Forgot password is my password!
(አሌክስ አብርሃም)
አሜሪካ ኑሮው ከባድ ነው፣ብቸኝነቱ ከባድ ነው፣ አየሩ ከባድ ነው ፣ ይሄ ከባድ ነው …ያ ከባድ ነው ይላሉ እንጅ እኔ እስከአሁን የከበደኝ ሁለት ነገር ብቻ ነው! አንዱ ፓስወርድ ማስታወስ ! ፓስወርድ የሌለውን ነገር ጠይቁኝ …. ፓስወርድ በጣም ከመብዛቱ የተነሳ ዝም ብሎ በተራ ቁልፍ የሚከፈት ነገር ላይ ሁሉ ጣቴን አሾላለሁ! ዋሌቴን የሞላውን ካርድ አውጥቸ ብበውዘው …. በየመንገዱ እየዞርኩ በመጫዎቻ ካርድ ማጅክ ምናምን የምሰራ ሰው ያስመስለኛል !እዚች አገር ትንሽ ከቆየሁ እንደጋሽ ስብሃት ካርዴን በፌስታል መያዜ የማይቀር ነው! እንግዲህ ይሄ ሁሉ ካርድ ፓስወርድ አለው! እንዴት እንደሚሰለች የደረሰበት ያውቀዋል! እና አንድ ወዳጀ forgot password is your password ይለኛል !
ሁለተኛው ችግሬ … በጣም የሚበዙ ኢትዮጵያዊያን ጋር ስቀላቀል ልክ እንደቻይና ኮሪያ ምናምን አንድ አይነት ይሆኑብኛል ! መለየት በጣም ነው የሚከብደኝ ! በምሳሌ ላስረዳ! አሁን በቅርቡ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ምሳ ጠሩኝ …ምክንያት? ከኢትዮጵያ እህታቸው ስለመጣች! ....ስደርስ ያለምንም ግነት ስድስት ወይም ሰባት የሚሆኑ አንድ አይነት ሴቶች ቤቱ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይላሉ …የሌላውን እንግዳ ብዛት ደግሞ ተውት …ሁሉም አንድ አይነት የባህል ልብስ ለብሰዋል …ሁሉም ሹሩባ ተሰርተዋል …ሁሉም በሜካፕ አብደዋል …ሁሉም አይፎን ስልክ ይዘዋል … እና ሁሉም ጥርሳቸው ብሬስ …በእርግጥ ሁሉም ቆንጆዎች ነበሩ ! እና ምሳ የጠራችኝ አክስታቸው እያስተዋወቀችኝ ነው …
እሷ ቲጅ ናት ባለፈው ዳኒን አግብታ የመጣችው …ያው ዳኒ ግን የአጎቷ ልጅ ነው …ለፕሮሰስ ነው እንጅ እሷ አላገባችም ሲንግል ነች ሂሂሂ(ምን ሂሂሂ ያስብላል) !ትክ ብየ አየኋት በስማም ቁንጅና ….ሌሎቹ ጋር አንድ አይነት !ይሄ የተረገመ ሹርባ እንዴት ነው ሰው የሚያመሳስለው! …ይችኛዋ ኪያ ነች ….የዛሬ አመት አሴን አግብታ የመጣችው …አሴን ታውቀው የለ የኔ ትልቁ ልጅ የሩታ ባል …ለፕሮሰስ ነው እንጅ ትክክለኛ ባሏ ዳጊ ነው ! ያች (ነይ አንች ሰላም በይው ) ፍልቅልቅ እያለች መጣች ! ይች ሩሃማ ነች … ለቫኬሽን መጥታ በአሳይለም የቀረችው …
ፖለቲከኛ ነች ጋዜጠኛ?…አልኩ …..
ማን እሷ? አሁን ያለው ጠቅላይ ሚንስትር ማነው ብትላት አታውቀውም …ለፕሮሰስ ነው ! ያችኛዋ ናኒ ነች የፍሬው ሚስት …እና ደግሞ ይች ፊኖ የሽሜ ሚስት …ያች ….ኪራ ለፕሮሰስ ፍፄን አግብታ የመጣችው ናት …ፍፄን ታውቀው የለ የሲቲና ባል ….
ዘወርወር ስላለብኝ …ከምግብ ቡፌው ላይ ሁለት ናብኪን አንስቸ ሰሃኑ ላይ ካነጠፍኩ በኋላ ቀይ ወጥ ጨመርኩበት …አልጫ ልጨምርበት ስል ነው እንጀራውን እንደረሳሁ ትዝ ያለኝ😐! ወደውስጥ ገብተው በተመለሱ ቁጥር አንዷ ከሌላኛዋ ይምታቱብኛል …ዋናው ነጥብ ሲንግል የተባለችውን ላለመርሳት መሞከር ነው እላለሁ ለራሴ…ለምልክት ቀሚሷን ቀይ ወጥ ላስነካው ይሆን ….! ግን ነገሩ ቀይዋን ያየ የሚሉት አይነት የካርታ ጨዋታ ነበር …ተበወዙብኝ …ውር ውር ውር ያገባች ያላገባች ፕሮሰስ አሳይለም! የቷ ናት ሲንግል ይለኛል አእምሮየ …ይች ነቻ እላለሁ …ተሳሳትክ ይች የፍሬው ሚስት ናት!
ሲንግሏ ናት ብየ ያሰብኳትን ፈገግ አልኩላት ፈገግ አለች …ብሬስ ! እንዴት ነው ታዲያ አገሩን ለመድሽው … ኦ እኔ አይደለሁምኮ የመጣሁት …የት ሄደች ቲጅ ናት … ተሳሳቅን! ቆይቸ ቲጅን አገኘኋት ብየ ወሬ ስጀምር ቶማስ መጥቶ አብርሽ ተጫዎት ተዋወቃችሁ?…ናኒ ባለቤቴ ነች ! እንዲቹ እንደተምታታብኝ ‹‹የታለች ሲንግሏ ቲጅ ? መልሳችሁ.... ወደአገር ቤት ላካችኋት እንዴ ? ….›› ብየ ልጮህ ምንም አልቀረኝም በሰው አገር ሰንደል ፀጉሬ ላይ ሰክቸ ከመዞሬ በፊት ማሰቡትን ትቸ ሰሀኔ ላይ አቀረቀርኩ! ምናይነት ፊዚክስ የሆነ ቤተሰብ ነው?! ተሰናብቸ ስወጣ አክስታቸው …ከተል ብላኝ በቁም ነገር …
‹‹እኔ የምልህ አብርሽ …. ትንሽ አትጫዎትም ነበር? ….
‹‹ሌላ ቀን እመጣለሁ ››
‹‹ መምጣትማ አለብህ ! አንግዳዋን እናተ ካላላመዳችኋት ማን ያላምዳታል?! …ካለች በኋላ ወደዋናው ነጥቧ ገባች! እየውልህ …ሰው በቁሙ ካልተጠቃቀመ መቸም በኋላ እየየ ምን ያደርጋል …አንድ ነገር አስቤኮ …አንድ እህታቸው ብቻ አገር ቤት ቀርታለች … ለፕሮሰስ ለማን ልዳራት ብየ ሳስብ አንተ ትዝ አልከኝ … ባይሆን ያንተን እህት ደግሞ አንዱ የኔ ልጅ አግብቶ ያመጣታል !
ሲንግል ናት …? አልኩ (እስቲምናገባኝ)
ኧረ አግብታ ሁለት ወልዳለች …ባሏ በካቦ ቢጎትቱት ከዛ አገር የሚንቀሳቀስ አይነት አይደለም እንጅ ! እንዴት ያለች ቆንጆ መሰለችህ …መዓዚየ! ይች ሴትዮማ በአሳይሎም ቀርታ እንጅ የሆነ የፖለቲካ ድርጅት መሪ ሳትሆን አትቀርም ! …ወደቤት ስመለስ መንገድ ላይ የትኛው መስመር የኔ የትኛው በተቃራኒ መስመር የሚመጣው መኪና እንደሆነ ብዥዥዥዥዥዥዥዥ …ጭራሽ የተሳሳተ ሰፈር ገብቸ አረፍኩ! ጂፒኤስ ለመጠቀም ስልኬን አወጣሁ…. ስልኬ በፓስወርድ ጥርቅም ተደርጎ ተዘግቷል ….ፓስወርዱን ምን ነበር ? ….አዎ forgot password is my password!
#AlexAbreham
ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
share and join
@write_event
@write_event
@write_event
(አሌክስ አብርሃም)
አሜሪካ ኑሮው ከባድ ነው፣ብቸኝነቱ ከባድ ነው፣ አየሩ ከባድ ነው ፣ ይሄ ከባድ ነው …ያ ከባድ ነው ይላሉ እንጅ እኔ እስከአሁን የከበደኝ ሁለት ነገር ብቻ ነው! አንዱ ፓስወርድ ማስታወስ ! ፓስወርድ የሌለውን ነገር ጠይቁኝ …. ፓስወርድ በጣም ከመብዛቱ የተነሳ ዝም ብሎ በተራ ቁልፍ የሚከፈት ነገር ላይ ሁሉ ጣቴን አሾላለሁ! ዋሌቴን የሞላውን ካርድ አውጥቸ ብበውዘው …. በየመንገዱ እየዞርኩ በመጫዎቻ ካርድ ማጅክ ምናምን የምሰራ ሰው ያስመስለኛል !እዚች አገር ትንሽ ከቆየሁ እንደጋሽ ስብሃት ካርዴን በፌስታል መያዜ የማይቀር ነው! እንግዲህ ይሄ ሁሉ ካርድ ፓስወርድ አለው! እንዴት እንደሚሰለች የደረሰበት ያውቀዋል! እና አንድ ወዳጀ forgot password is your password ይለኛል !
ሁለተኛው ችግሬ … በጣም የሚበዙ ኢትዮጵያዊያን ጋር ስቀላቀል ልክ እንደቻይና ኮሪያ ምናምን አንድ አይነት ይሆኑብኛል ! መለየት በጣም ነው የሚከብደኝ ! በምሳሌ ላስረዳ! አሁን በቅርቡ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ምሳ ጠሩኝ …ምክንያት? ከኢትዮጵያ እህታቸው ስለመጣች! ....ስደርስ ያለምንም ግነት ስድስት ወይም ሰባት የሚሆኑ አንድ አይነት ሴቶች ቤቱ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይላሉ …የሌላውን እንግዳ ብዛት ደግሞ ተውት …ሁሉም አንድ አይነት የባህል ልብስ ለብሰዋል …ሁሉም ሹሩባ ተሰርተዋል …ሁሉም በሜካፕ አብደዋል …ሁሉም አይፎን ስልክ ይዘዋል … እና ሁሉም ጥርሳቸው ብሬስ …በእርግጥ ሁሉም ቆንጆዎች ነበሩ ! እና ምሳ የጠራችኝ አክስታቸው እያስተዋወቀችኝ ነው …
እሷ ቲጅ ናት ባለፈው ዳኒን አግብታ የመጣችው …ያው ዳኒ ግን የአጎቷ ልጅ ነው …ለፕሮሰስ ነው እንጅ እሷ አላገባችም ሲንግል ነች ሂሂሂ(ምን ሂሂሂ ያስብላል) !ትክ ብየ አየኋት በስማም ቁንጅና ….ሌሎቹ ጋር አንድ አይነት !ይሄ የተረገመ ሹርባ እንዴት ነው ሰው የሚያመሳስለው! …ይችኛዋ ኪያ ነች ….የዛሬ አመት አሴን አግብታ የመጣችው …አሴን ታውቀው የለ የኔ ትልቁ ልጅ የሩታ ባል …ለፕሮሰስ ነው እንጅ ትክክለኛ ባሏ ዳጊ ነው ! ያች (ነይ አንች ሰላም በይው ) ፍልቅልቅ እያለች መጣች ! ይች ሩሃማ ነች … ለቫኬሽን መጥታ በአሳይለም የቀረችው …
ፖለቲከኛ ነች ጋዜጠኛ?…አልኩ …..
ማን እሷ? አሁን ያለው ጠቅላይ ሚንስትር ማነው ብትላት አታውቀውም …ለፕሮሰስ ነው ! ያችኛዋ ናኒ ነች የፍሬው ሚስት …እና ደግሞ ይች ፊኖ የሽሜ ሚስት …ያች ….ኪራ ለፕሮሰስ ፍፄን አግብታ የመጣችው ናት …ፍፄን ታውቀው የለ የሲቲና ባል ….
ዘወርወር ስላለብኝ …ከምግብ ቡፌው ላይ ሁለት ናብኪን አንስቸ ሰሃኑ ላይ ካነጠፍኩ በኋላ ቀይ ወጥ ጨመርኩበት …አልጫ ልጨምርበት ስል ነው እንጀራውን እንደረሳሁ ትዝ ያለኝ😐! ወደውስጥ ገብተው በተመለሱ ቁጥር አንዷ ከሌላኛዋ ይምታቱብኛል …ዋናው ነጥብ ሲንግል የተባለችውን ላለመርሳት መሞከር ነው እላለሁ ለራሴ…ለምልክት ቀሚሷን ቀይ ወጥ ላስነካው ይሆን ….! ግን ነገሩ ቀይዋን ያየ የሚሉት አይነት የካርታ ጨዋታ ነበር …ተበወዙብኝ …ውር ውር ውር ያገባች ያላገባች ፕሮሰስ አሳይለም! የቷ ናት ሲንግል ይለኛል አእምሮየ …ይች ነቻ እላለሁ …ተሳሳትክ ይች የፍሬው ሚስት ናት!
ሲንግሏ ናት ብየ ያሰብኳትን ፈገግ አልኩላት ፈገግ አለች …ብሬስ ! እንዴት ነው ታዲያ አገሩን ለመድሽው … ኦ እኔ አይደለሁምኮ የመጣሁት …የት ሄደች ቲጅ ናት … ተሳሳቅን! ቆይቸ ቲጅን አገኘኋት ብየ ወሬ ስጀምር ቶማስ መጥቶ አብርሽ ተጫዎት ተዋወቃችሁ?…ናኒ ባለቤቴ ነች ! እንዲቹ እንደተምታታብኝ ‹‹የታለች ሲንግሏ ቲጅ ? መልሳችሁ.... ወደአገር ቤት ላካችኋት እንዴ ? ….›› ብየ ልጮህ ምንም አልቀረኝም በሰው አገር ሰንደል ፀጉሬ ላይ ሰክቸ ከመዞሬ በፊት ማሰቡትን ትቸ ሰሀኔ ላይ አቀረቀርኩ! ምናይነት ፊዚክስ የሆነ ቤተሰብ ነው?! ተሰናብቸ ስወጣ አክስታቸው …ከተል ብላኝ በቁም ነገር …
‹‹እኔ የምልህ አብርሽ …. ትንሽ አትጫዎትም ነበር? ….
‹‹ሌላ ቀን እመጣለሁ ››
‹‹ መምጣትማ አለብህ ! አንግዳዋን እናተ ካላላመዳችኋት ማን ያላምዳታል?! …ካለች በኋላ ወደዋናው ነጥቧ ገባች! እየውልህ …ሰው በቁሙ ካልተጠቃቀመ መቸም በኋላ እየየ ምን ያደርጋል …አንድ ነገር አስቤኮ …አንድ እህታቸው ብቻ አገር ቤት ቀርታለች … ለፕሮሰስ ለማን ልዳራት ብየ ሳስብ አንተ ትዝ አልከኝ … ባይሆን ያንተን እህት ደግሞ አንዱ የኔ ልጅ አግብቶ ያመጣታል !
ሲንግል ናት …? አልኩ (እስቲምናገባኝ)
ኧረ አግብታ ሁለት ወልዳለች …ባሏ በካቦ ቢጎትቱት ከዛ አገር የሚንቀሳቀስ አይነት አይደለም እንጅ ! እንዴት ያለች ቆንጆ መሰለችህ …መዓዚየ! ይች ሴትዮማ በአሳይሎም ቀርታ እንጅ የሆነ የፖለቲካ ድርጅት መሪ ሳትሆን አትቀርም ! …ወደቤት ስመለስ መንገድ ላይ የትኛው መስመር የኔ የትኛው በተቃራኒ መስመር የሚመጣው መኪና እንደሆነ ብዥዥዥዥዥዥዥዥ …ጭራሽ የተሳሳተ ሰፈር ገብቸ አረፍኩ! ጂፒኤስ ለመጠቀም ስልኬን አወጣሁ…. ስልኬ በፓስወርድ ጥርቅም ተደርጎ ተዘግቷል ….ፓስወርዱን ምን ነበር ? ….አዎ forgot password is my password!
#AlexAbreham
ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
share and join
@write_event
@write_event
@write_event
የደራሲ በአሉ ግርማ ባለቤት አልማዝ አበራ አረፉ
የታላቁ ደራሲና ጋዜጠኛ የበአሉ ግርማ ባለቤት አልማዝ ዛሬ ጥቅምት 30/2015 ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው አርድተውኛል ሲል ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ አስታውቋል።
አልማዝ ባለቤታቸውን የበአሉ ግርማን ሞትና መሰወር አልቀበል ብለው የቆዩ ሲሆን፤ ሁልግዜ ጠዋት ላይ ቤታቸውን አፀዳድተው በር ከፍተው በአሉ ግርማን ይመጣል እያሉ ሲጠብቁት ኖረው በዛሬው ዕለት ህይወታቸው አልፏል።
አልማዝ አበራ ከደራሲ በአሉ ግርማ ያፈሯቸው የሦስት ልጆች እናት ነበሩ።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይማርል።
@write_event
@write_event
@write_event
የታላቁ ደራሲና ጋዜጠኛ የበአሉ ግርማ ባለቤት አልማዝ ዛሬ ጥቅምት 30/2015 ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው አርድተውኛል ሲል ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ አስታውቋል።
አልማዝ ባለቤታቸውን የበአሉ ግርማን ሞትና መሰወር አልቀበል ብለው የቆዩ ሲሆን፤ ሁልግዜ ጠዋት ላይ ቤታቸውን አፀዳድተው በር ከፍተው በአሉ ግርማን ይመጣል እያሉ ሲጠብቁት ኖረው በዛሬው ዕለት ህይወታቸው አልፏል።
አልማዝ አበራ ከደራሲ በአሉ ግርማ ያፈሯቸው የሦስት ልጆች እናት ነበሩ።
ፈጣሪ ነፍሳቸውን ይማርል።
@write_event
@write_event
@write_event
😥ልብ የሚነካ #የእናትና ልጅ አጭር ታሪክ፠
👇👇👇👇👇👇👇👇
አንድ የ16 አመት ወጣት ‹‹እማ፤ 18ኛ አመት ሲሞላኝ ምን ስጦታ ትሰጭኛለሽ ?›› ሲል እናቱን ይጠይቃል፡፡ እናትም ‹‹ልጄ፤ ለ18 አመት እኮ ገና ብዙ ይቀርሃል›› ስትል ትመልሳለች፡፡ ልጁ 17 አመት ከሞላዉ በኋላ አንድ ቀን ራሱን ስቶ ይወድቅና እናቱ ወደ ሆስፒታል ትወስደዋለች፡፡ ያዩት ዶክተሮቹም... ‹‹ልጅሽ ልቡ ጥሩ አይደለም›› ሲሉ ያረዷታል፡፡ ስትሬቸር ላይ የተቀመጠዉ ልጇ… ‹‹ እማ፤ ዶክተሩ እንደምሞት ነገረሽ ወይ?›› ብሎ ሲጠይቃት እናት ማልቀስ ትጀምራለች፡፡ በመጨረሻም ልጁ በ18ኛ አመት የልደት ቀኑ ላይ ወደ መልካም ጤንነቱ ተመልሶ፤ ወደ ቤቱ
ሲመጣ፤ አልጋዉ ላይ እናቱ የተወችለት ደብዳቤ ያገኛል፡፡ ደብዳቤዉም እንዲህ የሚል ነበር፡-
‹‹ልጄ፤ ይሄን ደብዳቤ እያነበብክ ከሆን፤
ይህ የሆነዉ ሁሉም ነገር በመልካም ሁኔታ በመሄዱ ነዉ፡፡ ለ18ኛ አመትህ ምን እንደምሰጥህ የጠየከኝንና የምመልሰዉ (መልስ) ያጣሁበትን ያን ቀን አስታዉስ፡፡ የምወድህ ልጄ፤ ልቤን ሰጥቸሃለሁ፡፡ በጥንቃቄ ያዘዉ፡፡ መልካም የደስታ ዘመንም ይሁንልህ፡፡››
❤❤❤❤❤❤❤❤❤
❤❤❤❤❤❤
እናት ልቧን ለልጇ መስጠት ስለነበረባት (እናትነት አስገድዷት) ህይወቷ አልፏል፡፡
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
ከእናት ፍቅር በላይ የሆነ ምንም ነገር የለም።
ስንቶቻችን በወላጆቻችን እናፍር ይሆን? ስንት አይነት መስዋዕት ከፍለው አሳድገውን ይሆን? ዛሬስ ምላሻችን ምንድነው? ጊዜው ያልመሸባችሁ በቻላችሁት አቅም ሁሉ ‘አለሁልህ አባቴ ፣ አለሁልሽ እናቴ’ በሏቸው። እኛን ሰው ለማድረግ ከሰውነት ተራ ወጥተው ያሉ ወላጆችን ቤቱ ይቁጠራቸው። እናስተውል! እንዳይቆጨን! ብዙ ወላጆች እኛን ራሳችንን እንጅ የእኛን ነገር አይፈልጉም ፣ በተቃራኒው ደግሞ እኛ የእንሱን ነገር እንጅ እነሱን አንፈልግም። እነሱን በመፈለግ ፍቅራችንን እናሳያቸው!
ይህ ታሪክ ከደረሳችሁ እናንተ ጋር እንዲቀር አትፍቀዱ ፣አስተማሪ ስለሆነ
እስከቻላችሁ ድረስ ለጓደኞቻችሁ ሼር በማድረግ እንጋብዛቸው።
Join and Share
@write_event
@write_event
@write_event
👇👇👇👇👇👇👇👇
አንድ የ16 አመት ወጣት ‹‹እማ፤ 18ኛ አመት ሲሞላኝ ምን ስጦታ ትሰጭኛለሽ ?›› ሲል እናቱን ይጠይቃል፡፡ እናትም ‹‹ልጄ፤ ለ18 አመት እኮ ገና ብዙ ይቀርሃል›› ስትል ትመልሳለች፡፡ ልጁ 17 አመት ከሞላዉ በኋላ አንድ ቀን ራሱን ስቶ ይወድቅና እናቱ ወደ ሆስፒታል ትወስደዋለች፡፡ ያዩት ዶክተሮቹም... ‹‹ልጅሽ ልቡ ጥሩ አይደለም›› ሲሉ ያረዷታል፡፡ ስትሬቸር ላይ የተቀመጠዉ ልጇ… ‹‹ እማ፤ ዶክተሩ እንደምሞት ነገረሽ ወይ?›› ብሎ ሲጠይቃት እናት ማልቀስ ትጀምራለች፡፡ በመጨረሻም ልጁ በ18ኛ አመት የልደት ቀኑ ላይ ወደ መልካም ጤንነቱ ተመልሶ፤ ወደ ቤቱ
ሲመጣ፤ አልጋዉ ላይ እናቱ የተወችለት ደብዳቤ ያገኛል፡፡ ደብዳቤዉም እንዲህ የሚል ነበር፡-
‹‹ልጄ፤ ይሄን ደብዳቤ እያነበብክ ከሆን፤
ይህ የሆነዉ ሁሉም ነገር በመልካም ሁኔታ በመሄዱ ነዉ፡፡ ለ18ኛ አመትህ ምን እንደምሰጥህ የጠየከኝንና የምመልሰዉ (መልስ) ያጣሁበትን ያን ቀን አስታዉስ፡፡ የምወድህ ልጄ፤ ልቤን ሰጥቸሃለሁ፡፡ በጥንቃቄ ያዘዉ፡፡ መልካም የደስታ ዘመንም ይሁንልህ፡፡››
❤❤❤❤❤❤❤❤❤
❤❤❤❤❤❤
እናት ልቧን ለልጇ መስጠት ስለነበረባት (እናትነት አስገድዷት) ህይወቷ አልፏል፡፡
❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤
ከእናት ፍቅር በላይ የሆነ ምንም ነገር የለም።
ስንቶቻችን በወላጆቻችን እናፍር ይሆን? ስንት አይነት መስዋዕት ከፍለው አሳድገውን ይሆን? ዛሬስ ምላሻችን ምንድነው? ጊዜው ያልመሸባችሁ በቻላችሁት አቅም ሁሉ ‘አለሁልህ አባቴ ፣ አለሁልሽ እናቴ’ በሏቸው። እኛን ሰው ለማድረግ ከሰውነት ተራ ወጥተው ያሉ ወላጆችን ቤቱ ይቁጠራቸው። እናስተውል! እንዳይቆጨን! ብዙ ወላጆች እኛን ራሳችንን እንጅ የእኛን ነገር አይፈልጉም ፣ በተቃራኒው ደግሞ እኛ የእንሱን ነገር እንጅ እነሱን አንፈልግም። እነሱን በመፈለግ ፍቅራችንን እናሳያቸው!
ይህ ታሪክ ከደረሳችሁ እናንተ ጋር እንዲቀር አትፍቀዱ ፣አስተማሪ ስለሆነ
እስከቻላችሁ ድረስ ለጓደኞቻችሁ ሼር በማድረግ እንጋብዛቸው።
Join and Share
@write_event
@write_event
@write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
Forwarded from °•ᴍᴏᴏɴ•° (ᴍᴏᴏɴ)
እውነተኛው ጓደኛህ ማነው?
፨፨፨፨፨፨//////////፨፨፨፨፨፨
እውነተኛው ጓደኛህ ማነው? በቀላሉ የሚረዳህ፣ መንገድህን የሚጠርግልህ፣ ሃሳብህን፣ ህልምህን፣ ራዕይህን የሚደግፍልህ፣
አዎ! ብዙ ሰው ብዙ ጓደኞች አሉት፤ ከብዛታቸው ያተረፈው ነገር ግን የለም።
አዎ! ጓደኝነት ሁሉም ነገር ነው። እየሳቀ ከሚጥልህ እየተቆጣ፣ እየገሰፀ የሚያስተካክልህ ሰው ላንተ ትልቅ ስፍራ አለው። ቢኖርም ከማይጠቅምህ፣ ቢሄድም ከማይጎዳህ ሰው መለየት ይኖርብሃል
-
ᎢᎬᏞᎬ :- @M00N_i 🖤
፨፨፨፨፨፨//////////፨፨፨፨፨፨
እውነተኛው ጓደኛህ ማነው? በቀላሉ የሚረዳህ፣ መንገድህን የሚጠርግልህ፣ ሃሳብህን፣ ህልምህን፣ ራዕይህን የሚደግፍልህ፣
አዎ! ብዙ ሰው ብዙ ጓደኞች አሉት፤ ከብዛታቸው ያተረፈው ነገር ግን የለም።
አዎ! ጓደኝነት ሁሉም ነገር ነው። እየሳቀ ከሚጥልህ እየተቆጣ፣ እየገሰፀ የሚያስተካክልህ ሰው ላንተ ትልቅ ስፍራ አለው። ቢኖርም ከማይጠቅምህ፣ ቢሄድም ከማይጎዳህ ሰው መለየት ይኖርብሃል
-
ᎢᎬᏞᎬ :- @M00N_i 🖤
ራሴን ወግቼ ላንቺ የምወግን
(በእውቀቱ ስዩም)
አይደለሁም ጀግና
ልቤን እና ክንዴን ፥እጠራጠራለሁ
ግን ተኩሼ ባልጥል፥ አነጣጥራለሁ
ቀማኛ ቢከብሽ፥ ፖሊስ እጠራለሁ::
ቅዱስ አይደለሁም፥
የጻድቃን ቤት ካለ፥ በውስጡ የለሁም::
መናኛው ራሴ፥ ቢበጠር፥ ቢላጭም
ለሳር ባርኔጣ እንጂ፥ ላክሊል አይታጭም::
ምንድን ሆኘ ነው ግን?
ራሴን ወግቼ ላንቺ የምወግን
ምኔን አሞኝ ነው ግን ?
እንችን የማሞግስ፥ ራሴን ወቅሼ
ሳቄን የማካፍል፤ ለብቻየ አልቅሼ፤
እንደ ጋሻ ጃግሬሽ ፤ ከሁዋላሽ ስባክን
ከፊትሽ ቀድሜ፥ እንቅፋት ሳመከን
አይተሽ እንዳላየ
ጀግኖች ምናረጉ
ሰማታት ምን ሰሩ፤ ከዚህ የተለየ፥
https://t.me/write_event
(በእውቀቱ ስዩም)
አይደለሁም ጀግና
ልቤን እና ክንዴን ፥እጠራጠራለሁ
ግን ተኩሼ ባልጥል፥ አነጣጥራለሁ
ቀማኛ ቢከብሽ፥ ፖሊስ እጠራለሁ::
ቅዱስ አይደለሁም፥
የጻድቃን ቤት ካለ፥ በውስጡ የለሁም::
መናኛው ራሴ፥ ቢበጠር፥ ቢላጭም
ለሳር ባርኔጣ እንጂ፥ ላክሊል አይታጭም::
ምንድን ሆኘ ነው ግን?
ራሴን ወግቼ ላንቺ የምወግን
ምኔን አሞኝ ነው ግን ?
እንችን የማሞግስ፥ ራሴን ወቅሼ
ሳቄን የማካፍል፤ ለብቻየ አልቅሼ፤
እንደ ጋሻ ጃግሬሽ ፤ ከሁዋላሽ ስባክን
ከፊትሽ ቀድሜ፥ እንቅፋት ሳመከን
አይተሽ እንዳላየ
ጀግኖች ምናረጉ
ሰማታት ምን ሰሩ፤ ከዚህ የተለየ፥
https://t.me/write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
።ፍቅር- ፈራን:ጠላን።🖤
"ፈራን"🖤
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
https://t.me/write_event
"ፈራን"🖤
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን
ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን
https://t.me/write_event
Telegram
ቃላዊ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
የወደፊት ሲደምቅ!
“ለወደፊቱ ራእይ የሌለው ሰው ሁል ጊዜ ወደኋላው ይመለሳል” (Kevin Gates)
ካለፈውና ካከተመለት ነገር ትምህርትን አግኝቶ ወደፊት ከመገስገስ ይልቅ እሱን እንደገና እያሰቡ የመጨናነቅ፣ የመረበሽና ተስፋ የመቁረጥ ሁኔታ የሚያጠቃችችሁ ከሆነ ምናልባት የወደፊት ራእይ ያለመኖሩ ምልክት እንዳይሆን ጠርጥሩ፡፡
የወደፊታችሁ እየፈዘዘ ከሄደና ማየት ከተሳናችሁ የኋላችሁና ያለፋችሁት ነገር መድመቅና መጉላት ይጀምራል፡፡ በሌላ አገላለጽ የአንዱ መድመቅ የሌላኛው መደብዘዝ ነው፡፡ ምርጫው ግን በእጃችሁ ነው፡፡
ያለፈ ጉዳት … ያለፈ የተሳሳተ ውሳኔ … ያለፈ ክስረት … ያለፈ ተጀምሮ የተቋረጠ ነገር … ያለፈ ጎድቶንና ትቶን የሄደ ሰው … እየተመላለሰ ስሜታችሁን ቀውስ ውስጥ የሚጨምረው ከሆነ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚቀርፍላችሁ ብቸኛ ነገር የወደፊታችሁን ራእይ ማየትና እሱ ላይ ማተኮር ነው፡፡
የወደፊት ራእያችሁ ካለፈው ታሪካችሁ ሊጠነክርና ሊደምቅ ይገባዋል፡፡
ያለፈው ታሪካችሁ ከሚሰጣችሁ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ይልቅ የወደፊታችሁ የሚሰጣችሁ የመጓጓት ስሜት ሊያይል ይገባዋል፡፡
ዶ/ር እዮብ ማሞ
@write_event
@write_event
@write_event
“ለወደፊቱ ራእይ የሌለው ሰው ሁል ጊዜ ወደኋላው ይመለሳል” (Kevin Gates)
ካለፈውና ካከተመለት ነገር ትምህርትን አግኝቶ ወደፊት ከመገስገስ ይልቅ እሱን እንደገና እያሰቡ የመጨናነቅ፣ የመረበሽና ተስፋ የመቁረጥ ሁኔታ የሚያጠቃችችሁ ከሆነ ምናልባት የወደፊት ራእይ ያለመኖሩ ምልክት እንዳይሆን ጠርጥሩ፡፡
የወደፊታችሁ እየፈዘዘ ከሄደና ማየት ከተሳናችሁ የኋላችሁና ያለፋችሁት ነገር መድመቅና መጉላት ይጀምራል፡፡ በሌላ አገላለጽ የአንዱ መድመቅ የሌላኛው መደብዘዝ ነው፡፡ ምርጫው ግን በእጃችሁ ነው፡፡
ያለፈ ጉዳት … ያለፈ የተሳሳተ ውሳኔ … ያለፈ ክስረት … ያለፈ ተጀምሮ የተቋረጠ ነገር … ያለፈ ጎድቶንና ትቶን የሄደ ሰው … እየተመላለሰ ስሜታችሁን ቀውስ ውስጥ የሚጨምረው ከሆነ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚቀርፍላችሁ ብቸኛ ነገር የወደፊታችሁን ራእይ ማየትና እሱ ላይ ማተኮር ነው፡፡
የወደፊት ራእያችሁ ካለፈው ታሪካችሁ ሊጠነክርና ሊደምቅ ይገባዋል፡፡
ያለፈው ታሪካችሁ ከሚሰጣችሁ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ይልቅ የወደፊታችሁ የሚሰጣችሁ የመጓጓት ስሜት ሊያይል ይገባዋል፡፡
ዶ/ር እዮብ ማሞ
@write_event
@write_event
@write_event
ለልደትህ ይድፋህ!?
(አሌክስ አብርሃም)
ወገኖቸ መልካም ልደት የሚሏችሁን ሁሉ አትመኑ! አንዳንዶች የልደት በግ አልብሰው ቀበሮ ሞት ይልካሉና😀ከፈቀዳችሁልኝ ልምዴን ላካፍል? አመሠግናለሁ! በጣም እንደምትወደኝ ዘላለም ብኖር ደስ እንደሚላት የነገረችኝ ልጅ ባለፈው አመት ልደቴን ሳከብር በፖስጣ የታሸገ ስጦታ አመጣችልኝ...ፖስታው ባዶ ስለሚመስልና ውስጡ የሆነ ወረቀት ነገር ስለነበር በቃ ዶላር ይሆናል ብየ አሰብኩ... ሰዎች ስጦታ ለመምረጥ ለመግዛት ጊዜ ካጡ ካሹን መስጠት የተለመደ ነገር ነው! (ዶላርን በስሙ ብቻ የምታውቁና ነክታችሁት ለማታውቁ እኔ አሁኑኑ.......አብራራላችኋለሁ! ዶላር /አንዳንዶች ዳላር ይሉታል / እንደምላጭ የሳሳ ግን እንደምላጭ ስለታም የገንዘብ አይነት ነው ! ከአገራችሁ ጋር የተያያዛችሁበትን ጨምሮ የማይቆርጠው እትብት የማይላጨው ፀጋ የለም😀)
እና ቆንጆ አይኖቿን እያስለመለመች "ክፈተዋ " አለችኝ ፖስታውን ! ስከፍተው ትኬት ነው ... አይኔን ማመን አልቻልኩም ....Go Skydiving on your Birthday...
Jump two miles up with Amazing Views... ይላል! አቻ ትርጉሙ " ለልደት ቀንህ ለምን ሶስት ኪሎሜትር ወደሰማይ ወጥተህ ከአውሮፕላን ዘለህ እንደዱባ አትፈጠፈጥም ለመገፍተሩ እኛ አለንልህ " ማለት ነው 😀 ያው በሉት! ትኬቱ ከፍላችሁ ከአውሮፕላን ላይ በዣንጥላ መዝለያ ነው! ለልደቴ ማለት ነው ... እኔ ማለት ነው ....በዣንጥላ ከላይ ከሰማይ ማለት ነው ...
ወ
ደ
ታ
ች
"አታካብዳ ! "
"አካብዳለሁ ! ከፍታ አልወድም አልጋ ራሱ እየራቀብኝ ፍራሽ ላይ ነው የምተኛው" አልኩ! ለነገሩ ክብደት ለመስጠት!
"ብቻህን አይደለህምኮ ...አብሮህ የሚዘል ነጭ አለ ... " ትለኛለች ጭራሽ! እንደው ቢሆን እንኳ "Where Are You From? " እየተባልኩ ከመፈጥፈጥ ...ስር መሰረቴን ከሚያውቅ ከአገሬ ልጅ ጋራ ቁልቁል እያየን "ያ ሜዳ ጎዣምን አይመስልም?" እየተባባልን አብሬ ብፈጠፈጥ አይሻልም ? ሲሆን ሲሆን እንደግብፅ ነገስታት የሆነች ቆንጆ ጋር አስተሳስረው ወደሞቴ ቢልኩኝ ሸጋ ነው!....ነፋስ ከሚያርመሰምሰው ጥቁር ፀጉሯ የሚመነጨውን የሻምፖና ኮንዲሽነር ሽታ ሳምባየን እንደሞላው ቁልቁል እንዲህ ያለም የለ እያልኩ😀 የሆነ ሆኖ በልደት ስጦታ ተጠቅልሎ ከሚመጣ ሞት ይጠብቃችሁ! እኔን አልፎኝ እዚህ ደርሻለሁ😀
#Share
#AlexAbreham
JOIN
@write_event
@write_event
@write_event
(አሌክስ አብርሃም)
ወገኖቸ መልካም ልደት የሚሏችሁን ሁሉ አትመኑ! አንዳንዶች የልደት በግ አልብሰው ቀበሮ ሞት ይልካሉና😀ከፈቀዳችሁልኝ ልምዴን ላካፍል? አመሠግናለሁ! በጣም እንደምትወደኝ ዘላለም ብኖር ደስ እንደሚላት የነገረችኝ ልጅ ባለፈው አመት ልደቴን ሳከብር በፖስጣ የታሸገ ስጦታ አመጣችልኝ...ፖስታው ባዶ ስለሚመስልና ውስጡ የሆነ ወረቀት ነገር ስለነበር በቃ ዶላር ይሆናል ብየ አሰብኩ... ሰዎች ስጦታ ለመምረጥ ለመግዛት ጊዜ ካጡ ካሹን መስጠት የተለመደ ነገር ነው! (ዶላርን በስሙ ብቻ የምታውቁና ነክታችሁት ለማታውቁ እኔ አሁኑኑ.......አብራራላችኋለሁ! ዶላር /አንዳንዶች ዳላር ይሉታል / እንደምላጭ የሳሳ ግን እንደምላጭ ስለታም የገንዘብ አይነት ነው ! ከአገራችሁ ጋር የተያያዛችሁበትን ጨምሮ የማይቆርጠው እትብት የማይላጨው ፀጋ የለም😀)
እና ቆንጆ አይኖቿን እያስለመለመች "ክፈተዋ " አለችኝ ፖስታውን ! ስከፍተው ትኬት ነው ... አይኔን ማመን አልቻልኩም ....Go Skydiving on your Birthday...
Jump two miles up with Amazing Views... ይላል! አቻ ትርጉሙ " ለልደት ቀንህ ለምን ሶስት ኪሎሜትር ወደሰማይ ወጥተህ ከአውሮፕላን ዘለህ እንደዱባ አትፈጠፈጥም ለመገፍተሩ እኛ አለንልህ " ማለት ነው 😀 ያው በሉት! ትኬቱ ከፍላችሁ ከአውሮፕላን ላይ በዣንጥላ መዝለያ ነው! ለልደቴ ማለት ነው ... እኔ ማለት ነው ....በዣንጥላ ከላይ ከሰማይ ማለት ነው ...
ወ
ደ
ታ
ች
"አታካብዳ ! "
"አካብዳለሁ ! ከፍታ አልወድም አልጋ ራሱ እየራቀብኝ ፍራሽ ላይ ነው የምተኛው" አልኩ! ለነገሩ ክብደት ለመስጠት!
"ብቻህን አይደለህምኮ ...አብሮህ የሚዘል ነጭ አለ ... " ትለኛለች ጭራሽ! እንደው ቢሆን እንኳ "Where Are You From? " እየተባልኩ ከመፈጥፈጥ ...ስር መሰረቴን ከሚያውቅ ከአገሬ ልጅ ጋራ ቁልቁል እያየን "ያ ሜዳ ጎዣምን አይመስልም?" እየተባባልን አብሬ ብፈጠፈጥ አይሻልም ? ሲሆን ሲሆን እንደግብፅ ነገስታት የሆነች ቆንጆ ጋር አስተሳስረው ወደሞቴ ቢልኩኝ ሸጋ ነው!....ነፋስ ከሚያርመሰምሰው ጥቁር ፀጉሯ የሚመነጨውን የሻምፖና ኮንዲሽነር ሽታ ሳምባየን እንደሞላው ቁልቁል እንዲህ ያለም የለ እያልኩ😀 የሆነ ሆኖ በልደት ስጦታ ተጠቅልሎ ከሚመጣ ሞት ይጠብቃችሁ! እኔን አልፎኝ እዚህ ደርሻለሁ😀
#Share
#AlexAbreham
JOIN
@write_event
@write_event
@write_event
🩸የሁለት ደቂቃ ንባብ
አትተርጉሙ!
አንድ አባት ከልጆቹ ጋር ወደ አንድ ካፌ ይገባል።ካፌው ውስጥ እንደገቡ ብዙም ሳይቀመጡ ልጆቹ መሯሯጥና እየተጯጯሁ መጫወት ይጀምራሉ።ይሄ ሁሉ ሲሆን አባት አንገቱን ደፍቶ በሀሳብ ጭልጥ ብሏል።ይሄን ሁሉ የሚመለከት አንድ ሰው በልጆቹ እንቅስቃሴ ተረብሾ ልጆቹን ስርአት የማያስይዝ ምን አይነት ቸልተኛ ሰው ነው እያለ በአባታቸውን ይናደዳል።በዚህ ብስጭት ውስጥ ሆኖ የሚሯሯጡት ልጆች ድንገት የእሱን ጠረጴዛ ነክተውት ኖሮ ያዘዘው ሻይ ልብሱ ላይ ተደፋ።ይሄን ጊዜ ንዴቱን መቋቋም አቅቶት ውደ አባትየው ሄደ።ለግጭት እየተጋበዘ ሊያንቀውም እየዳዳው”ምን አይነት የማትረባ ሰው ነህ?ልጆችህን ስርአት አታስይዝም?”ብሎ አምባረቀበት።አባትየው በረጅሙ ተንፍሶ በተረጋጋ አንደበት”ወዳጄ የልጅነት ሚስቴ የልጆቼ እናት ታማ ከምትረዳበት ሆስፒታል አሁን ከመግባታችን ተደውሎ መሞቷን ነገሩኝ።ምን ማድረግ እንዳለብኝና ለልጆቼ ምን እንደምል ግራ ገብቶኛል”አለው።ይሄን የሰማው ሰው በትልቅ ድንጋይ እንደተመታ ሰው ራሱን አመመው።
በህይወታችን ከምንሰራቸው ስህተቶች ውስጥ አንዱ ስለ ሁኔታዎች በቂ ግንዛቤ ሳይኖረን በራሳችን መተርጎምና መፈረጅ ነው።ሰዎች የሆነ ነገር ሲያደርጉ ስለማይወደኝ ነው፣ ስለማያከብረኝ ነው፣ ስልክ ሳያነሱ ወይ የሆነ ነገር ሲያደርጉ ሲቀሩ ደግሞ ሆም ብለው ነው ብለን በራሳችን እንተረጉማለን።የትርጉም ዋናው መዘዝ ከእውነታው አለም ያወጣንና የራሳችንን አለም እንደንፈጥር ያደርገናል።በህይወት ያሉትን ሰዎች እንገላቸውና ክፉ ናቸው አያከብሩኝም የምንላቸውን የራሳችንን ሰዎች በአዕምሯችን እንፈጥራለን።ሀሳባችንን ፊት ለፊት የመናገር ልምድ ስለሌለን በራሳችን ትርጉም በውስጣችንን እንበሰለሰላለን እንጎዳለን።መፍትሄው ምንድን ነው?
1.ምቾት ያልሰጡን ነገሮች ሲኖሩ በራሳችን ከመተርጎም ይልቅ ፊት ለፊት መጠየቅን እንለማመድ።
2.ያሰብኩትና የተሰማኝ ሁሉ ትክክል ነው ማለትን እናቁም።
3.ሰዎች በብዙ ችግርና ውስብስብ የህይወት መንገድ ያልፋሉና ለመረዳት እንሞክር።በዚህ መልኩ ጤናማ ግንኙነታችንን ማዳበር እንችላለን።
@write_event
@write_event
@write_event
ሲሞት!
ደረት መቺ አፈር ዘጋኝ
የጨከነ ሁሉ አዛኝ
ሲሞት!
ካርታ ቁማር ገባ ወጣ
እራት ምስር እስኪመጣ
ጋቢ መልበስ ድንኳን መጣል
ወጪ ማብዛት አልፏል ሲባል
ሲኖር!!
ኑሮ ከብዶ ሲደቁሰው
ሚቀምሰው አቶ ሆድ ሲብሰው
የረገጠው ሁሉ ሲመክን
ያዝኩት ያለው በኖ ሲመን
አይዞህ ያላለው በድን ስጋ
ሞተ ሲባል ያርዳል ሰንጋ
በ ኪሩቤል አሰፋ
@write_event
ደረት መቺ አፈር ዘጋኝ
የጨከነ ሁሉ አዛኝ
ሲሞት!
ካርታ ቁማር ገባ ወጣ
እራት ምስር እስኪመጣ
ጋቢ መልበስ ድንኳን መጣል
ወጪ ማብዛት አልፏል ሲባል
ሲኖር!!
ኑሮ ከብዶ ሲደቁሰው
ሚቀምሰው አቶ ሆድ ሲብሰው
የረገጠው ሁሉ ሲመክን
ያዝኩት ያለው በኖ ሲመን
አይዞህ ያላለው በድን ስጋ
ሞተ ሲባል ያርዳል ሰንጋ
በ ኪሩቤል አሰፋ
@write_event
❤1
‹‹መኪና፡)
(አሌክስ አብርሃም)
መቸስ ለአንድ ኢትዮጲያዊ መኪና ማለት ምን እንደሆነ ታውቁታላችሁ …መኪናኮ ድፍን ሁለት ሰዓት ስለተወራለት ‹‹ኧረ አሁንስ በዛ›› የሚባልለት ንብረት አይደለም …መኪና ድፍን ሁለት ሰዓት ተሰልፈን በናፍቆት የምንጠብቀው ‹‹ምፅዓት›› ነገር ነው ለእኛ ለኢትዮጲያዊያን !
መኪናኮ መንግስት ሰልፍ በከለከለበት አገር ‹‹መሰለፍ መብታችሁ ነው በየውስጣችሁ የብሶት መፎክር ይዛችሁ ተሰለፉ ›› ያለን መቶ ፐርሰንት ሳንመርጠው ለመብታችን የቆመ የማያንቀላፋ ወኪላችን ነው ….መኪናኮ ‹‹እከሊትኮ ባል አላት›› ከመባል በላይ ‹‹እከሊትኮ መኪና ያለው ባል አላት›› እስከማስባል የሚደርስ ስሙ እንደማእረግ ከማንነታችን በፊት የሚቀድም ንብረት ነው ….መኪናኮ ከወረርሽኝ በላይ በየቀኑ ስንቱን የሚረሽን አምባገነን እቃ ነው !! መኪናኮ ቁጭ ሲሉበት ወንበሩ ከፓርላማ ወንበር በላይ የሚመች ንብረት ነው ….:)
መኪናኮ በብዙ አማርኛ ፊልሞቻችን ላይ ራሱን ችሎ አንድ ገፀ ባህሪ የመሆን አቅም ያለው ‹‹ግኡዝ ታዋቂ ›› ነው መኪናኮ …..ተው እንጅ ሆድ አታስብሱኝ ወገኖቸ ….፡)
እና ከሰሞኑ አንድ ጓደኛየ መኪና ሊገዛ እኔም ላገዛዛው ስንዞር እንደነበር ነግሪያችሁ ነበር …ኧረ እናንተም በማማከር ከጎናችን ነበራችሁ …በእርግጥ አንዳንድ እህቶች ‹‹አሌክሶ የጓደኛህን ስልክ ስጠን›› ያላችሁኝ ነገር ትንሽ አሳዝኖኛል …እኔ ይሄን ያህል አመት እያሰለቸሁ ሳስተምራችሁ(እያዝናኑ ማስተማር ከሚለው የተወሰደ) አንዲት ሴት ስልኬን ጠይቃኝ የማታውቀውን ዛሬ ነጭ ይሁን ጥቁር የማይታወቅ ጓደኛየ ስልክ መጠየቃችሁ አንገብግቦኛል፡)!!(ቀልድ ነው!! መኪና በአሁኑ ሰዓት ጫማ ማለት ነው የሚሉ እህቶች ያልተገዛውን መኪና ሲያናንቁ ታየኝ …ጫማ ራሱ በአሁኑ ሰዓት መኪና ሁኖ የለ እንዴ ተው እንጅ፡)
ወደዋናው ጉዳየ ስገባ (እስካሁን አልገባህም ወይ? በእግሬ እኮ ነው የምጓዘው ቀስ ብየ ብደርስ ምን ያስገርማል…ገና ለገና ጓደኛው መኪና ሊገዛ ነው ተብሎማ ማጣደፍ ነውር ነው፡)) እና ደላላው ምን አለን … ‹‹ይሄ መኪና አሪፍ ነው በሴት እጅ ነው የቆየው›› እንዴ ምን አገናኘው ስል …ሴቶች የሚይዟቸው መኪናዎች ከአመታት በኋላ እንኳን ገና ከፋብሪካ የወጡ ነው የሚመስሉት የሚል ምላሽ ተሰጠኝ … በቃ ሴቶች መኪና ከገዙ እንደህፃን ልጅ ነው የሚጠነቀቁለት … ወላ ከባል በላይ:) ቸግሯቸውም ይሁን የተሻለ መኪና ለመግዛት ሲሸጡት ታዲያ መኪናቸው ከዱባይ የተጫነ እንጅ አዲስ አበባ መንገዶች ላይ የተነዳ አይመስልም …አለን ደላላው !
ገረመኝ ሴቶች እንዲህ ጥንቁቅ ንብረት ተንከባካቢ ከሆኑ የከተማ አውቶብሶቻችንን ሴቶች ይያዙልን ….ባቡሩን ሴቶች ይያዙልን …እንደውም ድሪም ላይነራችንን ሴቶች ያብርሩልን ታንኮቻችንን ሳይቀር ሴት የመከላከያ ሰራዊት አባሎቻችን ይያዙልን ….እያልኩ አሰብኩና በኋላ ውልና ማስረጃ ለሌላ ጉዳይ ጎራ ስል አንዳንድ የተፋቱ ባልና ሚስቶች የንብረት ጉዳይ ሲጨራርሱ እና ሲለያዩ በመመልከቴ ሃሳቤን ቆም ብየ ለመከለስ ተገደድኩ....
እውነቱን ለመናገር ተፋቾቹ ሚስቶች ያማረባቸው.. ውበት ከደም ግባት ጢም አድርጎ የሞላቸው.... ተፋች ሳይሆን ሙሽራ የሚመሳስሉ ፈገግታቸው ከትዳር ሳይሆን ከቅሊንጦ የተለቀቁ የሚያስመስላቸው ነበሩ ...... ወንዶቹ ግን አንጀት የራቃቸው ... ፀጉራቸው የተንጨባረረ ... ቀበቷቸውን እንኳን በስርአት ያልታጠቁ ( ጠ/ሚንስትርኮ ቀበቶ እንኳን በስርዓት ለመታጠቅ ጊዜ አልነበራቸውም አለች ያች ልጅ፡)) በቃ ጉስቁል ያሉ ናቸው … እና ብዙዎቹ ተፋቾች ደግሞ ስለቤትና መኪና ክፍፍል ጉዳይ ነው የሚያወሩት …መቸም ፍች ያሳዝናል …ሰው አንድ አካል አንድ አምሳል የተባለ አጋሩ ጋር በጥላቻ ጎራዴ ተከፍሎ ተጥሎ ስለንብረት ክፍፍል ወገቡን ገትሮ ሲከራከር ማየት …አያድርስ ነው ( ለነገሩ ውስጡን ማን አየ!)
ታዲያ ምን አሰብኩ እኒህ ‹‹አንዳንድ የአዲስ አበባ ባለመኪና ተፋች ሴቶች ›› መኪናቸው አዲስና ያማረበት የሚፈቷቸው ባሎቻቸው ግን ጎስቋላና ውሃ ውስጥ ተነክራ የወጣች ድመት የሚመስሉት በምን ምክንያት ነው ብየ አሰብኩ …. ከምር አሰብኩ ….ከአድሎ ነፃ ሁኘ ስለወንዶች አሰብኩ፡) ሴቶቹ መኪናዎቻቸውን እቤት አቁመው በአዲስ አበባ ወጣ ገባ መንገዶች ላይ ባሎቻቸውን ነበር እንዴ ሲነዱ የኖሩት?:) ብየ አሰብኩ !! እኛ አንዳንድ ኢትዮጲያዊያን ባሎች ለመኪናን የሚደረገውን ያህል እንክብካቤ ከሚስቶቻችን እንዳላገኘን ተሰማኝ … ስለዚህ የሰርጋችን ለት በመኪና የታጀብን መስሎን ተሸወድን እንጅ ለካስ ባሎች ሽክ ብለንና ተሰባስበን መኪና ማጀባችን ነበር ሰርጉ፡) የሚል ሃሳብ ሽው አለብኝ ! በዚህ የመኪና ፍቅር ሚስቴን ደውየ ‹‹ሃኒየ መኪና ገጨኝ ›› ብላት ምን ልትለኝ እንደምትችል አሰብኩ ‹‹ አንተሰውየ ግን ለምን ከጥሩ ንብረቶች ጋር ትጋጫለህ ኧረ ተው ፀባይ ይኑርህ››፡)
እና እንዲህ እያልኩ ሳስብ አንድ ባልና ሚስት እየተሰዳደቡ ንብረት ክፍፍል ወረቀታቸው ላይ ይፈርማሉ ከንግግራቸው እንደተረዳሁት ባል ያለፈለት ይችን ሴትዮ ካገባ በኋላ ይመስለኛል እና ሴቲቱ እንዲህ ስትል አሽሙር ተናገረች ‹‹ከእያንዳንዱ ስኬታማ ወንድ በስተጀርባ ጠንካራ ሴት አለች›› እድሜ ለኔ በል ከኋላህ ባልኖር ደሃ መንዳካ ሁነህ ትቀራት ነበር ይመስላል ንግግሩ
ባልም እየፈረመ እንዲህ ሲል ተናገረ ‹‹ ድሮስ ከተሳካለት ወንድ ኋላ ኋላ ከመከተል ውጭ ሌላ ምን ስራ አላችሁ ቆንጆ ሚስቶች፡)››
አንድ የዋህ የሚመስል ከጎኔ የተቀመጠ ሰው ህህህህህህህ ብሎ ሳቀና እንዲህ አለ … ‹‹ይሄ ሰውየ አሁንም ሚስቱን ያፈቅራታል››
‹‹በምን አወክ አልኩት›› ተገርሜ እያየሁት
‹‹ሚስቱን እየተፋቱም ቆንጆ ይላታል ህህህህህህህ›› ከዚህ ጅል ወንድ ጀርባ ምናይነት ሴት ትኖር ይሆን ብየ እያሰብኩ ዘወር ስል ከኋላየ ቆንጅየ ልጅ ቁማለች ‹‹ ስኬታማ ሆንኩ እንዴ›› ብየ አሰብኩና ወዲያው ከጎኔ የቆመው ሰውየ ጅልነት የተጋባባኝ መስሎኝ በውስጤ ህህህህህህህ ብየ ሳኩ ! የሆነ ሁኖ አንዳንድ ሴቶች ከሚስትነት በላይ የሹፍርና ተሰጥኦ እንዳላቸው ጠረጠርኩ …ይሄ ጥሩ ሃሳብ ነው… ከሹፌር ሴት ኋላ ተሳፋሪ ወንድ ይኖራል ይሄም የተፋቹን ባል አሽሙር ውድቅ ያደርገዋል …
በነገራችን ላይ የሚፈታት ሚስቱ ቆንጆ ነች …እንደውም ለፊርማ ስክርቢቶ ሳቀብላት የሚያምር ፈገግታዋን አሻረችኝ ….ባልየው በግልምጫ አንስቶ አፈረጠኝ ‹‹እየተፋታም ይቀናል እንዴ ..ወይስ ፈገግታዋንም በውልና ማስረጃ በኩል ግማሹ ይገባኛል ብሎ ሊረካከብ አስቧል ይሄንንስ እንኳን ፈታችው›› …በየ ሳልጨርስ...
ወዲያው ይች ቆንጆ ሚስቱ እኔ ያዋስኳትን እስክርቢቱ ፈገግ ብላ ላላዋሳት ልጅ ስትመልስ አየሁ ቀልበ ቢስ!...ደግሞ እንጅ የልጁ …ያላዋሰውን ስክርቢቶ ቆንጆ ሴት ስለሰጠችው ብቻ ካለሃቁ ፈገግ ብሎ ይቀበላል እንዴ …ሆሆ !ይሄ ወረቀት አቀብላ ‹‹ፈርም›› ብትለውም ምንድነው ሳይል ነው ፊርማውን የሚገጠግጠው! ‹‹የዞረባት ይችንስ እንኳን ፈታት›› አልኩ፡) ከእያንዳንዷ ቆንጆ ሴት ጀርባ ያላዋሳትን ስክርቢቶ ለመቀበል ያሰፈሰፈ ወንድ አለ ለካ !!
ሀህሀህሀህሀህሀህሀህ አለ ይሄ ጅል !!
እውነትም ህህህህህ ወደው አይጀሉ !!
@write_event
@write_event
@write_event
😍
(አሌክስ አብርሃም)
መቸስ ለአንድ ኢትዮጲያዊ መኪና ማለት ምን እንደሆነ ታውቁታላችሁ …መኪናኮ ድፍን ሁለት ሰዓት ስለተወራለት ‹‹ኧረ አሁንስ በዛ›› የሚባልለት ንብረት አይደለም …መኪና ድፍን ሁለት ሰዓት ተሰልፈን በናፍቆት የምንጠብቀው ‹‹ምፅዓት›› ነገር ነው ለእኛ ለኢትዮጲያዊያን !
መኪናኮ መንግስት ሰልፍ በከለከለበት አገር ‹‹መሰለፍ መብታችሁ ነው በየውስጣችሁ የብሶት መፎክር ይዛችሁ ተሰለፉ ›› ያለን መቶ ፐርሰንት ሳንመርጠው ለመብታችን የቆመ የማያንቀላፋ ወኪላችን ነው ….መኪናኮ ‹‹እከሊትኮ ባል አላት›› ከመባል በላይ ‹‹እከሊትኮ መኪና ያለው ባል አላት›› እስከማስባል የሚደርስ ስሙ እንደማእረግ ከማንነታችን በፊት የሚቀድም ንብረት ነው ….መኪናኮ ከወረርሽኝ በላይ በየቀኑ ስንቱን የሚረሽን አምባገነን እቃ ነው !! መኪናኮ ቁጭ ሲሉበት ወንበሩ ከፓርላማ ወንበር በላይ የሚመች ንብረት ነው ….:)
መኪናኮ በብዙ አማርኛ ፊልሞቻችን ላይ ራሱን ችሎ አንድ ገፀ ባህሪ የመሆን አቅም ያለው ‹‹ግኡዝ ታዋቂ ›› ነው መኪናኮ …..ተው እንጅ ሆድ አታስብሱኝ ወገኖቸ ….፡)
እና ከሰሞኑ አንድ ጓደኛየ መኪና ሊገዛ እኔም ላገዛዛው ስንዞር እንደነበር ነግሪያችሁ ነበር …ኧረ እናንተም በማማከር ከጎናችን ነበራችሁ …በእርግጥ አንዳንድ እህቶች ‹‹አሌክሶ የጓደኛህን ስልክ ስጠን›› ያላችሁኝ ነገር ትንሽ አሳዝኖኛል …እኔ ይሄን ያህል አመት እያሰለቸሁ ሳስተምራችሁ(እያዝናኑ ማስተማር ከሚለው የተወሰደ) አንዲት ሴት ስልኬን ጠይቃኝ የማታውቀውን ዛሬ ነጭ ይሁን ጥቁር የማይታወቅ ጓደኛየ ስልክ መጠየቃችሁ አንገብግቦኛል፡)!!(ቀልድ ነው!! መኪና በአሁኑ ሰዓት ጫማ ማለት ነው የሚሉ እህቶች ያልተገዛውን መኪና ሲያናንቁ ታየኝ …ጫማ ራሱ በአሁኑ ሰዓት መኪና ሁኖ የለ እንዴ ተው እንጅ፡)
ወደዋናው ጉዳየ ስገባ (እስካሁን አልገባህም ወይ? በእግሬ እኮ ነው የምጓዘው ቀስ ብየ ብደርስ ምን ያስገርማል…ገና ለገና ጓደኛው መኪና ሊገዛ ነው ተብሎማ ማጣደፍ ነውር ነው፡)) እና ደላላው ምን አለን … ‹‹ይሄ መኪና አሪፍ ነው በሴት እጅ ነው የቆየው›› እንዴ ምን አገናኘው ስል …ሴቶች የሚይዟቸው መኪናዎች ከአመታት በኋላ እንኳን ገና ከፋብሪካ የወጡ ነው የሚመስሉት የሚል ምላሽ ተሰጠኝ … በቃ ሴቶች መኪና ከገዙ እንደህፃን ልጅ ነው የሚጠነቀቁለት … ወላ ከባል በላይ:) ቸግሯቸውም ይሁን የተሻለ መኪና ለመግዛት ሲሸጡት ታዲያ መኪናቸው ከዱባይ የተጫነ እንጅ አዲስ አበባ መንገዶች ላይ የተነዳ አይመስልም …አለን ደላላው !
ገረመኝ ሴቶች እንዲህ ጥንቁቅ ንብረት ተንከባካቢ ከሆኑ የከተማ አውቶብሶቻችንን ሴቶች ይያዙልን ….ባቡሩን ሴቶች ይያዙልን …እንደውም ድሪም ላይነራችንን ሴቶች ያብርሩልን ታንኮቻችንን ሳይቀር ሴት የመከላከያ ሰራዊት አባሎቻችን ይያዙልን ….እያልኩ አሰብኩና በኋላ ውልና ማስረጃ ለሌላ ጉዳይ ጎራ ስል አንዳንድ የተፋቱ ባልና ሚስቶች የንብረት ጉዳይ ሲጨራርሱ እና ሲለያዩ በመመልከቴ ሃሳቤን ቆም ብየ ለመከለስ ተገደድኩ....
እውነቱን ለመናገር ተፋቾቹ ሚስቶች ያማረባቸው.. ውበት ከደም ግባት ጢም አድርጎ የሞላቸው.... ተፋች ሳይሆን ሙሽራ የሚመሳስሉ ፈገግታቸው ከትዳር ሳይሆን ከቅሊንጦ የተለቀቁ የሚያስመስላቸው ነበሩ ...... ወንዶቹ ግን አንጀት የራቃቸው ... ፀጉራቸው የተንጨባረረ ... ቀበቷቸውን እንኳን በስርአት ያልታጠቁ ( ጠ/ሚንስትርኮ ቀበቶ እንኳን በስርዓት ለመታጠቅ ጊዜ አልነበራቸውም አለች ያች ልጅ፡)) በቃ ጉስቁል ያሉ ናቸው … እና ብዙዎቹ ተፋቾች ደግሞ ስለቤትና መኪና ክፍፍል ጉዳይ ነው የሚያወሩት …መቸም ፍች ያሳዝናል …ሰው አንድ አካል አንድ አምሳል የተባለ አጋሩ ጋር በጥላቻ ጎራዴ ተከፍሎ ተጥሎ ስለንብረት ክፍፍል ወገቡን ገትሮ ሲከራከር ማየት …አያድርስ ነው ( ለነገሩ ውስጡን ማን አየ!)
ታዲያ ምን አሰብኩ እኒህ ‹‹አንዳንድ የአዲስ አበባ ባለመኪና ተፋች ሴቶች ›› መኪናቸው አዲስና ያማረበት የሚፈቷቸው ባሎቻቸው ግን ጎስቋላና ውሃ ውስጥ ተነክራ የወጣች ድመት የሚመስሉት በምን ምክንያት ነው ብየ አሰብኩ …. ከምር አሰብኩ ….ከአድሎ ነፃ ሁኘ ስለወንዶች አሰብኩ፡) ሴቶቹ መኪናዎቻቸውን እቤት አቁመው በአዲስ አበባ ወጣ ገባ መንገዶች ላይ ባሎቻቸውን ነበር እንዴ ሲነዱ የኖሩት?:) ብየ አሰብኩ !! እኛ አንዳንድ ኢትዮጲያዊያን ባሎች ለመኪናን የሚደረገውን ያህል እንክብካቤ ከሚስቶቻችን እንዳላገኘን ተሰማኝ … ስለዚህ የሰርጋችን ለት በመኪና የታጀብን መስሎን ተሸወድን እንጅ ለካስ ባሎች ሽክ ብለንና ተሰባስበን መኪና ማጀባችን ነበር ሰርጉ፡) የሚል ሃሳብ ሽው አለብኝ ! በዚህ የመኪና ፍቅር ሚስቴን ደውየ ‹‹ሃኒየ መኪና ገጨኝ ›› ብላት ምን ልትለኝ እንደምትችል አሰብኩ ‹‹ አንተሰውየ ግን ለምን ከጥሩ ንብረቶች ጋር ትጋጫለህ ኧረ ተው ፀባይ ይኑርህ››፡)
እና እንዲህ እያልኩ ሳስብ አንድ ባልና ሚስት እየተሰዳደቡ ንብረት ክፍፍል ወረቀታቸው ላይ ይፈርማሉ ከንግግራቸው እንደተረዳሁት ባል ያለፈለት ይችን ሴትዮ ካገባ በኋላ ይመስለኛል እና ሴቲቱ እንዲህ ስትል አሽሙር ተናገረች ‹‹ከእያንዳንዱ ስኬታማ ወንድ በስተጀርባ ጠንካራ ሴት አለች›› እድሜ ለኔ በል ከኋላህ ባልኖር ደሃ መንዳካ ሁነህ ትቀራት ነበር ይመስላል ንግግሩ
ባልም እየፈረመ እንዲህ ሲል ተናገረ ‹‹ ድሮስ ከተሳካለት ወንድ ኋላ ኋላ ከመከተል ውጭ ሌላ ምን ስራ አላችሁ ቆንጆ ሚስቶች፡)››
አንድ የዋህ የሚመስል ከጎኔ የተቀመጠ ሰው ህህህህህህህ ብሎ ሳቀና እንዲህ አለ … ‹‹ይሄ ሰውየ አሁንም ሚስቱን ያፈቅራታል››
‹‹በምን አወክ አልኩት›› ተገርሜ እያየሁት
‹‹ሚስቱን እየተፋቱም ቆንጆ ይላታል ህህህህህህህ›› ከዚህ ጅል ወንድ ጀርባ ምናይነት ሴት ትኖር ይሆን ብየ እያሰብኩ ዘወር ስል ከኋላየ ቆንጅየ ልጅ ቁማለች ‹‹ ስኬታማ ሆንኩ እንዴ›› ብየ አሰብኩና ወዲያው ከጎኔ የቆመው ሰውየ ጅልነት የተጋባባኝ መስሎኝ በውስጤ ህህህህህህህ ብየ ሳኩ ! የሆነ ሁኖ አንዳንድ ሴቶች ከሚስትነት በላይ የሹፍርና ተሰጥኦ እንዳላቸው ጠረጠርኩ …ይሄ ጥሩ ሃሳብ ነው… ከሹፌር ሴት ኋላ ተሳፋሪ ወንድ ይኖራል ይሄም የተፋቹን ባል አሽሙር ውድቅ ያደርገዋል …
በነገራችን ላይ የሚፈታት ሚስቱ ቆንጆ ነች …እንደውም ለፊርማ ስክርቢቶ ሳቀብላት የሚያምር ፈገግታዋን አሻረችኝ ….ባልየው በግልምጫ አንስቶ አፈረጠኝ ‹‹እየተፋታም ይቀናል እንዴ ..ወይስ ፈገግታዋንም በውልና ማስረጃ በኩል ግማሹ ይገባኛል ብሎ ሊረካከብ አስቧል ይሄንንስ እንኳን ፈታችው›› …በየ ሳልጨርስ...
ወዲያው ይች ቆንጆ ሚስቱ እኔ ያዋስኳትን እስክርቢቱ ፈገግ ብላ ላላዋሳት ልጅ ስትመልስ አየሁ ቀልበ ቢስ!...ደግሞ እንጅ የልጁ …ያላዋሰውን ስክርቢቶ ቆንጆ ሴት ስለሰጠችው ብቻ ካለሃቁ ፈገግ ብሎ ይቀበላል እንዴ …ሆሆ !ይሄ ወረቀት አቀብላ ‹‹ፈርም›› ብትለውም ምንድነው ሳይል ነው ፊርማውን የሚገጠግጠው! ‹‹የዞረባት ይችንስ እንኳን ፈታት›› አልኩ፡) ከእያንዳንዷ ቆንጆ ሴት ጀርባ ያላዋሳትን ስክርቢቶ ለመቀበል ያሰፈሰፈ ወንድ አለ ለካ !!
ሀህሀህሀህሀህሀህሀህ አለ ይሄ ጅል !!
እውነትም ህህህህህ ወደው አይጀሉ !!
@write_event
@write_event
@write_event
😍
ጠበኛ እውነቶች
ደራሲ:- ሜሪ ፈለቀ
"እናትሽ በጠና ታማለች። እባክሽ ልታይሽ ትፈልጋለች።"
ለአራተኛ ጊዜ የተላከልኝ መልዕክት ነው።
"እስካሁን አልሞተችም እንዴ? ለምን ታጓጓኛለች? አንዳችሁ እንኳን ምናለ ‘ሞተች’ የሚል ብስራት ብታሰሙኝ?"
"በስመ አብ ወ ወልድ ወ መንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ!! (ገዳዳ መስቀል በሰራ እጁ እያማተበ) ምነው ልጄ? ምን የሚሉት ጭካኔ ነው? ደግም አይደል! እግዜርም አይወደው።"
መልሴ አንገሽግሾታል። ሀምሳ ዓመት የሚያልፈው ሰውዬ ነው። የወለደችኝ ሴትዮ የነፍስ አባቷ ነው።
"በናትህ ከቤቴ ውጣልኝ!!"
"ምነው ልጄ? እግዜር የሰጠኝን ሹመት ባታከብሪ በእድሜ አባትሽ አልሆንም?" የሚናገረው ቃል የለዘበ ይሁን እንጂ ቀይ ወጥ የመሰለ ግለታም ዓይኑ እንደተጠየፈኝ ያሳብቅበታል።
እድሜውን ሳይሆን የለበሰውን የቤተ ክህነት ልብስ ባከብር ደስ ባለኝ ግን ለባሹ ልብሱን እንጂ ልብሱ ለባሹን እንዴት ሊያስከብረው ይችላል? ልብሱ ይሄን ከንቱ ሰውዬ እንዴት ክቡር ሊያደርገው ይችላል? መሆን የነበረበት ልብሱ ተገፎ ለተከበረ ሰው መደረብ ነበር። ያኔ ልብሱም ለባሹም ይከበራሉ።
መጎናፀፊያ አካልን ይሸፍን ይሆናል፤ ምናልባትም የአካል እንከንን የነፍስ ሴሰኝነት ግን በልብስ አይሸፈንም። ዝቃጭ ምግባር ግን ለቅድስና ሌት ተቀን ለሚታገሉ ልበ ብርቱዎች በተዘጋጀ መደረቢያ አይከለልም። በሱ ቤት እኔ ከእናቴ ጋር የሚሰራውን ብልግና አላውቅበትም። የናቴ ውሽማዋ ነው።
ይሄኔ በየመቅደሱ ‘ሰው የዘራውን ያጭዳል’ እያለ ይቦጠለቃል። እሱ ግን ያልዘራውን ለማጨድ በሰው እርሻ ይኳትናል።
ሴሰኝነትን እየዘራ መከበርን ለማጨድ ማጭድ ይስላል። ከንቱ!!
ይሄኔ ስንቶች ስንጥር ለምታክል በደላቸው ንሰሃን ሽተው ከፊቱ ሲመጡ ዋርካ የሚያክል ስድነቱን በብብቱ ሸሽጎ ልባቸው ለንሰሃ እንዲሰበር ዘክሯል። የዘቀጠ!! የእናቴን ጣር ላይ መሆን ሊነግሩኝ እንደመጡት ሶስቱ እሱም
እየተፀየፈኝ ቤቴን ለቆ ወጣ።
(ከመፅሃፉ ገፆች የተቆረሰ)
#share -----> @write_event
@write_event
ደራሲ:- ሜሪ ፈለቀ
"እናትሽ በጠና ታማለች። እባክሽ ልታይሽ ትፈልጋለች።"
ለአራተኛ ጊዜ የተላከልኝ መልዕክት ነው።
"እስካሁን አልሞተችም እንዴ? ለምን ታጓጓኛለች? አንዳችሁ እንኳን ምናለ ‘ሞተች’ የሚል ብስራት ብታሰሙኝ?"
"በስመ አብ ወ ወልድ ወ መንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ!! (ገዳዳ መስቀል በሰራ እጁ እያማተበ) ምነው ልጄ? ምን የሚሉት ጭካኔ ነው? ደግም አይደል! እግዜርም አይወደው።"
መልሴ አንገሽግሾታል። ሀምሳ ዓመት የሚያልፈው ሰውዬ ነው። የወለደችኝ ሴትዮ የነፍስ አባቷ ነው።
"በናትህ ከቤቴ ውጣልኝ!!"
"ምነው ልጄ? እግዜር የሰጠኝን ሹመት ባታከብሪ በእድሜ አባትሽ አልሆንም?" የሚናገረው ቃል የለዘበ ይሁን እንጂ ቀይ ወጥ የመሰለ ግለታም ዓይኑ እንደተጠየፈኝ ያሳብቅበታል።
እድሜውን ሳይሆን የለበሰውን የቤተ ክህነት ልብስ ባከብር ደስ ባለኝ ግን ለባሹ ልብሱን እንጂ ልብሱ ለባሹን እንዴት ሊያስከብረው ይችላል? ልብሱ ይሄን ከንቱ ሰውዬ እንዴት ክቡር ሊያደርገው ይችላል? መሆን የነበረበት ልብሱ ተገፎ ለተከበረ ሰው መደረብ ነበር። ያኔ ልብሱም ለባሹም ይከበራሉ።
መጎናፀፊያ አካልን ይሸፍን ይሆናል፤ ምናልባትም የአካል እንከንን የነፍስ ሴሰኝነት ግን በልብስ አይሸፈንም። ዝቃጭ ምግባር ግን ለቅድስና ሌት ተቀን ለሚታገሉ ልበ ብርቱዎች በተዘጋጀ መደረቢያ አይከለልም። በሱ ቤት እኔ ከእናቴ ጋር የሚሰራውን ብልግና አላውቅበትም። የናቴ ውሽማዋ ነው።
ይሄኔ በየመቅደሱ ‘ሰው የዘራውን ያጭዳል’ እያለ ይቦጠለቃል። እሱ ግን ያልዘራውን ለማጨድ በሰው እርሻ ይኳትናል።
ሴሰኝነትን እየዘራ መከበርን ለማጨድ ማጭድ ይስላል። ከንቱ!!
ይሄኔ ስንቶች ስንጥር ለምታክል በደላቸው ንሰሃን ሽተው ከፊቱ ሲመጡ ዋርካ የሚያክል ስድነቱን በብብቱ ሸሽጎ ልባቸው ለንሰሃ እንዲሰበር ዘክሯል። የዘቀጠ!! የእናቴን ጣር ላይ መሆን ሊነግሩኝ እንደመጡት ሶስቱ እሱም
እየተፀየፈኝ ቤቴን ለቆ ወጣ።
(ከመፅሃፉ ገፆች የተቆረሰ)
#share -----> @write_event
@write_event
"ውበትን የምታገኙት የማይታየውን ስታዩ ነው፤ በግልፅ ያልሆነውን ስትረዱ ነው፤ ድምፅ የሌለውን ንግግር ስትስሙ ነው፡፡ ውበት፣ በውስጣችሁ ተጀምሮ ከሥጋዊ ፍላጐቶቻችሁ ባሻገር የሚያበቃ ድንቅ የሀዘንና ደስታ ውህድ ነው፡፡ ልቦና ውስጥ የሚገኝ ብርሃን ነው።"
ካህሊል ጂብራን
Join: https://telegram.me/Write_Event
ካህሊል ጂብራን
Join: https://telegram.me/Write_Event
Telegram
እኛ እና የኛ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
ጥሬ ጨዉ
=========
መስለዉኝ ነበረ
የበቁ የነቁ
ያወቁ የረቀቁ
የሰዉ ፍጡሮች
ለካ እነሱ ናቸዉ
ጥሬ ጨዉ…ጥሬ ጨዉ ጥሬ ጨዋዎች
መፈጨት-መሰለቅ-መደለዝ-መወቀጥ-
መታሸት መቀየጥ
ገና እሚቀራቸዉ
“እኔ የለሁበትም!”
የዘወትር ቋንቋቸዉ።
___
ደበበ ሰይፉ
@Write_Event
@Write_Event
=========
መስለዉኝ ነበረ
የበቁ የነቁ
ያወቁ የረቀቁ
የሰዉ ፍጡሮች
ለካ እነሱ ናቸዉ
ጥሬ ጨዉ…ጥሬ ጨዉ ጥሬ ጨዋዎች
መፈጨት-መሰለቅ-መደለዝ-መወቀጥ-
መታሸት መቀየጥ
ገና እሚቀራቸዉ
“እኔ የለሁበትም!”
የዘወትር ቋንቋቸዉ።
___
ደበበ ሰይፉ
@Write_Event
@Write_Event
" # እጅ_ከፍንጅ "?
-
አንዲት ባለትዳር ፥ በጓዳዋ ሳለች ፥ ጉንዳን ቆነጠጣት
ከእግር እስከ ራሷ ፥ ተርመስምሶ ገብቶ ፥ ነክሶ ፋታ አሳጣት
-
ይሄን ጊዜ ጮኸች፤
ልብሶቿን አራግፋ ፥ ራቁቷን ቀረች!
-
ጩኸቷን የሰማ ፥ ላጤ ጎረቤቷ ፥ ገባ ተንደርድሮ
ያቺን ቆንጆ እንስት ፥ እርቃኗን ሲያያት ፥ ቀረ ተገትሮ!
-
በዚህ ሁነት መሃል ፥ ሰይጣን አይኑን ሲጥል ፥ ባል ድንገት
ይደርሳል
ሰበብ የጠፋ 'ለት ፥ የጉንዳን ወረራ ፥ ትዳርን ያፈርሳል ።
---------//----------
(✍ በርናባስ ከበደ )
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
-
አንዲት ባለትዳር ፥ በጓዳዋ ሳለች ፥ ጉንዳን ቆነጠጣት
ከእግር እስከ ራሷ ፥ ተርመስምሶ ገብቶ ፥ ነክሶ ፋታ አሳጣት
-
ይሄን ጊዜ ጮኸች፤
ልብሶቿን አራግፋ ፥ ራቁቷን ቀረች!
-
ጩኸቷን የሰማ ፥ ላጤ ጎረቤቷ ፥ ገባ ተንደርድሮ
ያቺን ቆንጆ እንስት ፥ እርቃኗን ሲያያት ፥ ቀረ ተገትሮ!
-
በዚህ ሁነት መሃል ፥ ሰይጣን አይኑን ሲጥል ፥ ባል ድንገት
ይደርሳል
ሰበብ የጠፋ 'ለት ፥ የጉንዳን ወረራ ፥ ትዳርን ያፈርሳል ።
---------//----------
(✍ በርናባስ ከበደ )
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
🙏1
።።።ምን አገባኝ ።።።
እኔ ምን አገባኝ
የምትሉት ሀረግ
እሱ ነዉ አገሬን
ያረዳት እንደ በግ
ብዬ ግጥም ልፅፍ
ብድግ አልኩኝና
ምን አገባኝ ብዬ
ቁጭ አልኩ እንደገና
(በእውቀቱ ስዩም)
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
እኔ ምን አገባኝ
የምትሉት ሀረግ
እሱ ነዉ አገሬን
ያረዳት እንደ በግ
ብዬ ግጥም ልፅፍ
ብድግ አልኩኝና
ምን አገባኝ ብዬ
ቁጭ አልኩ እንደገና
(በእውቀቱ ስዩም)
@Write_Event
@Write_Event
@Write_Event
ጎ ጆ ቤ ት
┈•✦•┈
✍ እንዳለጌታ ከበደ
'
ሀገርስ ጎጆ ናት!!!
መሪዋም ምሰሶ
ሹማምንቷም ማገር
አንዳንዶቹም ቋሚ
ሌሎቹም ወጋግራ
ሠራዊቷም አጥር!
ሀገርስ ጎጆ ናት!!!
ሕዝቡም ክዳን ሆኖ
ጎጆውን አልብሶ
እንደሳር ቢቀጥን፤
ቢኖር ተራ መስሎ
ከዝናብ ያድናል፤
ውርጩን አሰናብቶ
ፀሐይን ይከላል፤
በጥላው ከልሎ ...
ሀገርስ ጎጆ ናት!!!
እውነትም ጎጆ ናት
ሊቃውንቷም እሳት
ላንዱ ጭስ ሲደርሰው
ለሌላው ትኩሳት።
ምሰሶው ቢተልቅ -
መሪው ገዝፎ ቢታይ
ጎጆው ከቶ አይሞቅም -
ካልጫሩበት እሳት
ጎጆው ቤት አይሆንም -
ሳር ከሌለው በአናት...
... ሀገርስ ጎጆ ናት!!! ...
═══════
📓 ልብ ሲበርደው
🗓 መጋቢት 2007 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Write_Event
┈•✦•┈
✍ እንዳለጌታ ከበደ
'
ሀገርስ ጎጆ ናት!!!
መሪዋም ምሰሶ
ሹማምንቷም ማገር
አንዳንዶቹም ቋሚ
ሌሎቹም ወጋግራ
ሠራዊቷም አጥር!
ሀገርስ ጎጆ ናት!!!
ሕዝቡም ክዳን ሆኖ
ጎጆውን አልብሶ
እንደሳር ቢቀጥን፤
ቢኖር ተራ መስሎ
ከዝናብ ያድናል፤
ውርጩን አሰናብቶ
ፀሐይን ይከላል፤
በጥላው ከልሎ ...
ሀገርስ ጎጆ ናት!!!
እውነትም ጎጆ ናት
ሊቃውንቷም እሳት
ላንዱ ጭስ ሲደርሰው
ለሌላው ትኩሳት።
ምሰሶው ቢተልቅ -
መሪው ገዝፎ ቢታይ
ጎጆው ከቶ አይሞቅም -
ካልጫሩበት እሳት
ጎጆው ቤት አይሆንም -
ሳር ከሌለው በአናት...
... ሀገርስ ጎጆ ናት!!! ...
═══════
📓 ልብ ሲበርደው
🗓 መጋቢት 2007 ዓ.ም.
📖 📖 📖 📖 📖
https://t.me/Write_Event
Telegram
እኛ እና የኛ
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።
ግጥም ለመላክ
➫ @Melikitegna_bot
💬
❝ቀስትህን እስከመጨረሻው ካልሳብከው ዒላማው ውስጥ እስከመጨረሻው አይገባም፤ ዕውቀትን የሚሻም ተማሪ እስከመጨረሻው የሚተጋ ብቻ ነው።❞
ሜንሲየስ
💬
❝ከመጻሕፍት አንዳንዶች የሚቀመሱ፤ አንዳንዶች የሚዋጡ፤ ሌሎች ደግሞ የሚመነዠኩም ናቸው።❞
ፍራንሲስ ቤከን
💬
❝በመመገቢያ ጠረጴዛህ ላይ መጽሐፎች ይሙሉ። ከዚያም በጣም ደስተኛ ትሆናለህ። ትራስህም መጽሐፎች ይሁኑ፤ ከዚያም ፍፁም የሠላም እንቅልፍ ትተኛለህ።❞
ፊዮዶር ዶስቶዬቭስኪ
💬
❝ዛፎች መሬት ለሰማይ የጻፈቻቸው ግጥሞች ናቸው።❞
ካህሊል ጂብራን
💬
❝ንፁህ አእምሮ ማለት ሙሉ ንቃት ማለት ነው። ለዚህም ነው ንፁህ አእምሮ፣ የሚወደውን ነገር በንቃት መመልከት የሚችለው።❞
ብሌዝ ፓስካል
💬
❝አንድን ሰው ምንም ልታስተምሩት አትችሉም፤ ማድረግ የምትችሉት ነገር ቢኖር ከራሱ ውስጥ እንዲፈልገው መርዳት ነው።❞
ጋሊሊዮ
💬 💬
ጥቅሶች
@write_event
❝ቀስትህን እስከመጨረሻው ካልሳብከው ዒላማው ውስጥ እስከመጨረሻው አይገባም፤ ዕውቀትን የሚሻም ተማሪ እስከመጨረሻው የሚተጋ ብቻ ነው።❞
ሜንሲየስ
💬
❝ከመጻሕፍት አንዳንዶች የሚቀመሱ፤ አንዳንዶች የሚዋጡ፤ ሌሎች ደግሞ የሚመነዠኩም ናቸው።❞
ፍራንሲስ ቤከን
💬
❝በመመገቢያ ጠረጴዛህ ላይ መጽሐፎች ይሙሉ። ከዚያም በጣም ደስተኛ ትሆናለህ። ትራስህም መጽሐፎች ይሁኑ፤ ከዚያም ፍፁም የሠላም እንቅልፍ ትተኛለህ።❞
ፊዮዶር ዶስቶዬቭስኪ
💬
❝ዛፎች መሬት ለሰማይ የጻፈቻቸው ግጥሞች ናቸው።❞
ካህሊል ጂብራን
💬
❝ንፁህ አእምሮ ማለት ሙሉ ንቃት ማለት ነው። ለዚህም ነው ንፁህ አእምሮ፣ የሚወደውን ነገር በንቃት መመልከት የሚችለው።❞
ብሌዝ ፓስካል
💬
❝አንድን ሰው ምንም ልታስተምሩት አትችሉም፤ ማድረግ የምትችሉት ነገር ቢኖር ከራሱ ውስጥ እንዲፈልገው መርዳት ነው።❞
ጋሊሊዮ
💬 💬
ጥቅሶች
@write_event