...
እኛም አንድ ጸሎት አለን
አንድዬ አንዴ ስማና...
:
አንድነት እየሰበኩን-አንድነት የሚቀፋቸዉ ፣
አንድዬ አንድ አርገንና...አንድ ቀን አንድ በላቸዉ !!
:
(አንፈርስም አንታደስም ገፅ ፩፻፸፱)
@Write_event
@Write_event
@Write_event
አራት ዓይነት እብደት...
ኤፍሬም ሥዩም ( ኑ ግድግዳ እናፍርስ!)
፩
ብቸኝነት ብርዱ ገላህን ቀዝቅዞ
ከሰው መሀል አንተን ለብቻህ ሰቅዞ
መጠየቅ ስትጀምር ...
ለምን!...እንዴት?...ስትል?
ጥያቄህ በራሱ እብደት ነው የሚባል
ኡፍፍፍ...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
፪
መጠየቅ ሰልችቶህ ከሕዝቦች ስትርቅ
በራስህ ዓለም ላይ ህሊናህ ሲራቀቅ
አፍህ ዝም ባለ
እብድ መባል አለ።
ኤጭ!...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
፫
የሕዝብ ሁሉ ሀሳብ የእብደት ሲመስልህ
ያንተ አሳብ የእውነት....
እውነት እንደሆነ ውስጥህን ሲሰማህ
እብዱ ትባላለህ።
ኤዲያ!...
አውቆ የሚተኛ ሕዝብ መሀል ነቅተን፣
አቦ ተሰቃየን!
፬
ዓለሙም እብድ ነው!
ግና ያለም እብደት ካንተ የሚለየው
አንተ የምታብደው ለዓለም ስትል ነው
ዓለሙ ያበደው አንተን ሊያሳብድ ነው።
ወገን ተሰቃየን!
አውቆ በተኛ አቋመ ቢስ መሐል...
ለብቻችን ነቅተን
አወይ ተሰቃየን!!
.....
@Write_event
@Write_event
@Write_event
ኤፍሬም ሥዩም ( ኑ ግድግዳ እናፍርስ!)
፩
ብቸኝነት ብርዱ ገላህን ቀዝቅዞ
ከሰው መሀል አንተን ለብቻህ ሰቅዞ
መጠየቅ ስትጀምር ...
ለምን!...እንዴት?...ስትል?
ጥያቄህ በራሱ እብደት ነው የሚባል
ኡፍፍፍ...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
፪
መጠየቅ ሰልችቶህ ከሕዝቦች ስትርቅ
በራስህ ዓለም ላይ ህሊናህ ሲራቀቅ
አፍህ ዝም ባለ
እብድ መባል አለ።
ኤጭ!...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!
፫
የሕዝብ ሁሉ ሀሳብ የእብደት ሲመስልህ
ያንተ አሳብ የእውነት....
እውነት እንደሆነ ውስጥህን ሲሰማህ
እብዱ ትባላለህ።
ኤዲያ!...
አውቆ የሚተኛ ሕዝብ መሀል ነቅተን፣
አቦ ተሰቃየን!
፬
ዓለሙም እብድ ነው!
ግና ያለም እብደት ካንተ የሚለየው
አንተ የምታብደው ለዓለም ስትል ነው
ዓለሙ ያበደው አንተን ሊያሳብድ ነው።
ወገን ተሰቃየን!
አውቆ በተኛ አቋመ ቢስ መሐል...
ለብቻችን ነቅተን
አወይ ተሰቃየን!!
.....
@Write_event
@Write_event
@Write_event
(በረከት በላይነህ)
....
አብዬ ያልታደለ
'መልካም አስብ' ሲባል 'አንባቢ ነኝ' አለ
እምዬ ቀለለች
'የዉበቴ ምስጢር ቀለም ነዉ' ትላለች
:
የሃሳብህን ስብራት
በዉሸት ለማሸት
ስታወራ ዉለህ ስትቀባጥር ማምሸት
የመልክሽን ህመም
በቀለም ለማከም
መዳፍሽ እስኪዝል መስታወት ፊት መድከም
:
:
ምን ልልሽ መሰለሽ
'መልክ ስጠኝ እንጂ...' ብለሽ አተርቺ
በቀለም ይመጣል - በመቀባት በርቺ
:
ምን ልልህ መሰለህ
ተርት ተተርተረዉ - ማንንም አትፍራ
'ሙሉ ሰዉ' ዝም ይላል - አንተ ስታወራ. . . . .
:
:
ባንተና በሷ ንግስ - አማካሪ አያሻ
የእውነት ጅማሬ ነዉ - የዉሸት መጨረሻ፡፡
:
ሊመክርህ ያለዉን - ያኔ ታገኛለህ
ወይ እዉነት ጋር ስትደርስ - ወይ ሲዋሽ ታያለህ፡፡@Write_event
@Write_event
@Write_event
የእኔ ውብ ከተማ
(በዓሉ ግርማ)
ሕንጻ መች ሆነና ፣ የድንጋይ ክምር
የእኔ ውብ ከተማ
መንገድ መች ሆነና ፣ የድንጋይ አጥር
የእኔ ውብ ከተማ ፣ የእኔ ውብ አገር
የሰው ልጅ ልብ ነው
የሌለው ዳርቻ ፣ የሌለው ድንበር
ሕንጻው ምን ቢረዝም ፣ ምን ቢጸዳ ቤቱ
መንገዱ ቢሰፋ ፣ ቢንጣለል አስፋልቱ
ሰው ሰው ካልሸተተ ፣ ምንድን ነው ውበቱ ? @Write_event
@Write_event
@Write_event
ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም ፤ የመሰለች ልጅ!
(ነብይ መኮንን)
ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም
ከመሰለች ልጅ ፊት ለፊት
ተቀምጫለሁ፡፡ __ ቡና ቤት፡፡
መልኳ ጉራማይሌ ነው
በባለቀለም ጀምሮ በጥቁርና ነጭ የሚያልቅ
... የድሮ ፊልም የሚመስል።
ስትስቅ ፤ ቤት አትመታም ፤
ስታለቅስ ፤ ዜማ የላትም ፤
ስታዝ ፤ ቃላት አትመርጥም።
ማኪያቶ ስትፈልግ፦
«ጎምዘዝ ያለ መኪያቶ
ስኳሩ እንደ ጠዋት ህልም፣
... እየጣመ ‘ሚያልቅ» ትላለች፡፡
ወይም ደግሞ፤
«እስኪ አንድ ቢራ ስጠኝ እንደ ዕንባ የቀዘቀዘ»
ወይም «አንድ ጎርደን ደብል
ካልቀዘቀዘ በረዶና ከሎሚ ዝልዝል ጋር…
ምነው አኮረፍክ?
የሚያስቅ ነገር ተናገርኩ?»
ዳሩ ቦዮቹም ያቋታል፡፡ ምንም አይናገሯትም፡፡
የጨዋታዋ ለዛ መብዛት፣ ለዛ-ቢስ ያ’ረጋታል
ስለራሷ ስታወራም… ነገር ታረዝም ታረዝምና
«ውይ እስቲ አንዴ አዳምጠኝ፤
... ዓመት አላወራ!!» ትልና
ከዛ ትዘበዝባለች ፣ ደሞ ሌላ ዓመት ጨምራ።
ከቶም ወደዚህ ቡና ቤት፣ መመላለስ ከጀመርኩ
እኔ ራሴ እንኳ በሷ ወግ፤ ዘልዛላ ርዝመት ሳቢያ
... ሁለት ሦስቴ አርጅቻለሁ፡፡
አንድ ቀን ግን ጨክኜ፦
«ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም!
ያን ከማንበብ ይሻላል! ፣ ገዳም ገብቶ መጋደም!»
አልኳትና ሂሳብ ከፍዬ፤ ራመድ ... ራመድ ስል
ያ! የማውቀው ፌዘኛ ቦይ፣ ወደኔ መጥቶ እንደግዳጅ
«ያቺ ያልተጨረሰች ቀሽም ግጥም፣
... የመሰለችው ሴት ልጅ፤
‘ ታኮዬ ይበላሻል እንጂ፣ እሄድብህ ነበር በልልኝ ! ’
... አለችኝ ጋሼ» አለኝ፡፡
እኔም ነገሩ ገርሞኝ
«ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም ነው ያልከው?
ኬት ሰማኸው?!» ብዬ ብለው
«ጋሼ፤ ከሷ! ከራሷ አፍ ነው፡፡
ራሷ! ራሷን የምትጠራው፣ እንዲሁ እያለችኮ ነው!»
«ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም፣»
... ላንተ ምን ስሜት ይሰጥሀል?» ብዬ ብለው
«ንገረኝ ካሉስ ጋሼ፤... የላይኛው መስመር በሷ
የታችኛው መስመር በርሶ
የተጻፈ ይመስለኛል።!?
አለ አይደለ ፤ የማያልቅ ዘልዛላ ግጥም
ላፍ የማይጥም … ለኑሮ እማይጠቅም።
... ግን ጋሼ አንድ ነገር ልንገርዎት
እሷስ ተጀምራ ያልተጨረሰች ቀሽም ግጥም ሆና ነው፤
ገና ያልተጀመረ፤ ስንት ቀሽም ግጥም አለ መሰሎት?»
አለኝና፤
ከአግራሞቴ ጋራ ጥሎኝ፣ ወደ ደንበኛው በረረ እኔም፤
ያልተጨረሰችውን ቀሽም ግጥም ልጅ!
... ልታልቅ አንድ - አሙስ የቀራት
እራፊ ጠቀሳ ጠቀስኳት፡፡
ከዚያም ያልተገረዘ ፈገግታ እያሳየኋት፤
እንዳላለቀ የገጠር መንገድ
… እየተንገዳገድኩ አስፋልቱ ጋ ስደርስ፣
ቡችላዬን አገኘኋት።
የዚያችን!
ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም ልጅ ነገር
ለሸውራራዋ ድንክ ውሻዬ ነገርኳት!
እሷም! «O my God!
ምነው መጀመሪያውኑ ሳትጻፍ ብትቀር!
እጸሐፊው አንጎል ውስጥ፣
አርፎ መቀመጥ ማንን ገደለ?!»
አለች፡፡!!
@Write_event
@Write_event
የገጣሚ፦ ነብይ መኮንን "ስውር ስፌት" ከተሰኘው የግጥም መድብል ላይ የተወሰደ
@Write_event
(ነብይ መኮንን)
ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም
ከመሰለች ልጅ ፊት ለፊት
ተቀምጫለሁ፡፡ __ ቡና ቤት፡፡
መልኳ ጉራማይሌ ነው
በባለቀለም ጀምሮ በጥቁርና ነጭ የሚያልቅ
... የድሮ ፊልም የሚመስል።
ስትስቅ ፤ ቤት አትመታም ፤
ስታለቅስ ፤ ዜማ የላትም ፤
ስታዝ ፤ ቃላት አትመርጥም።
ማኪያቶ ስትፈልግ፦
«ጎምዘዝ ያለ መኪያቶ
ስኳሩ እንደ ጠዋት ህልም፣
... እየጣመ ‘ሚያልቅ» ትላለች፡፡
ወይም ደግሞ፤
«እስኪ አንድ ቢራ ስጠኝ እንደ ዕንባ የቀዘቀዘ»
ወይም «አንድ ጎርደን ደብል
ካልቀዘቀዘ በረዶና ከሎሚ ዝልዝል ጋር…
ምነው አኮረፍክ?
የሚያስቅ ነገር ተናገርኩ?»
ዳሩ ቦዮቹም ያቋታል፡፡ ምንም አይናገሯትም፡፡
የጨዋታዋ ለዛ መብዛት፣ ለዛ-ቢስ ያ’ረጋታል
ስለራሷ ስታወራም… ነገር ታረዝም ታረዝምና
«ውይ እስቲ አንዴ አዳምጠኝ፤
... ዓመት አላወራ!!» ትልና
ከዛ ትዘበዝባለች ፣ ደሞ ሌላ ዓመት ጨምራ።
ከቶም ወደዚህ ቡና ቤት፣ መመላለስ ከጀመርኩ
እኔ ራሴ እንኳ በሷ ወግ፤ ዘልዛላ ርዝመት ሳቢያ
... ሁለት ሦስቴ አርጅቻለሁ፡፡
አንድ ቀን ግን ጨክኜ፦
«ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም!
ያን ከማንበብ ይሻላል! ፣ ገዳም ገብቶ መጋደም!»
አልኳትና ሂሳብ ከፍዬ፤ ራመድ ... ራመድ ስል
ያ! የማውቀው ፌዘኛ ቦይ፣ ወደኔ መጥቶ እንደግዳጅ
«ያቺ ያልተጨረሰች ቀሽም ግጥም፣
... የመሰለችው ሴት ልጅ፤
‘ ታኮዬ ይበላሻል እንጂ፣ እሄድብህ ነበር በልልኝ ! ’
... አለችኝ ጋሼ» አለኝ፡፡
እኔም ነገሩ ገርሞኝ
«ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም ነው ያልከው?
ኬት ሰማኸው?!» ብዬ ብለው
«ጋሼ፤ ከሷ! ከራሷ አፍ ነው፡፡
ራሷ! ራሷን የምትጠራው፣ እንዲሁ እያለችኮ ነው!»
«ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም፣»
... ላንተ ምን ስሜት ይሰጥሀል?» ብዬ ብለው
«ንገረኝ ካሉስ ጋሼ፤... የላይኛው መስመር በሷ
የታችኛው መስመር በርሶ
የተጻፈ ይመስለኛል።!?
አለ አይደለ ፤ የማያልቅ ዘልዛላ ግጥም
ላፍ የማይጥም … ለኑሮ እማይጠቅም።
... ግን ጋሼ አንድ ነገር ልንገርዎት
እሷስ ተጀምራ ያልተጨረሰች ቀሽም ግጥም ሆና ነው፤
ገና ያልተጀመረ፤ ስንት ቀሽም ግጥም አለ መሰሎት?»
አለኝና፤
ከአግራሞቴ ጋራ ጥሎኝ፣ ወደ ደንበኛው በረረ እኔም፤
ያልተጨረሰችውን ቀሽም ግጥም ልጅ!
... ልታልቅ አንድ - አሙስ የቀራት
እራፊ ጠቀሳ ጠቀስኳት፡፡
ከዚያም ያልተገረዘ ፈገግታ እያሳየኋት፤
እንዳላለቀ የገጠር መንገድ
… እየተንገዳገድኩ አስፋልቱ ጋ ስደርስ፣
ቡችላዬን አገኘኋት።
የዚያችን!
ያልተጨረሰ ቀሽም ግጥም ልጅ ነገር
ለሸውራራዋ ድንክ ውሻዬ ነገርኳት!
እሷም! «O my God!
ምነው መጀመሪያውኑ ሳትጻፍ ብትቀር!
እጸሐፊው አንጎል ውስጥ፣
አርፎ መቀመጥ ማንን ገደለ?!»
አለች፡፡!!
@Write_event
@Write_event
የገጣሚ፦ ነብይ መኮንን "ስውር ስፌት" ከተሰኘው የግጥም መድብል ላይ የተወሰደ
@Write_event
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በአሁኑ ወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደደው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ለማረጋገጥ ተችሏል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነ ሲሆን በህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ለማረጋገጥ መቻሉን አሳውቋል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት ነበረ።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ፦
- ወጣት በ97፣
- ወንድሜ ያዕቆብ፣
- ላውንድሪ ቦይ፣
- ማርትሬዛ፣
- ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣
- ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣
- አንድ ሁለት ፣
- ብር ርርር፣
- ወደው አይሰርቁ፣
- ወፌ ቆመች፣
- እንደ ቀልድ ፣
- ወቶ አደር ፣
- አባት ሀገር
- የሞግዚቷ ልጆች፣
- ይዋጣልን ፣
- ዋሻው፣
- ወሬ ነጋሪ እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል።
@tikvahethiopia
በተለያዩ የሀገራችን ፊልሞች ላይ በድንቅ ብቃት በመተወን በተለይ ደግሞ በአሁኑ ወጣቶች ዘንድ እጅግ የሚወደደው አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን ለማረጋገጥ ተችሏል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) አርባ ያህል ፊልሞች ላይ የተወነ ሲሆን በህመም ምክንያት ህይወቱ ማለፉን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) ከአርቲስቱ የቅርብ ሰዎች ለማረጋገጥ መቻሉን አሳውቋል።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ የአንድ ልጅ አባት ነበረ።
አርቲስት ታሪኩ ብርሃኑ (ባባ) ፦
- ወጣት በ97፣
- ወንድሜ ያዕቆብ፣
- ላውንድሪ ቦይ፣
- ማርትሬዛ፣
- ይመችሽ-የአራዳ ልጅ 2 ፣
- ሞኙ የአራዳ ልጅ 4፣
- አንድ ሁለት ፣
- ብር ርርር፣
- ወደው አይሰርቁ፣
- ወፌ ቆመች፣
- እንደ ቀልድ ፣
- ወቶ አደር ፣
- አባት ሀገር
- የሞግዚቷ ልጆች፣
- ይዋጣልን ፣
- ዋሻው፣
- ወሬ ነጋሪ እና ሌሎችም ፊልሞች ላይ ተውኗል።
@tikvahethiopia