ቃላዊ
346 subscribers
38 photos
5 videos
1 file
121 links
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።

ግጥም ለመላክ
@Melikitegna_bot
Download Telegram
ቅምሻ 😍

በዚህ ምድር ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ (ያለምንም Qualification) ጥሩ የሆነው ነገር ምንድ ነው ?" ሲል ይጠይቃል ኢማኑኤል ካንት የሞራል ፍልስፍናውን ሲጀምር ። ለዚህ ጥያቄ ካንት እራሱ መልሱን እንዲ ሲል ይሰጠናል ።

#ገንዘብ!? አይደለም ፤ ገንዘብ ጥሩ የሚሆነው ለጥሩ ነገር ስናውለው እንጂ ገንዘብ በራሱ በተፈጥሮ ባህሪው ጥሩነት የለውም ።
# ዕውቀት!? ዕውቀት አይደለም ፤ እውቀት ጥሩ የሚሆነው መልካም ሰው ሲያገኝ ነው ።

#ጉብዝና(Courage)!? እሱም አይደለም ፤ ጉብዝና ጥሩ የሚሆነው ለጥሩ ዓላማ ሲሆን ነው ። ለምሳሌ ሂትለር ጎበዝ (Couragous) ነው ። ሆኖም ግን ፣ የእሱ ጉብዝና መጥፎ #ጉብዝና ነው ።
# እና ታዲያ ምንድ ነው? ለካንት መልሱ አንድ ነው~በዚህ ዓለም ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በራሱ መልካም የሆነው ነገር አንድ ብቻ ነው ፤ እሱም "በጎነት ወይም ቅንነት /Good Will" ነው። (Kant 1987 ፡ 7)
ዕውቀት ፣ በጎነትና ጉብዝና ቅንነት ላይ ካላረፉ አደገኛ ይሆናል ። የፍልስፍና ትምህርት ።

#ቅን እንሁን-

@write_event
ለፈገግታ 😂

" ነገራችንን "አትንሳን
(አሌክስ አብርሃም)

ወታደራዊ ሰላምታ ሰጥቻለሁ! ! እኔ
ጓድ ኮሮኔል መንግስቱ ሃይለማሪያም ብሆንእና በአሁኑ ሰአት
ኢትዮጲያን የማስተዳድረው እኔ ብሆን ኖሮ የሚከተሉት አብዮታዊ እርምጃዎች እወስድ
ነበር,,,,,,የእናተንም ብትነግሩኝ ደስ ይለኛል!!

☹️1ኛ, መሰለ መንግስቱ የሚባለውን ሰውየ በክብር አባርሬ ያንን
ቢራ የወለደው የሬዲዮ ጣቢያ ፍቅር ይልቃልና ገነነ መኩሪያ
(ሊብሮ) በጋራ እንዲያስተዳድሩት እሰጥ ነበር! !
2ኛ, " አቤ ከቤ ከአሰላ " የሚባለውን ሰውየ የአምስት አመት
ስልክ ያለመደወል መአቀብ እጥልበት ነበር! !

3ኛ,....

4ኛ, ለቀጣይ ሁለት አመታት የአማርኛ ፊልሞች እንዳይሰሩ እገዳ እጥል ነበር!የመድረክ
ቲያትሮችም በእጥፍ እንዲጨምሩ ቀጭን ትእዛዝ አስተላልፍ ነበር
5ኛ, ማንኛውም የሬዲዮ ጣቢያ የስፖርት ዜናም ይሁን ትንታኔ
በቀን ከ5 ደይቃ ለማይበልጥ ጊዜ ብቻ እንዲያቀርብ እንዲሁም በቀን ከ3 ዘፈኖች በላይ
እንዳያቀርብ አስገድድ ነበር!
6ኛ, በኢትዮጲያ ጥራታቸውን የጠበቁ ግዙፍ ( በመቀበል
አቅማቸውም በትምመህርት ጥራታቸውም) 10 ዮኒቨርስቲዎች ብቻ በማስቀረት ሌሎቹን
የሱሰኞች ማገገሚያ እንዲሆኑ አዝ ነበር!
7ኛ, ሁሉም (( ሴቶች )) ከአምስተኛ ክፍል ጀምሮ በግድ
ወታደራዊ ስልጠና እንዲወስደዱ እና ( ሴቶች ከሄዱ ወንዱም
እየተጋፋ ይገባል:)) ሁሉም ዜጋ ቢያንስ በመጀመሪያና በሁለተኛ ደረጃ ት/ ቤቶች ቆይታው
ክላሲክ የሚባሉ የአገር ውስጥም ይሁኑ የውጭ መፅሃፍትን እንዲያነብ አስገድድ ነበር,,,
ግዙፍ የመፃህፍት ማከፋፈያዎችንም እከፍት ነበር
8ኛ, አዲሱን የባቡር ሃዲድ ድልድይ ምናምን አስፈርሸ አዲስ
አበባን እጅግ በሰፋፊ መንገዶች እሞላት ነበር
9ኛ ከዚህ በኋላ አዲስ አበባ ላይ ከአራት ፎቅ በላይ ህንፃ
እንዳይሰራ አዝ ነበር,,,, ባለመስተዋት ህንፃዎችማ ድርሽ
አይሏትም!
10ኛ ቢራና የአልኮል መጠጦች ላይ ከፍተኛ ግብር በመጣል ቢራ መጠጣትንም
መጥመቅንም በአገራችን እጅግ በጣም ውዱ ነገር አደርገው ነበር እንዲሁም
11ኛ, ማታ ማታ በቲቪ በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ከሌለ በስተቀር
ዜና እንዳይነበብ አደርግ ነበር !!
ከወራደራዊ ሰላምታ ጋር ገጭ!!

@write_event
@write_event
@write_event
"እጅህ የሚያገኘውን ስራ ሁሉ በሙሉ ሀይልህ ስራው ፣ልትሄድበት ባለው መቃብር ውስጥ መስራትም ሆነ ማቀድም የለምና"።

⚜️ ጠቢቡ ሰለሞን⚜️

@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
😂😂ለፈገግታ😂😂

‹‹ቲማቲም ወርውሮ ትላንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው››
(አሌክስ አብርሃም)
🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅
የሆነ ጊዜ ሃላፊየ ወክለውኝ ሃላፊ ሁኘ ስሰራ . . . ሁለት ወጣቶች ቢሮየ መጡ . . .💃🕺
ሴትና ወንድ ናቸው ! ሁለቱም መስሪያ ቤቴ አካባቢ ካለ
የሃብታም ልጆች ትምህርት🏢 ቤት ነበር አመጣጣቸው . . .
የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪወች ሲሆኑ የሴቷ አለባበስ ያለማጋነን የኦስካር እጩ
አስመስሏታል . . .በዛ ላይ ኑሮ ምችት ያላት ቆንጆ . . .በእንግሊዝኛ አፏን ስለፈታች ነው መሰል አማረኛ ገደል ሁኖባት ቃላትን እየፈለገች ነው
የምትናገረው …ወንዱም እንደልጅቱ ባይሆንም ሽክ ብሏል ….

👱‍♀‹‹ የመጣነው ላሰብነው ፕሮግራም ስፖ….ንሰር እንድትሆኑን ነው ››
አለች
ልጅቱ ብዙ ጊዜ ወደቢሮ ብቅ እያሉ ስፖንሰርየሚጠይቁን የቀበሌ
የወጣቶች ..የሴቶች …የምንትስ ሰወች ወይም የተቸገሩ ሚስኪኖች ስለነበሩ ‹‹ስፖንሰር ›› የሚለው ፅንሰሃሳቡ ወይ የድሆች ወይ
የፖለቲከኞች እየመሰለኝ ከመጣ ቆይቷል . . . እነዚህ ምቾት ያሰቃያቸው ልጆች እንዴት ‹‹ስፖንሰር ሁኑን ›› እንዳሉ ገርሞኝ ጉደዩን ጠየኩ

👱‍♀‹‹ ዩ ኖ . . . በትምህርት ቤታችን ‹የቲማቲም ቀን🍅› ልናከብር አስበናል . . . ዛት ማች ብዙ ብር ምናምን የሚፈልግ አይደለም …››

👨‍💼‹‹የቲማቲም ቀን 🍅? ›› ስል ጠየኩ

👱‍♀‹‹ያ …በቃ ተማወች የሆነ ሰአት ይወስኑና ግቢ ውስጥ ቲማቲም መወራወር ምናምን በጣም ያዝናናል ...ውጭ ምናምን የተለመደ ነው
..እናም በጎ ነገሮችን ወደሃገራችን ብናስገባ ቀስ እያለ ከትምህርት ቤት ወደሁሉም ትምህርት ቤቶች ከዛ በአገር ደረጃ በቃ የቲማቲም ቀን
ተብሎ በአመት አንዴ ይከበራል . . . ››
ሁለቱም ገርመውኝ ተራ በተራ እያየኋቸው

👨‍💼‹‹እና ቲማቲም🍅 እየተወራወራችሁ ቀኑን ልታከብሩ ነው . . ?>>

👱‍♀<<YAp>>

👨‍💼<<.አላማው ግን ምንድነው ?››

👱‹‹ ጀስት ፈን! …እና ደግሞ አለ አይደል ሌላው <ወርል ድ> በፋሚን ድሮውውት ምናምን ነው ኢትዮጲያን የሚያውቃት ..የቲማቲም ቀን
በማክበር ግን አገራችን ጀስት ከእርሃብ እንደወጣች ለማሳየት … በዛ ላይ ቦንብ ምናምን ድንጋይ የሚወረወርበት ጊዜ እንዳለፈና ፒስ
መሆናችንን ለማሳየት ››
አለ ወንዱ ልጅ

👱‍♀‹‹በተጨማሪም ›› አለች ሴቷ ‹‹በተጨማሪም አሁን ያለንን የአበላል ሃቢት አለ አይደል ፒፕሉ ስጋ ቁርጥ ምናምን ያበዛል .. ይሄ ለብዙ በሽታ
ስለሚያጋልጥ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲመገብ ፕሮሞት ማድረግም ይቻላል
›› ስትል አብራራችልኝ !

👨‍💼ጎበዝ ተበላን ! እነዚህ የሃብታም ትምህርት ቤቶች ባለራእይ ትውልድ እያመረቱ ነው . . . ትክዝ ብየ አየኋቸው . . . ደመወዝ ጨምሩልኝ እያለ
ሁለት ወር ቢሮየ የተመላለሰው የአራት ልጆች አባት ጋሽ ወጋየሁ ቢሮየ በር ላይ ቁሞ ይታየኛል ልጆቹ እስኪወጡ እየጠበቀ . . . ሁለት መቶ
ብር ጨምሩልኝ ብሎ ሁለት ገፅ ማመልከቻ ፅፏል …ሚስኪን የቲማቲም ቀን ሲከበር ይሄ ሰውየ ‹‹የአበላል ሃቢቱን ያስተካክል ይሆን ? ››
እላለሁ . . .

👱‍♀‹‹ አስር ሽ ብር ምናምን ስፖንሰር ብትሆኑን . . . ›› ልጅቱ ቀጥላለች . . .


እኔም በዓሉ ላይ ብገኝ እና ቲማቲም እነዚህ ልጆች ላይ እንዲሁም መምህራኖቻቸው ላይ ብወረውር ብየ ተመኘሁ ...እና በተለይ
ወላጆቻቸው ላይ ....ግን እኔ የምወረውረው ቲማቲም በጣሳ የታሸገ መሆን አለበት . . . ግንባር ግንባራቸውን !
ቲማቲም ወርውሮ ትላንትና አንድ ሰው
አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው
ደነገጥኩ አይቸ ሲንዠቀዠቅ ደሙ
በጣሳ ውስጥ ነበር ለካስ ቲማቲሙ …..እንዲል ገጣሚው !
*
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
*
ማንም ሰው በዛ ቦታ ቢሆን ተመሣሣዩን ላለማድረጉ በፍፁም ታማኝነት ራሱን እስካልጠየቀ ድረስ መፍረድ የለበትም!
            -- Viktor Frankl --

JOIN US 🙏
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
እምነት - ክህደት - እውነት
┈┈┈•✦•┈┈┈
ኤፍሬም ስዩም
'
የምናምን ዕለት
ፀሐይ ትዞራለች
ባስራ-ሁለቱ መስኮት ገብታ ትወጣለች

የምንጠይቅ ወራት
መሬት ትዞራለች
ያማኝን ልቦና.. ሽፍታ ታደርጋለች

በገጣሚ ምናብ
ከንቱ የ'ምነት ዓይን ከንቱ ፍልስፍና
ሰማይ ነው የሚዞረው። ...
ምክንያቱም..
የትላንቱን ኮከብ ከትላንቱ ቦታው
ዛሬ ላይ መች አየው? ...
════════
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
════════
ኤፍሬም ስዩም

ጊ ዜ
┈✦┈
እግዜር
በምድራችን የተከላት
ጊዜ የሚሏት - ጽጌረዳ
ገና እንኳን ሳታብብ ገና ሳትፈነዳ
ጨለማዋ እሾህ
ጨክኖ ቢወጋት
ወግቶ ቢያሸንፋት
የልቧን አወራች
እውነት ተናገረች ...
ነገ በማለዳ ... ዛሬ ሟች ነኝ አለች።
════════
📓 ኑ ግድግዳ እናፍርስ
join
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
ውዴ!
ሂድ ባልሽኝ መንገድ
ቃልሽን አክብሬ ከፊትሽ ሄጃለሁ፤
ግን
የመውደዴን ቅኔ ለልብሽ ትቻለሁ ፤
እናም አንቺ
ለቅኔው ፍቺ ፈልገሽ፣
ሂድ ባልሽኝ መንገድ ና ያልሽኝ ለታ፣
ከመንገድ ቆሜያለሁ
ሌላ ቅኔ አግኝቼ ቅኔሽን ሳልፈታ።

==========
መላኩ ደምሴ
ከ"ገላ ና ገላ' የግጥም መድብል መፅሐፍ
2013
==========
https://t.me/write_event
ዝሜን እጮኻለሁ
============
ቃል እስከሚያልቅብኝ
ቃልን እስክኾነው...
የምጮኸው ኹሉ ፣ ታላቅ ጥሞና ነው።



=======
ዲበኩሉ ጌታ
ከ"ነፍስ ቦታ"
========

JOIN & SHARE

@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
ቅኝት
____
አንድ ነው ክራሩ...
የጅማት ነው ክሩ...
የሚወጣው ዜማ ለየቅል የሆነው
ቅኝቱን ስንቃኝ...
ያንተ አንቺ ሆዬ የኔ ትዝታ ነው።

========
በረከት አበበ
ከ"ሰው ከሆሳዕና እስከ ስቅለት " የግጥም መድብል።
___

JOIN & SHARE
___
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
በሁለት ስሜት መሃል ፣ የተውሽኝ አግለሽ ፣
እንደ ጌታ ምጽአት ፣ "ብቻ ጠብቅ" ብለሽ ፣
ያልሽኝን ሰምቼ ፣ አለሁ እያነሱ ጋጠጥኹ፣
ያንቺን መምጣት ሳይኾን
የኔን ተስፋ መቁረጥ ፣ በቁሜ እየጠበቀኹ።

__________
ኤልያስ ሽታኹን
__________
ከ"ርዕስ የለውም " ግጥም መድብል
__________

JOIN & SHARE

__________
@Write_event
@Write_event
@Write_event
__________
እንዴት እንዴት ፣

እንዴት እችላለሁ
ከቅኝትሽ መውጣት
ከፍ ቢልም
ዝቅ ቢልም
ሸሽቼ ማልሸሸው
ወጥቼ የማልወጣው
ሁሉም ቅኝትሽ ነው።

_____________
አሸናፊ ተሾመ
ከ"ካፊያ ሆኖ ቀረ" የግጥም መድብል

____________

JOIN & SHARE
@Write_event
@Write_event
@Write_event
___________
"ላይለ ኩሉ"
--------------
አደይ አዳዬ እማ ደብተራ ኦሪቷ
ሀዘን ገብቷት ዛሬ ላልቶ መቀነቷ

አስኬማውን ደፍቶ መንጋውን ካልመራ
መምሬ አያስብልም ጥምጣምና ጭራ

ፍሙ ቢንቀለቀል ምን ቢያነደው ንዳድ
ምነው አልሰማ አለ ለገመ ያ ምጣድ

ጋሞ ጪማ አዋቲ ተው ባይ ቢገኝባት
ፍቅር በረታው ልብ ሳር አብርዷል እሳት

--------------
ዳን_አድማሱ
Dan_admasu

--------------
JOIN & SHARE

@Write_event
@Write_event
@Write_event
--------------
" ......ተገቢውን ፍርድ ለመስጠት የምትሹ እናንተ ዳኞች ሆይ ...በስጋው ታማኝ ቢሆንም በመንፈስ ሌባ ለሆነ ሰው ምን ፍርድ ትሰጡታላችሁ ?......በስጋው ለሚያርድ በመንፈሱ ግን እርሱ ራሱ ለታረደውስ ምን ቅጣት ትጥሉበታላችሁ ?......እናስ በተግባር አታላይና ጨቋኝ ቢሆንም እርሱ ራሱ የተጨቆነውን የተዋረደውንስ እንደምን ትዳኙታላችሁ ?.....ገና ሳይፈረድባቸው ፀፀታቸው ከመጥፎ ድርጊታቸው በእጅጉ በልጦ የተገኘውንስ እንዴት አድርጋችሁ ነው ቅጣት የምትጥሉባቸው ?.......በአግባቡ እያገለገላችሁት የምትገኙት ያ ህግ በራሱ የሚሰጠው ፍትሀዊ ብይንስ ፀፀት አይደለምን ? እንደዚያም ሆኖ በንፁሃን ላይ ፀፀት ልታሳድሩ ወይም ከጥፋተኞች ልብ ላይ ፀፀት ነቅላችሁ ልታወጡ አይቻላችሁም ። ...." ገፅ ( 38 / 39 )

".....ወዳጆቼ ሆይ በእምነቶችና በባዶ ሐይማኖቶች ለተሞላች ሀገር እዘኑላት ....በጥባጮችን እንደ ጀግና በእልልታ ለምትቀበል ፣ አንፀባራቂ ድል አድራጊዎችን እንደ ለጋስ ለምታሞካሽ ሀገር እዘኑላት ..... መሪው ቀበሮ ፈላስፋው ቀጣፊ ጥበቡም መኮረጅና መለጣጠፍ ለሆነ ህዝብ እዘኑለት ..... አዋቂዎቿ በእድሜ መግፋት ዲዳ ለሆኑባት ፣ ብርቱ ልጆችዋ ገና ከህፃን አልጋ ላይ ላልተነሱላት ሀገር እዘኑላት ..... ግዛቷ ለተበጣጠሰባትና እያንዳንዱ ብጥስጣሽ ራሱን እንደ አንድ ሀገር ለሚቆጥርባት ሀገር እዘኑላት .....

ገፅታዎች ( 153 )
የጠቢባን መንገድ


@Write_event
@Write_event
@Write_event
💡ሕይወት በ’የኔ’ እና ‘የኛ’ የምናሳንሰው ነገር የላትም… ከጽንፍ አልባው ምልዓት ላይ በተገለጸልን ልክ የገባንን ሁሉ የእኔ/ኛ አንልም… እኛ ራሳችንን ያንን ምልዓት አይደለን? “You are not a drop in the ocean; you are the entire ocean in a drop” ይላል Rumi

❤️ ይህን ሁለንተና በግላዊነት መያዝ አይቻልም… የኔ ብሎ ማሳነስ አይቻልም… እኛው ራሳችን ሁለንተናውን ነንና ፣ ብዙ የአለማችን እሳቤዎች ከሕይወት በተናጥሎ የመኖርን ቅዠት ይሰብካሉ… ውቅያኖሱን ሆነህ ሳለ የውቅያኖሱን ‘አንድ ጠብታ ወስደህ’ የኔ ማለት ከራስም ያሳንሳል…ከራስህ ተነጥለህ ‘የራስህ’ ሊኖርህ አይችልም።

💡የግዙፍ ውቅያኖስ አካል ነን ፣ከኔ ቤት ላይ የረጨኸው እሳት ከሆነ ነበልባሉ ያንተን ቤት ይነካል ሽቶ ስትረጨኝ የመዓዛው ቅንጣቶች ለአፍንጫህ ውብ ጠረን ይለግሳል ሰው የዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳል ይህን ምስራቃውያኑ Karma ሲሉት ሌሎች ደግሞ Boomerang ይሉታል Boomerang አውስትራሊያኖቹ አቦርጂኒስቶች ከእንጨት የሚሰሩት ደጋን ቅርጽ ያለው የአደን መሳሪያ ሲሆን ወርዋሪው ዘንድ ተመልሶ እንዲመጣ ተደርጎ የሚነደፍ ነው… ለሃሳብ፣ ለስሜትና ድርጊትህ መጠንቀቅ የሚኖርብህ ወላፈኑ ‘ለእኔም’፣ ‘ለእርሷም’፣ ‘ለእነርሱም’ እንደሚተርፍ በማሰብ ነው ምክንያቱም We are all One!

💎በረከት በላይነህ "የመንፈስ ከፍታ" ላይ እንዲህ ይለናል
“የግልህ ወንዝ ስለሌለህ ብቻህን የምትሰራው ድልድይ የለም! የሰማዩ ርቀት፣ የምድሪቱ ስፋት በ’እኛ’ እንጂ በ’እኔ’ አይለካም፡፡ ውዱ ‘እኔ’ ከ’እኛ’ የተሰራው ነውና!”

ደምስ ሰይፉ

           ውብ አሁን!!❤️


@Write_event
@Write_event
@Write_event
የሰማያት ቁጣ!
(መዘክር ግርማ)

መብረቅ ብርሃን ጅራፍህ
ሰማይ ላይ ሲጦፍ ሲኖጋ
ያጮኽከው ሥውር እጅ ሆይ!
ያረ'ከው አፍታ እንዲነጋ
የት እንደወደቀ ባላ'ቅም
ለማን እንደሆን ይህ ቁጣ
ቤቴን ደርምሶ ባይገባም
ከሁሉ እኔን ነው የቀጣ!

ዐይኖቿን ጨፍና – ውበቷን ግን ገልጣ
እንደ መልአክ አምናኝ፣ ጎኔ ተሸጉጣ
ተኝታ የነበር ተነሳች ደንግጣ፡፡



@Write_event
@Write_event
@Write_event
አንድዬና አንድ ቀን
(አሌክስ አብርሃም)


አንድ ቀን ያልፋል እያለ
አንድ ነፍስ ስንት አመት ይልፋ፣
አንድ ቀን አይመጣ መስሎት
አንድስ ክንድ ስንት ጉድ ይግፋ...
አንድዬስ ለአንድ ምፅአት
ምነዉ ገደልከን በተስፋ ?
:
''አንድ አይነድ ፍርድም ባንድ አያምር''
ሰዉኛ ብሂል ተርተዉ
ባንድ ክንድ እየደቆሱ፣
ባንድ እሳት አገር ሲያምሱ...
አንድ ሰዉ ይጠይቀዉ ዘንድ
ያንድዬ ምን ይሆን መልሱ?
:
ኮሳሶች ደስ ይበላችሁ
ካንድ ብርቱ ልትበረቱ፣
ሁለት ኮሳሳ ይሻላል
ብሎ ብያፀናን ተረቱ፣
ሁለት ኮሳሶች በርትተዉ
ስለ አንድነት ቢዘምቱ፣
አንዱ አንዱን እያደባየ
መልሶ ያዉ አንድ ብርቱ!
:
ምንድነዉ አንድ አንቆ መጮህ
አንድዬ አንድ በለና፣
አንድ ወንዝ ስንቴ እንሻገር
ጠብ ለማይል መና...
:
ሕዝብህ ሁለት ባላ ተክሎ፣
አንዱ ሲቀል በአንዱ
ተፍገምግሞ ተንጠልጥሎ...
''አንድዬ አንተ ታዉቃለህ''
እያለህ ሲኖር በዘዴ፣
ላንዳንዶች እንደምንለዉ
''ት'ግስትህ አልበዛም እንዴ''
:
አንድ ለናቱ ለመባል የእናቱን ልጆች ጨርሶ፣
አንድ አይፈርድ ተረት ቢያሰማን
የአንድ ዓይን እንባ አልቅሶ...
እኛም አንድ ጸሎት አለን
አንድዬ አንዴ ስማና...
:
አንድነት እየሰበኩን-አንድነት የሚቀፋቸዉ ፣
አንድዬ አንድ አርገንና...አንድ ቀን አንድ በላቸዉ !!
:
(አንፈርስም አንታደስም ገፅ ፩፻፸፱)


@Write_event
@Write_event
@Write_event
አራት ዓይነት እብደት...
ኤፍሬም ሥዩም ( ኑ ግድግዳ እናፍርስ!)



ብቸኝነት ብርዱ ገላህን ቀዝቅዞ
ከሰው መሀል አንተን ለብቻህ ሰቅዞ
መጠየቅ ስትጀምር ...
ለምን!...እንዴት?...ስትል?
ጥያቄህ በራሱ እብደት ነው የሚባል
ኡፍፍፍ...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!


መጠየቅ ሰልችቶህ ከሕዝቦች ስትርቅ
በራስህ ዓለም ላይ ህሊናህ ሲራቀቅ
አፍህ ዝም ባለ
እብድ መባል አለ።
ኤጭ!...
አቋመ ቢስ መሐል ለብቻችን ነቅተን
አቦ ተሰቃየን!


የሕዝብ ሁሉ ሀሳብ የእብደት ሲመስልህ
ያንተ አሳብ የእውነት....
እውነት እንደሆነ ውስጥህን ሲሰማህ
እብዱ ትባላለህ።
ኤዲያ!...
አውቆ የሚተኛ ሕዝብ መሀል ነቅተን፣
አቦ ተሰቃየን!


ዓለሙም እብድ ነው!
ግና ያለም እብደት ካንተ የሚለየው
አንተ የምታብደው ለዓለም ስትል ነው
ዓለሙ ያበደው አንተን ሊያሳብድ ነው።
ወገን ተሰቃየን!
አውቆ በተኛ አቋመ ቢስ መሐል...
ለብቻችን ነቅተን
አወይ ተሰቃየን!!
.....



@Write_event
@Write_event
@Write_event