ቃላዊ
346 subscribers
38 photos
5 videos
1 file
121 links
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።

ግጥም ለመላክ
@Melikitegna_bot
Download Telegram
የሰው ልጅ የልምምድ ውጤት ነው። በልምምድ እንጅ በመወለድ ብቻ ሰው መሆን አይችልም። ከማፍቀር እስከ መቆርቆር ይለማመዳል። ማፍቀርን ያህል ያህል ነገር እንኳ አውቆ አይወለድም። እርሱን ብቻ አይደለም፤ መጥላትን ሳይቀር ይለማመዳል። ከማወቅ እስከ መናቅ፣ ከመወለድ እስከ መታነቅ፤ ከመድቀቅ እስከማድቀቅ፤ ከመጋባት እስከ መፍታት፤ ከስንፈት እስከ ጥረት ... ከመርመጥመጥ እስከ መፈርጠጥ፣ ከቆመጥ እስከ ነፍጥ...ተለማምዶት እንጅ ተሰጥቶት አይደለም። ከክህደት እስከ እምነት ካልተለማመደ አይችልም።

ከራሱ ያገኘው ማንነት የለውም። ሁሉም በሂደት እና በልምምድ የመጣ ነው። መልኩን ቆላ ሲወርድና ደጋ ሲወጣ ይቀያየራል። ልቡን በየግድሙ ይጥላል። ቀልቡን መቋጠሪያ የለውም። በመለማመድ አሁን የደረሰበትን እንጅ ወደፊት የሚሄድበትን ማንም ሊያውቅ አይችልም።

ክቡር ድንጋይ
ይስማዕክ ወርቁ

@write_event
@write_event
@write_event
ሱ!
(በእውቀቱ ስዩም)

እንደሰንበሌጥ ቤት ምድሪቱን አፍርሶ
ማድጋ ይመስል ጀምበርን ከስክሶ
እስኪያሰናብተን ጉዳችን ሳይፈላ
እንፍጠን ለተድላ
ልብ ያለህ ልብስ በል
ሆድ ያለህ ሆድ ሙላ

የወይራው የጥዱ ችግኙ ይነቀል
በመስኩ በሽጡ ጭገር ብቻ ይብቀል
መቀነትሽን ፍቺ ሸምቀቆህን ፍታ
ግባባት ጠብድለህ ታስገባህ ተከፍታ
አጥምቃት ተጠመቅ
ዓይንህን ጨፍነህ
ዕውር እድል አምነህ
ግባ ተመቀመቅ

ብትን ክስክስ ስትል
ሕይወት ከ'ጅ አምልጣ ልክ እንደ ብርሌ
እጣቸው አንድ ነው ድንግልና ሸሌ
ዋጋቸው መላ ነው ጭምትና አለሌ

ስብከት ደና ሰንብት ወግድ አትሮኖሱ
ጭላንጭል የለውም ቀፎ ነው ፋኖሱ
መስጠማችን ላይቀር በየውቅያኖሱ
ተነሱ ደንሱ

ሱ!!
#bewketusiyoum

@write_event
@write_event
@write_event
መፍትሄ
(በረከት በላይነህ)

በር መስኮት ዘግተህ ፣
ቀዳዳውን ደፍነህ
የለኮስከው ሻማ "በራ"! ፣"ጠፋ"! ካለ፤

ጠርጥር!
ቤት ያፈራው ንፋስ ከጎጆው እንዳለ።
#bereketbelayineh
@write_event
@write_event
@write_event
መአዛሽ ፈወሰኝ
(በእውቀቱ ስዩም)

ጎራዳ አፍንጫየን
ጎራዳ አፍንጫየን
ከሰገባው ሰቤ
ስምግሽ ቀርቤ
አንገትሽ ሽነት ዛፍ
ጡትሽ ደብረ-ከርቤ

እፎይ!!!

እንዲያው ሲፈርድብኝ ቤቴ አዲስ አበባ
ሰማዩ ጥንብ ነው መሬቱም አዛባ
አይን ጆሮ ምላስ ለኑሮ ሳያንሰኝ
ምን በድየውጌታ አፍንጫ ለገሰኝ
እያልኩኝ ሳማርር አንቺን ልኮ ካሰኝ
መድሃኒት ሆነና መአዛሽ ፈወሰኝ።
#bewketusiyoum

@write_event
@write_event
@write_event
በቃ ጨርሰናል!!
(አሌክስ አብርሃም)

አንዱ ከመሸ ወደሱቅ ይሄዳል ሱቁ ዝግ ነው ! ባለሱቁም ዘጋግቶ የሰላም እንቅልፉን ይለጥጣል! የመጣው ሰው ግን የፈለገው ነገር አስቸኳይ ስለነበር የተዘጋውን ሱቅ ማንኳኳት ጀመረ ጓ ጓ ጓ !

ማነው?
ደነበኛ ነኝ
ተኝቻለሁኮ
አውቃለሁ እባክህ አስቸኳይ ሁኖብኝ ነው
እሽ ምን ፈለክ ?
አምፖል አምፖል ፈለጌ ነው ባክህ

አምፖል ? አምፖል ግማሹ ተሽጦ ግማሹ ተሰብሮ አንዲት ባለ 25 ሻማ አምፖል ብቻ ናት የቀረችኝ
ይሁን ግዴለም ስንት ነው?
አምስት ብር ከከፈልክ ተነስቸ ልስጥህ?

<<አምስት ብርማ ውድ ነው የሰፈርህ ሰው ስላልሆንኩ ነው? >>
<<በቃ አራት ብር ውሰድ ልተኛበት>>
<<አራት ብር? ብዙኮ ነው ገና ለገና ሃይማኖታችን ይለያያል ብለህ ነው አይደል? ፈጣሪ ይወደዋል?>>
<<ሰውየ ፊታችን እንኳን ሳይተያይ የምን ስም መለጣጠፍ ነው ? ሶስት ብር ክፈልና ይዘህ ወደዛ ሂድልኝ በቃ ሰው መተኛ ያጣል እንዴ >>
<< ተው እንጅ ገና ለገና ካንተ ብሔር ስላልሆንኩ ዋጋ አትቆልልብኝ የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ብቻ መከበር የለበትም ? >>

ባለሱቁ ብስጭት ብስጭትጭት ብሎ ከመኝታው ዘሎ ተነሳ ! ወደመደርደሪያው ሂዶ አምፖሉን አውርዶ መሬት ላይ ከሽ አደረገውና ምን አለ ? <<በቃ ጨርሰናል!!>>
፨፨፨፨፨፨፨
@write_event
@write_event
@write_event
#BREAKING

የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ይህ የተገለጸው በደቡብ አፍሪካ ሲያደረግ የነበረው የሰላም ንግግር ውጤት በተገለጸበት ወቅት ነው።

የፌደራል መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ንግግር ይዘት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ እየገለጹ ነው።

@tikahethiopia
የትግራይ ምስኪን እናቶች እና ንፁሃን ይህ ዘለቄታዊ ስምምነት ከምንም በላይ ያስደስታቸዋል። ማንም እናት የልጇን ሞት አትሻም።

የኢትዮጵያ እናቶች ፀሎት በዋዛ አልቀረም ለህወሓት ልቦና ሰቷቸው ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን።


እኛም እንደ መንግሥታችን ኮለኔል መንግሥቱ
ኢትዮጵያ ትቅደም
እንላለን።

#Rise_up_Ethiopia
#Rise_up_Africa
#we_are_black
#KE_HASAB_ALEM

@write_event
@write_event
@write_event
#ሠላም_ለኢትዮጵያ
#ፍቅር_ለኢትዮጵያ
#አንድነት_ለኢትዮጵያ

እናትዬ እንዴት አደርሽ?
አደዬ ከመይ ሓዲርኪ?


እናትዬ እንዴት ዋልሽ?
አደዬ ከመይ ውዒልኪ?


እንዴት ዋልሽ እህቴ?
ከመይ ውዒልኪ ሓፍት?

እንዴት ዋልክ ወንድሜ?
ከመይ ውዒልካ ሓው?

እንዴት ዋላችሁ?

ከመይ ውዒልኩም?


#KE_HASAB_ALEM

@write_event
@write_event
@write_event
ያንተ ሲሳይ..!

        በአንድ ካንፓኒ ውስጥ ተቀጥሮ  በሚያገኘው ገቢ እናቱን ሚስቱን እና ልጆቹን ያስተዳድራል ዘውትር ስራውን በአግባብ እና በእምነት ለአለቃው ይሰራል እናም አንድ ቀን ስራ ሳይገባ ቀረ። የካንፓኒው ባለቤትም፦"በርግጠኝነት ክፍያ አንሶት ነው የቀረው ስለዚህ ነገ ሲመጣ ክፍያ እጨምርለታለሁ።" ብሎ ይወስናል።

በነጋታው ይህ ሰው ስራ ቦታ ከመግባቱ ክፍያውን ከነ ጭማሪው ሰጠው። ሰውየው ግን ስለጭማሪው ምንም አልደነቀውም ለምን ክፍያ እንደተጨመረለትም አለቃውን አልጠየቀም። ዝም ብሎ ስራውን ቀጠለ። ለተወሰኑ ቀናት እንደበፊቱ ስራውን በአግባብ ሰራ'ና አሁንም አንድ ቀን ስራ ሳይገባ ቀረ። አለቃው በጣም ተቆጣ የጨመረለትንም ደሞዝ መልሶ ቀነሰበት።

ስራውን ጨርሶ ክፍያ ሲቀበለው የጨመረለትን እንደቀነሰ አወቀ አሁንም ምንም ሳይል ትቶ ወጣ። በሰራተኛው ሁኔታ የተገረመው አለቃው፦"ባለፈው ክፍያ ስጨምርልህ ምንም አላልክም ዛሬም ስቀንስብህ ምንም አይነት ጥያቄ አላቀረብክም ለምንድነው?" ብሎ ጠየቀው።

እሱም፦"የመጀመሪያ ግዜ ስራ የቀረሁት የዛን ቀን ሚስቴ ወልዳ ነው ያን ቀን ደሞዝ ስትጨምርልኝ ስለጭማሪው ያልጠየቅኩህ የደሞዙ ጭማሪ ያ አዲስ ለተወለደው ህፃን አላህ የመደበለት ሪዝቅ እንደሆነ ስላወቅኩ ነው። ትናንት ስራ የቀረሁት እናቴ ሞታ ነው። አሁን ደሞ ደሞዝ ስትቀንስብኝ ዝም ያልኩት ያ ከዚህ በፊት ትበላው የነበረው የእናቴ ሪዝቅ በሷ መሞት ምክንያት አላህ አቋርጦት እንደሆነ ስላወቅኩ ነው።"ብሎ መለሰለት።

@write_event
@write_event
@write_event
ለፈገግታ..!

አንዱ ነው አሉ ሚስቱ አልታዘዝም ብላ አስቸገረችው። ከዛ ገርፎ ሊያስተካክላት አስቦ ጩኀቷ ከቤት ውጪ እንዳይሰማ ብሎ የቤቱን በር ቆለፈባት አሉ።

ከዛ ሊመታት እጁን ሲሰነዝርባት እጁን ያዝ አድርጋ አንስታ ጣለችው። ከዛ ከላይ ቁጭ ብላበት ቀጠቀጠችው ሰውዬው " ተጋደልን" እያለ መጮህ ጀመረ። በጣም ስትበረታበት "ገደለችኝ" ብሎ መጮህ ጀመረ።

ከዛ ሰዎች ሊገላግሉ መጡ በሩን እንደምንም ሰብረው ልክ ሲገቡ፣ ሚስትየው ፈጠን ብላ ገልበጥ አድርጋ ባሏን ከላዩዋ ላይ አስቀምጣ ከስሩ ገባች። ከዛ እሱም እሷን መምታት ጀመረ።

የገቡት ሰዎች አረ ገደልካት ብለው ሊዙት ሲሉ "ተውኝ አዲስ ተገልባጭ ነኝ " አለቸው ይባላል ።

ለፈገግታ..!

አንዱ ነው አሉ ሚስቱ አልታዘዝም ብላ አስቸገረችው። ከዛ ገርፎ ሊያስተካክላት አስቦ ጩኀቷ ከቤት ውጪ እንዳይሰማ ብሎ የቤቱን በር ቆለፈባት አሉ።

ከዛ ሊመታት እጁን ሲሰነዝርባት እጁን ያዝ አድርጋ አንስታ ጣለችው። ከዛ ከላይ ቁጭ ብላበት ቀጠቀጠችው ሰውዬው " ተጋደልን" እያለ መጮህ ጀመረ። በጣም ስትበረታበት "ገደለችኝ" ብሎ መጮህ ጀመረ።

ከዛ ሰዎች ሊገላግሉ መጡ በሩን እንደምንም ሰብረው ልክ ሲገቡ፣ ሚስትየው ፈጠን ብላ ገልበጥ አድርጋ ባሏን ከላዩዋ ላይ አስቀምጣ ከስሩ ገባች። ከዛ እሱም እሷን መምታት ጀመረ።

የገቡት ሰዎች አረ ገደልካት ብለው ሊዙት ሲሉ "ተውኝ አዲስ ተገልባጭ ነኝ " አለቸው ይባላል ።

Fouad Oumer |
@write_event
@write_event
@write_event
ሰሞንኛ
(በእውቀቱ ስዩም)

የሆነ ጊዜ ላይ የተወሰኑ ጓደኞቼን የምወዳት ልጅ ወላጆች ቤት ሽምግልና ላክሁዋቸው::
የፍቅረኛየ አባት “ልጁ ምናለው?” ብለው ጠየቁ ::
ከሽማግሌዎች አንዱ ትንሽ ሲያቅማማ ከቆየ በሁዋላ፥

“ ከሁለት መቶ ሺህ ያላነሰ ተከታይ አለው፤ ፌስቡክ ላይ “ ብሎ ተከዘ::
ቁሞ የመቅረት ታሪኬም በዛች ቀን ጀመረ፤

በቀደም ለታ፥ ፌስቡክ ፥ ከሁለት መቶ ሺህ በላይ ተከታዮቼ መካከል፥ ዘጠኝ ሺውን ብቻ አስቀርቶል ሌላውን አፈሰብኝ፤ የገንዘቡ ሳያንስ የተከታይ ግሽበት መታገስ የምችልበት ጫንቃ አልነበረኝም::

ከተከታዮቼ መሀል ፥ ጽፌ የምለጥፈውን አንብበው መውደዳቸውን የሚያሳዩኝ አስተያየቱን የሚለግሱኝ ከአስር ሺህ አይበልጡም፤ ከተከታዮቼ መሀል” ክንዴ ቢዝል፥ ምላሴን ቢያዳልጠው፥ ግጥሜ ልቦና ባይረታ፥ ቀልዴ ጥርስ ባይመታ፥ ልክ ልኬን ሊነግሩኝ መከትከቻውን እየሳሉ እሚጠብቁኝ እንዳሉ አውቃለሁ፤ዝም ብለው ደጃፍ ላይ ተቀምጠው ሳልፍ ሳገድም እሚያዩኝም ሞልተዋል::

ቢሆንም “
“ባይነዳ ባይረዳ ባይኖረውም ሀብት “
ከደጃፍ ሲቀመጥ ደስ ይላል አባት “ ይላል እማ ሸንበቆ ጠላ ቤት ግድግዳ ላይ የተለጠፈ ጥቅስ!
እኔም እለላሁ፤
“ባይለይክ፤ ባይኮምንት ፤ አሻራው ባይታይ”
ከደጃፍ ሲቀመጥ ደስ ይላል ተከታይ”

የፌስቡክ አለቃ ፥ በሁሉን አወቅነቱ፥ ይህንን ስሜቴን ተረድቶ ፥ በነበሩት ተከታዮቼ ላይ አንድ የቀበሌ አዳራሽ የሚሞሉ ተከታዮች ከራሱ ጨምሮ መለሰልኝ::

በባለፈው ዝግጅት ላይ ለታደሙ ወዳጆቼ የምስጋና ቃል ልጽፍ ሰንዳ ሰንዳ ስል መብራት እልም አለ:: እኛ ሰፈር ያለው ትራንስፎርመር በሚፈነዳበት መጠን የልደት ፊኛ አይፈነዳም ፤ አሁን አሁንማ፥ መብራት ሲጠፋ እንደ ድሮው መናደድ አቁሚያለሁ፤ በጨለማ ውስጥም ቢሆን ስራ እንዳልፈታ ምቾት እንዳላጣ አድርጌ ራሴን አላማምደዋለሁ፤ ሆመር ፥ ሀሰን አማኑ፥ እማሆይ ገላነሽ፥ ወዘተ፤ ውበት ፥ ሀሳብ እና ለዛ ለማፍለቅ የግድ ውጫዊ ብርሀን አስፈላጊ እንዳልሆነ ምስክር ናቸው፤ እንዲህ እያልሁ ዘና ብየ ጥቂት እንደቆየሁ አምፖሉ እንደ ነሀሴ ሰማይ ብልጭ ብሎ ድርግም ይላል፤ ጉዋደኛየ ምኡዝ አንድ የሚወዳት ልጅ ነበረች፤ የሆነ ቀን ሲጽፍላት አትመልስም፤ ሲደውልላት አታነሳም፤ ጭራሽ ለተወሰኑ ወራት መገኛዋን ሁሉ ትደመስሳለች፤ እሱም ያለ እሷ ለመኖር ራሱን ለማለማመድ ይፍጨረጨራል፤ ከዛ እፎይ ብሎ እየኖረ እያለ You miss me? 😘🥰😊 '' የሚል ቴክስት ትልክለታለች፤ አምፖሌ ብልጭ ብሎ የተለማመድሁትን የጨለማ ደስታ ሲያደፈርስብኝ ትዝ የሚለኝ ይሄ ነው፤

ጥለት ሚድያ ባሰናዳው የሰኞ ዝግጅት ላይ የታደማችሁ ምስጋናየን ይድረሳችሁ፤ ገና ሁለተኛ ዝግጅታችን እንደመሆኑ መጠን ጉድለታችንን ለማሻሻል አጥብቀን እንሰራለን፤ ሐረር ባንድ ጀንበር አልተገነባችም፤ (በጊዜው በጉልህ የታየው የድምጽ ችግር ከመብራት መጥፋት ጋራ በተያያዘ በጄኔረተር ምክንያት የመጣ ነው፤ ለዚህ ይቅርታ እንጠይቃለን) ሌላ እንዲስተካከል እምትፈልጉትን ሳታስባንኑ ፥ በአካል አግኝታችሁ፥ ምሳ እየጋበዛችሁ፤ ትከሻየን እየቸበቸባችሁ ንገሩኝ፤ በማቱሳላ አቆጣጠር ገና ልጅ ነኝ፤ እታረማለሁ::

የዝግጅቱ ቀን ከጉዋደኛየ ጋራ ስደርስ ጥቂት አርፍጄ ነበር፤ ከብሄራዊ ትያትር ወዲህ ማዶ፥ ኢትዮጵያ ሆቴልን አለፍ ብሎ ሰው በረጅሙ ተሰልፎ ሳይ ራሴን መቆጣጠር ተሳነኝ፤ ልቤ ተነካ፤” ወንድ ልጅ ብቻውን ነው እሚያለቅሰው “ ይላል ባለቅኔ ጸጋየ ገብረመድህን:: እኔ ግን ወንድ ልጅ በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ባያላቅስ ደስ ይለኛል፤ የዛን ቀን ግን አልቻልኩም፤ የደስታ እምባየ “ናፕኪን” ከደረት ኪሴ እስካወጣ እንኳን አልታገሰኝም

“ አሁን እኔ ይሄን የሚያህል ሰልፍ deserve አደርጋለሁ?”
አልሁት ጓደኛየን፥

“ ተረጋጋ! እነዚህ ወደ ሜክስኮ የሚሄደውን ምኒባስ ለመሳፈር የተሰለፉ ናቸው “

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!

https://t.me/write_event
ነጠብጣብ ሐሳቦች
በ. ሥ)
ሰማይ ከሚመክን ፤ይጸንስ መከራ
ያርግፍ ! ያርግፍ! ያርግፍ ! መኣት እያፈራ
የ’ሣት ዛፍ ባለበት ፤ ሰደድ አያስፈራ
.............
ከሐምሌት ጋር ሞቷል፤ የማመንታት ዓለም
ከሆኑ በኋላ፤ አለመሆን የለም
ሸክም ጸጋ ሆኗል፤ ጸጋህን አትግፋ
በጠባብ ዓለም ውስጥ፤ ትከሻህን አስፋ!
............
አንድ ሕልም እንደ ጠጅ፤ እየደጋገሙ
ንግር ፤ትንቢት ሳይሆን፤ ታሪክ እያልለሙ
ተኝቶ መነሣት
አቤት ሲያቅለሸልሽ
ጌታ ሆይ አትንሣት
ነፍሴን እንቆቅልሽ
(ከስብስብ ግጥሞች)
share and join
@write_event
@write_event
@write_event
ዝግ ዓለም
(በ.ሥ)
ከትራሴ ግድም ፤በተደፋው ሰማይ
ኮከብ እያበራ ፤በመከዳየ ላይ
ምንም አላነበብኩ ፤ከህዋው ግድግዳ
እውነትና ንጋት፤ እያደር እንግዳ፡፡
(ከስብስብ ግጥሞች)
share and join
@write_event
@write_event
@write_event
እረፉ!
“ዘመመ!” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ
እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ።
እረፍ!
“ቆሜያለሁ!” ለማለት አጥሬን አትደገፍ
ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ።
እረፍ!
በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም
በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም።
እረፊ!
በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ
በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ።.
...ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ
ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ።
#Eyayu Fenges


share and join
@write_event
@write_event
@write_event
"""""""" ናፍቆት """""""""
እንደምነሽ እቴ ?
እኔ እንዳለሁ አለሁ ሳላሰማ ኮቴ
ይኸው ነጥቀውኛል ስሜን ከነ እርስቴ
እንደምነሽ አንች ?
እኔማ ዴግ ነኝ ተስፋ አይሞትም ስባል
ተስፋ እየጠበኩኝ በጨለማ መሃል
አዎ እኔ ደህና ነኝ ¡
ያው እንደምታይኝ ቁመቴ ጨምሯል
በእድሜየ ግማሽ ላይ ዘመን ይታከላል
ይኸውልሽ ዘንድሮ _
ያ የምንጠጣበት ኩሬያችን ደፍርሶ
የምናወጋበት ግራራችን ታርሶ

በእንተማርያም የሚል የዋህ ዲያቆን ጠፍቶ
ሸሚዜን ሰረቀኝ ቀየረው ጠረኔን በማይሆን ቡትቶ
ጦሴን ይዞት ይሂድ

ግን አንች እንደምነሽ ? ሞት እንዲህ ያኮራል?
ገነት እንደምናት? የጻድቃን መኖሪያ ሰምቻለሁ ሲባል
እዚህ እንደሚወራው ሲኦል ከምር አለ?
እዚህማ ሞልቷል ምን የቀረን አለ
ኪራይ ቤት ሲኦል ነው
ሽንትቤት ሲኦል ነው
ስራውም ሲኦል ነው
ምድርም እኮ እራሷ ሲኦል መሆኗ ነው

አንች እንደምን አለሽ ?
ከሰማያት በላይ ከደመና እርቀሽ
በመላእክት መዝሙር ነው አሉ ሚያስተኙሽ
እዛስ ሙዚቃ አለ ?
እዚህ ዘፈን በዝቷል ሁሉም ሙዚቀኛ
ተሸላሚ ሞልቷል ከነክብሩ አንደኛ
በዝቶልሻል ቅኔ
ይናገረው ይዟል ሰው ሁሉ በወኔ
____አየ ቅኔ
_አወይ እኔ
መንግስትም አለ እኮ ምንግዜም የማይወርድ
ለ ግብጽ ወታደር የማይርበደበድ
ድርቅ የማይነካካው ረሃብ የማያውቅ
እድገት አስመዝግቧል ታይቶ ማይታወቅ
እረ ምን ነክቶሻል ምን የሌለን አለ
ኔት ወርክ በሽ ነው ሁሉ እየታደለ
አለሜ
እኔ ግን መሮኛል ምጻት አልጠብቅም
___ምጻት ይምጣ አልልም
እኔ እቀድመዋለሁ በናፍቆትሽ በትር ቁሜ አልገረፍም
ያሬድ ከበደ
( ያሬዳዊ ግጥም)
*
እምነት ሲበረታ


እንደው ለተአምር
የመርፌ ቀዳዳ ግመል ካሻገረ
"""""" """""""
ድር ያበረ ለታ
ከሠንሠለት ከሮ አምበሳን ካሰረ
""""""" """"""""
ከሚባለው እጥፍ
እጥፍ ከሚባለው ሆድ ካገር ከሰፋ
““"""" “““"""
በልቡ ያመነ
ከጥፋቱ ድኖ ተራራን ከገፋ
““““ “"""""
ቀስትና ፍላፃው
ክንዱ ሲበረታ የእምነታችን ደጋን
"""""" """""""
ድጋፉ ሳይዋልል
በጠጠር መዳፍ ላይ ከተቀመጠ ጋን
"""""" """""""""
በባለፀጋ ህልም
በመርፌ ቀዳዳ ከመሻገር ጥማት
""""""" """"""""
በፅድቅ መነፅር
ከግመል ቁመና ይወፍራል ጅማት

share and join
@write_event
@write_event
@write_event
፨፨፨፨የይቅርታ መሐልይ፨፨፨
ማነዉ የፈለገኝ?
በማይነጋ ሌሊት
በማይመሽ ቀን መሀል
ተዘርሬ ስገኝ።
ከተዉሽኝ በኀላ 'ርቃን ቀርታ ነፍሴ
እንኳን ከሰው ዐዉድ ተነጠልኩ ከራሴ፡፡
፨ ፨ ፨
ተመልሼ ልምጣ ተመልሰሽ ነዪ
ልጣል ምሰሶዬን ማገርሽን ጣዪ
አዲስ ቤት መገንባት ዛሬ መች ይደላል
ለምደዉ ወደተዉት መመለስ ይቀላል፡፡
፨ ፨ ፨
ካሳ ባልክልሽ ቁና ጤፍ ሰፍሬ
ባዶ እጄን አልቆምም ከደጅሽ ደፍሬ
ጵንፍ የለሽ ይቅርታን ውሰጅ ከከንፈሬ፡፡
★★★በእውቀቱ ስዩም★★★
https://t.me/write_event
---ድምጽ አልባ ፊደላት---
ፀጉሩን አንጨብሮ ፂሙን አጎፍሮ
ጥግ ተቀምጦ ለሚታየኝ ወጣት
ሂድና ታዘዘው ስጠው አንድ ድራፍት
ቅዳለት ደብል ጂን ሃሳቡን ይርሳበት
በፂሙ መጎፈር በፀጉሩ መንጨብረር
ቁጥር ፈታ በሚል በግንባሩ መስመር
ይታየኛል ቋንቃ ይታየኛል ነገር
እዛም ከጨለማው ብቸኝነት ውጧት
ሲጋራዋን ይዛ ለቆመችው ወጣት
ሂድና ታዘዛት የሚጠጣ ስጣት
ምጋ በተፋችው በጭሶቹ መሃል
ሴትነት ሲበደል እህትነት ሲጣል
እናትነት ሲጎድል
ይታየኛል ቋንቃ ይታየኛል ፊደል።
👉👉ኤፍሬም ስዩም👈👈

https://t.me/write_event