ቃላዊ
346 subscribers
38 photos
5 videos
1 file
121 links
በዚህ ቻናል
◈ሰፊ ማህበራዊና ፍልስፍናዊ እይታዎች
◈ህይወትን የሚያድሱ የስነ-ልቦና ምክሮች
◈የአንጋፋ እና ጀማሪ ገጣሚያን ግጥሞች
◈ግሩም የፍቅር ታሪኮችና ወጎች
◈በፅሁፍ እና በድምፅ ይቀርባሉ
በኢትዮጵያውያን አና በውጭ ሀገር ደራስያን የተጻፉ አማርኛ መፅሃፍት በጥቂቱ የሚቀርቡበትና ውብ የጥበብ ስራዎች
በድምፅ ሚተረኩበት ግሩምና ድንቅ ቻናል ነው።

ግጥም ለመላክ
@Melikitegna_bot
Download Telegram
የዛሬ መቶ ዓመት ማንኛችንም አልነበርንም።ከመቶ ዓመት በኋላም አንዳችንም አንኖርም። ይህንን ከልባችን ማሰብና አስረግጠን መረዳት ብንችል ትንሽ መተዛዘን የተሻለ_መተሳሰብ ያለንን ተከፋፍለንና ተረዳድተን አብረን በሰላም መኖር ብንችል ምን እንሆናለን ??? ሀገር የጭንቅላታችንን እንጂ የቆዳ ስፋቷን ያህል አይደለችምና።

ዶክተር_ምህረት_ደበበ


@write_event
"የተዘጋ ሀሳብ"

( በኤፍሬም ሥዩም)


☞ እዚህ……
ሙዚቃ ከሌለው ስሜት ከማይሰጥ ቤት
ሀዘን ያልተለየው የከሰለን ህይወት
አዳፋ ለባሾች የቀን ሰራተኞች
ንቃቃታም ሴቶች ጉሊት ቸርቻሪዎች
አግዳሚ ወንበሩን ሚስኪኖች ከበውት
ማገር የሌለውን ጠባቡን ያፈር ቤት
በጠላ ባረቂ በጠጅ አጅበውት።
.
ከኑሯቸው በላይ ጫጫታቸው በዝቶ
ካዘናቸው ይልቅ ሳቃቸው ተሰምቶ
አንዱ ድሀ ዘፋኝ አንዱ አጨብጫቢ
አንድኛው ፎካሪ የጋባዥ አጃቢ
ባንድነት ተፋፍገው እየተማማሉ
ምግብ አልበላንም እየተባባሉ
ለድሃ እሚራራ ነፍስን ያደማሉ።
.
☞ እዚያ....
ጥቂት ሹማምንቶች የመተያያን ገንዘብ 'ሚጥሉበት
አጥተው
የግፍ ነጋዴዎች ንጋት ሳይቀድማቸው
ያልፈኩ አበቦች ከሚቆረጡበት
ለአይን የሚያሳሱ እንስቶች ካሉበት
ልክ በሌለው አፍ ዘፈኑ ተከፍቶ
የሚረግጠው ስፍራ እግራቸው ቦታ አጥቶ
በሬጌና በቫልስ፣ በቡጊ በቻቻ በሳንባና በራፕ፤
እንዲሁም በስክስታ ጭፈራቸው ደርቷል
የቀን ግፋቸውን ግድ የለሽ አይምሮን በውስኪ ያጥቡታል።
.
ከደጅ ከሀብታሞች ቡና ቤት፣ ድሆችም ባሉበት ካረቂ ቤቱ
በር
ከገንዳ ላይ ለቅሞ ሆዱን የሚሞላ አንድ ሚስኪን ነበር።
.
☞ እኔ .....
ሀብትን ከማይጠሉት ለድሆች ከሚያዝኑት መካከል ላይ
ቆሜ እሰቃይ ነበረ...
እውነት በሚሰፍር ቀን በሚታይ ህልሜ።
.
☞ ገንዳ ለቃሚው....
ኑሯቸው ነው ብለህ ስለነዚህ ድሆች ስለምን ታዝናለህ
እኒህ ትንሽ ድሆች ሀብት ቢሞላቻው ብር ቢተርፋቸው
ከባንኮኒ ቆመው ከመጠጣት ሌላ ምንድን ነው ትርፋቸው?
ምንድን ነው ተስፋቸው ገንዳው ላይ ለቆመው?
.
እኒህስ ሀብታሞች ከውስኪ ቤት አልፈው
ከመግባት ውስኪ ቤት
አንዷን ቆንጆ ትተው ከማቀፍ ሌላ ሴት
አይምሮአቸው ሂዶ ደርሶ የሚያርፍበት
አዲስ ኬላ የለም ሰርተው የሚፈጥሩት።
.
ስለዚህ ግጥምህን እንዲህ ብለህ ዝጋው
እንደዚህ አትማው
ሰካራም ድሃና መጠን አልባ ሀብታም
ፍፃሜው አንድ ነው
ከባንኮኒ ቆመው ከአግዳሚ ተነስተው ውስኪ ለማድረግ
ነው
አረቄውን ደፍተው።



(ከሶልያና የግጥም ሲዲ የተጻፈ)


@write_event
" # እጅ_ከፍንጅ "?
-
አንዲት ባለትዳር ፥ በጓዳዋ ሳለች ፥ ጉንዳን ቆነጠጣት
ከእግር እስከ ራሷ ፥ ተርመስምሶ ገብቶ ፥ ነክሶ ፋታ አሳጣት
-
ይሄን ጊዜ ጮኸች፤
ልብሶቿን አራግፋ ፥ ራቁቷን ቀረች!
-
ጩኸቷን የሰማ ፥ ላጤ ጎረቤቷ ፥ ገባ ተንደርድሮ
ያቺን ቆንጆ እንስት ፥ እርቃኗን ሲያያት ፥ ቀረ ተገትሮ!
-
በዚህ ሁነት መሃል ፥ ሰይጣን አይኑን ሲጥል ፥ ባል ድንገት
ይደርሳል
ሰበብ የጠፋ 'ለት ፥ የጉንዳን ወረራ ፥ ትዳርን ያፈርሳል ።
---------//----------
( በርናባስ ከበደ )

https://t.me/write_event
( በወዳጃችን ጥያቄ የተደገመ....)

አንቺነት ሰይጣኑ ከኔነት ጋንኤል



አየሽ....
የሄደው ሲመጣ
የመጣም ይሄዳል

ከመንፈስሽ አስኳል
ካንቺነትሽ ጫፍ ላይ
የሚቀርሽ እውነት ብቻነት ይባላል፡፡

ትዝ ይልሻል ያኔ -!?

ከትዝታሽ ማኅደር
ስለተሰደረ ታጅሎ ኩነኔ
ማስታወስሽ አለ እልህ ቋጥሮ ካይኔ፡፡

እናም...
ትዝ ይልሻል- -፤

ሀይማኖት ልንማር
እምነት ልንሰበክ
ከቤተ - እምነታችን
በም’መናን ፅናት ካ’ውደ - ም’ረት ውለን
በሊቀ - ቀንዳችን እግዜር ሲነገረን - !?

ከቤተ - ዓምልኳችን
ቅፅር አለፍ ብሎ ድሪቶውን ለብሶ

እሱም ተደራርቶ
እንዳልባሌ ቁስ ነፍሱ ላይ ተኝቶ
ለሌላው አይን ሻግቶ

ያለፍነው ያ ነዳይ...!!
ብጤያችን ያልሆነ የኛ ብጤ ተባይ
የኛ ብጤ መሳይ...!!!

ምንድን ነበር ያልነው - !?

“....የለማኝ ሀገር ልጅ
የመለመን እጣው ደምቆ የተፃፈ

የማሳፈር ገድሉ
የማሰደብ ሀይሉ
እንደመልካም ታሪክ ጠሎ ያሰፈፈ፡፡

መለመን
መለመን …!!!
ሀገሪቱ ለማኝ

ዜጎቿ በሙላ
የለማኝ ልጅ ሁላ
ነዳይ በጠቅላላ፡፡

ከልመና ከርስ ውስጥ ነፍሳቸው ተጥላ

በቧጋች ማንነት
መፅዋች በመፈለግ ያለች ተንጠልጥላ
አሳሯን አጥልላ....፡፡”

አልነበረ ያልነው - !?

ሀገርን....ዜጎቿን
በማን አለብኝ ልጥ አስረን የዘለፍነው - !?

አየሽ …
ሐረግና ማማ
ሆኖ መተቃቀፍ ለሁሌው ይመስላል

እጣ ክፍልሽ ሲሆን
የያዙትን መልቀቅ ያነሱትን መጣል

“እኔነት” የሚባል
የሚያውቁት ዲያቢሎስ
ከማያውቁት መላ’ክ ላይሻል ይበቅላል፡፡

አየሽ …
ካድማሱ ገመገም ከተራራው አናት
ሰማዩን ልቀርበው ልደመም በውበት
የያዘኝን ፍቅር ልይዘው በግዞት

- - ቆሳስዬ ወጣሁ - -

ሰማይ ከተራራ ካድማስ እንደሚርቅ
የተራራው ጉጠት የሜዳው ሌላ መልክ

- - መሆኑን ተረዳሁ - -

አየሸ …
የቀን ሲቀርቡት ሌላ ርቀት አለ፡፡
ጥልቁንም ሲደርሱት ሌላ ጥልቀት አለ፡፡

የያዘኝ ፍቅርሽ ውስጥ ምስልሽ ተንፈላ’ሷል
የደለው ምስልሽ ውስጥ
ሊነኩት
ሊደርሱት ሊየውቁት የማይቻል
አንቺነት ተኝቷል፡፡

እኔነት አጋንንት እኔነት ጋንኤል
ካንቺነት ሰይጣኑ
ካንቺነት ደያቢሎስ
ፍቅር ይሉት አዘቅት ውስጥ ወድቆ ይዳክራል፡፡

ትዝ ይልሻል ያኔ - !?

ሃይማኖት ሲሰብኩን
ማመን ሲያስተምሩን.....

ገኖ የከበረ
የገዢዎች ሁሉ ገዢያቸው የሆነ
“ፍቅር እግዜሩ ነው” ብለውን ነበረ፡፡

ልሳን ብናወራ
ጥበብን መርምረን ጉባኤ ብንመራ

አውቀን ብንመነጥቅ
ከልባችን ሙዳይ ፍቅር ካልሆነን ስንቅ

ከንቱ ነው ብለዋል ከምኩራብ ላይ ቆመው
በኩራት ተጠምቀው፡፡

የሉት ይመስልሻል - !?
’ውነት ነው ብለሻል - !?

የተኛን መቀስቀስ
ፀላየ ሰናይን
ማገጠም ከሆነ ከፍተኛ ግብሩ

አንድነት መዘመር
በሚል ቃል ጠፍሮ
መለየት ከሆነ ዕፀ - መሰውሩ

“ፍቅር” ለሚለው ቃል
ሃይማኖት አብሏል
ማር የተለወሰ እሬት ሆኖ ቀርቧል፡፡

’ውነት ግን - !?
’ውነት ግን - !?

- - እንዲያ ነው እግዜሩ - - !?

እኔነት ካንቺነት ለህመም ሲጣመሩ
ለሞት ሲቃጠሩ -፤

መለየትነ ቋጥረው
ከጊዜው ሸሽገው አብሮነት ሲያወሩ

ኖረው የሚያልፉበት
ገድለው ’ሚኖሩበት

- - እንዲያ እኮ ነው ፍቅሩ - -!!!

እኔነት ካንቺነት
ስጋት ረግረግ ውስጥ ተውጠው እያሉ

ፀሀይን ለተስፋ
ጨረቃን ለማጌጥ ይዘናል እያሉ

የሚታበዩበት
የታይታ ህይወትን የሚያራምዱበት

- - እንዲያ እኮ ነው ፍቅሩ - -!!

አየሽ …
የሄደው ሲመጣ
የመጣም ይሄዳል

ከመንፈስሽ አስኳል
ካንቺነትሽ ጫፍ ላይ
የሚቀርሽ እውነት ብቻነት ይባላል፡፡

- - ጥለሽኝ ስለሄድሽ - -

ነፍሴን ጎርፍ ሞላት
የልቤ ክረምቱ
ፀደዬን ገደለ ደመና አረገዘ

በነዝናዛ ካፊያ
ዘላለም በሚመስል
አሰቃቂ ውድቀት መንፈሴ ተያዘ፡፡

- - ጥለሽኝ ስለሄድሽ - -

ስለኔ መኖሬ
ስለኔ ማደሬ
ስለኔ ማዝመሬ መሰለኝ ተረቴ
እንዲህ የምቀምሰው የእጦት ዳረጎቴ፡፡

“… እኔነት የሚባል ካንቺነት የዋለ
ካንቺነት ያደረ
ጋንኤል ነበረ … (!?)

ግና ካልነበረ...
ዳቦውን ሳትቆርሱ
አፍም ሳታብሱ
ተረት አትመልሱ …”

አየሽ …
ጥለሽኝ ስለሄድሽ ‘ነበር’ እንኳን ጣለኝ
እኔነቴ ብቻ ችንካሩ አሳዘነኝ።

የጭንቅ ስቅላቱ
ዳር...ወሰን አልባነት ለራሴው ሰቀቀኝ፡፡

አየሽ …
የማይታወቅን
ለማወቅ መታከት ህመም ያስታቅፋል፡፡

የማይደርሱበትን
ለመድረስ መታገል ስቀይን ይወልዳል፡፡

የታቀፉት ህመም
የወለዱት ስቃይ
የማይለቁት ሆኖ ከሰይጣን ይከፋል፡፡

የሰው ጫካ መሀል
እንደተላጠ ግንድ
የተለበለበ እርቃንን ያስኬዳል፡፡

የሚገርመው ደግሞ...
ለኔነት ጋንኤል
ላንቺነት ዲያቢሎስ የሚያከብረው ምሱ

ከምንም መሻቱ
አጥብቆ እሚመኘው ይኼ እኮ ነው ሱሱ፡፡

አየሽ …
ሀረግና ማማ
ሆኖ መተቃቀፍ ለሁሌው ይመስላል

እጣ ክፍልሽ ሲሆን
የያዙትን መልቀቅ ያነሱትን መጣል

“እኔነት” የሚባል
የሚያውቁት ዲያቢሎስ
ከማያውቁት መልአክ ላይሻል ይበቅላል፡፡



( ዮሐንስ ሀብተማሪያም (ጆ) )

@write_event
#እሷና ወንዝነት
(ትርጉም ፦ Khalil Gibran)
አለ ፍርሀት በወንዝ እውነት
በባህር ውስጥ መቅረት
እሷም እንደዚህ ናት
ስትወርድ ከላይ ከተራራው ቁልቁል
ከተማ 'ሚያካልል ...
አለ ውቅያኖስ ከመንደሩ ማዶ
የብስ አይሆን ነገር ወደኋላው ሄዶ
አትችልም መሻገር
ከማመን በስተቀር
ማመን ትልቅነት
አቅምን መገመት
ያድናል ከመስመጥ !
ሆኖም ለወንዝነት
በዚያ ፍሳሽ ዥረት
ፍርሀት ደንብ አይደለም
በዛው ሰምጦ መቅረት
ውረድ.. ፍሰስ.. .ክነፍ
ግባ ከሰፊው አምድ አትሰጋ ተንደርደር
ፍርሀት ሲሞት ነው ...
ባህር ነህ ተብሎ ላንተ የሚነገር!

(ሚካኤል.አ)

@write_event
@write_event
@write_event
የሰው ልጅ የልምምድ ውጤት ነው። በልምምድ እንጅ በመወለድ ብቻ ሰው መሆን አይችልም። ከማፍቀር እስከ መቆርቆር ይለማመዳል። ማፍቀርን ያህል ያህል ነገር እንኳ አውቆ አይወለድም። እርሱን ብቻ አይደለም፤ መጥላትን ሳይቀር ይለማመዳል። ከማወቅ እስከ መናቅ፣ ከመወለድ እስከ መታነቅ፤ ከመድቀቅ እስከማድቀቅ፤ ከመጋባት እስከ መፍታት፤ ከስንፈት እስከ ጥረት ... ከመርመጥመጥ እስከ መፈርጠጥ፣ ከቆመጥ እስከ ነፍጥ...ተለማምዶት እንጅ ተሰጥቶት አይደለም። ከክህደት እስከ እምነት ካልተለማመደ አይችልም።

ከራሱ ያገኘው ማንነት የለውም። ሁሉም በሂደት እና በልምምድ የመጣ ነው። መልኩን ቆላ ሲወርድና ደጋ ሲወጣ ይቀያየራል። ልቡን በየግድሙ ይጥላል። ቀልቡን መቋጠሪያ የለውም። በመለማመድ አሁን የደረሰበትን እንጅ ወደፊት የሚሄድበትን ማንም ሊያውቅ አይችልም።

ክቡር ድንጋይ
ይስማዕክ ወርቁ

@write_event
@write_event
@write_event
ሱ!
(በእውቀቱ ስዩም)

እንደሰንበሌጥ ቤት ምድሪቱን አፍርሶ
ማድጋ ይመስል ጀምበርን ከስክሶ
እስኪያሰናብተን ጉዳችን ሳይፈላ
እንፍጠን ለተድላ
ልብ ያለህ ልብስ በል
ሆድ ያለህ ሆድ ሙላ

የወይራው የጥዱ ችግኙ ይነቀል
በመስኩ በሽጡ ጭገር ብቻ ይብቀል
መቀነትሽን ፍቺ ሸምቀቆህን ፍታ
ግባባት ጠብድለህ ታስገባህ ተከፍታ
አጥምቃት ተጠመቅ
ዓይንህን ጨፍነህ
ዕውር እድል አምነህ
ግባ ተመቀመቅ

ብትን ክስክስ ስትል
ሕይወት ከ'ጅ አምልጣ ልክ እንደ ብርሌ
እጣቸው አንድ ነው ድንግልና ሸሌ
ዋጋቸው መላ ነው ጭምትና አለሌ

ስብከት ደና ሰንብት ወግድ አትሮኖሱ
ጭላንጭል የለውም ቀፎ ነው ፋኖሱ
መስጠማችን ላይቀር በየውቅያኖሱ
ተነሱ ደንሱ

ሱ!!
#bewketusiyoum

@write_event
@write_event
@write_event
መፍትሄ
(በረከት በላይነህ)

በር መስኮት ዘግተህ ፣
ቀዳዳውን ደፍነህ
የለኮስከው ሻማ "በራ"! ፣"ጠፋ"! ካለ፤

ጠርጥር!
ቤት ያፈራው ንፋስ ከጎጆው እንዳለ።
#bereketbelayineh
@write_event
@write_event
@write_event
መአዛሽ ፈወሰኝ
(በእውቀቱ ስዩም)

ጎራዳ አፍንጫየን
ጎራዳ አፍንጫየን
ከሰገባው ሰቤ
ስምግሽ ቀርቤ
አንገትሽ ሽነት ዛፍ
ጡትሽ ደብረ-ከርቤ

እፎይ!!!

እንዲያው ሲፈርድብኝ ቤቴ አዲስ አበባ
ሰማዩ ጥንብ ነው መሬቱም አዛባ
አይን ጆሮ ምላስ ለኑሮ ሳያንሰኝ
ምን በድየውጌታ አፍንጫ ለገሰኝ
እያልኩኝ ሳማርር አንቺን ልኮ ካሰኝ
መድሃኒት ሆነና መአዛሽ ፈወሰኝ።
#bewketusiyoum

@write_event
@write_event
@write_event
በቃ ጨርሰናል!!
(አሌክስ አብርሃም)

አንዱ ከመሸ ወደሱቅ ይሄዳል ሱቁ ዝግ ነው ! ባለሱቁም ዘጋግቶ የሰላም እንቅልፉን ይለጥጣል! የመጣው ሰው ግን የፈለገው ነገር አስቸኳይ ስለነበር የተዘጋውን ሱቅ ማንኳኳት ጀመረ ጓ ጓ ጓ !

ማነው?
ደነበኛ ነኝ
ተኝቻለሁኮ
አውቃለሁ እባክህ አስቸኳይ ሁኖብኝ ነው
እሽ ምን ፈለክ ?
አምፖል አምፖል ፈለጌ ነው ባክህ

አምፖል ? አምፖል ግማሹ ተሽጦ ግማሹ ተሰብሮ አንዲት ባለ 25 ሻማ አምፖል ብቻ ናት የቀረችኝ
ይሁን ግዴለም ስንት ነው?
አምስት ብር ከከፈልክ ተነስቸ ልስጥህ?

<<አምስት ብርማ ውድ ነው የሰፈርህ ሰው ስላልሆንኩ ነው? >>
<<በቃ አራት ብር ውሰድ ልተኛበት>>
<<አራት ብር? ብዙኮ ነው ገና ለገና ሃይማኖታችን ይለያያል ብለህ ነው አይደል? ፈጣሪ ይወደዋል?>>
<<ሰውየ ፊታችን እንኳን ሳይተያይ የምን ስም መለጣጠፍ ነው ? ሶስት ብር ክፈልና ይዘህ ወደዛ ሂድልኝ በቃ ሰው መተኛ ያጣል እንዴ >>
<< ተው እንጅ ገና ለገና ካንተ ብሔር ስላልሆንኩ ዋጋ አትቆልልብኝ የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ብቻ መከበር የለበትም ? >>

ባለሱቁ ብስጭት ብስጭትጭት ብሎ ከመኝታው ዘሎ ተነሳ ! ወደመደርደሪያው ሂዶ አምፖሉን አውርዶ መሬት ላይ ከሽ አደረገውና ምን አለ ? <<በቃ ጨርሰናል!!>>
፨፨፨፨፨፨፨
@write_event
@write_event
@write_event
#BREAKING

የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ዘላቂ ግጭት የማቆም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ይህ የተገለጸው በደቡብ አፍሪካ ሲያደረግ የነበረው የሰላም ንግግር ውጤት በተገለጸበት ወቅት ነው።

የፌደራል መንግሥት እና የህወሓት የሰላም ንግግር ይዘት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ እየገለጹ ነው።

@tikahethiopia
የትግራይ ምስኪን እናቶች እና ንፁሃን ይህ ዘለቄታዊ ስምምነት ከምንም በላይ ያስደስታቸዋል። ማንም እናት የልጇን ሞት አትሻም።

የኢትዮጵያ እናቶች ፀሎት በዋዛ አልቀረም ለህወሓት ልቦና ሰቷቸው ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን።


እኛም እንደ መንግሥታችን ኮለኔል መንግሥቱ
ኢትዮጵያ ትቅደም
እንላለን።

#Rise_up_Ethiopia
#Rise_up_Africa
#we_are_black
#KE_HASAB_ALEM

@write_event
@write_event
@write_event
#ሠላም_ለኢትዮጵያ
#ፍቅር_ለኢትዮጵያ
#አንድነት_ለኢትዮጵያ

እናትዬ እንዴት አደርሽ?
አደዬ ከመይ ሓዲርኪ?


እናትዬ እንዴት ዋልሽ?
አደዬ ከመይ ውዒልኪ?


እንዴት ዋልሽ እህቴ?
ከመይ ውዒልኪ ሓፍት?

እንዴት ዋልክ ወንድሜ?
ከመይ ውዒልካ ሓው?

እንዴት ዋላችሁ?

ከመይ ውዒልኩም?


#KE_HASAB_ALEM

@write_event
@write_event
@write_event
ያንተ ሲሳይ..!

        በአንድ ካንፓኒ ውስጥ ተቀጥሮ  በሚያገኘው ገቢ እናቱን ሚስቱን እና ልጆቹን ያስተዳድራል ዘውትር ስራውን በአግባብ እና በእምነት ለአለቃው ይሰራል እናም አንድ ቀን ስራ ሳይገባ ቀረ። የካንፓኒው ባለቤትም፦"በርግጠኝነት ክፍያ አንሶት ነው የቀረው ስለዚህ ነገ ሲመጣ ክፍያ እጨምርለታለሁ።" ብሎ ይወስናል።

በነጋታው ይህ ሰው ስራ ቦታ ከመግባቱ ክፍያውን ከነ ጭማሪው ሰጠው። ሰውየው ግን ስለጭማሪው ምንም አልደነቀውም ለምን ክፍያ እንደተጨመረለትም አለቃውን አልጠየቀም። ዝም ብሎ ስራውን ቀጠለ። ለተወሰኑ ቀናት እንደበፊቱ ስራውን በአግባብ ሰራ'ና አሁንም አንድ ቀን ስራ ሳይገባ ቀረ። አለቃው በጣም ተቆጣ የጨመረለትንም ደሞዝ መልሶ ቀነሰበት።

ስራውን ጨርሶ ክፍያ ሲቀበለው የጨመረለትን እንደቀነሰ አወቀ አሁንም ምንም ሳይል ትቶ ወጣ። በሰራተኛው ሁኔታ የተገረመው አለቃው፦"ባለፈው ክፍያ ስጨምርልህ ምንም አላልክም ዛሬም ስቀንስብህ ምንም አይነት ጥያቄ አላቀረብክም ለምንድነው?" ብሎ ጠየቀው።

እሱም፦"የመጀመሪያ ግዜ ስራ የቀረሁት የዛን ቀን ሚስቴ ወልዳ ነው ያን ቀን ደሞዝ ስትጨምርልኝ ስለጭማሪው ያልጠየቅኩህ የደሞዙ ጭማሪ ያ አዲስ ለተወለደው ህፃን አላህ የመደበለት ሪዝቅ እንደሆነ ስላወቅኩ ነው። ትናንት ስራ የቀረሁት እናቴ ሞታ ነው። አሁን ደሞ ደሞዝ ስትቀንስብኝ ዝም ያልኩት ያ ከዚህ በፊት ትበላው የነበረው የእናቴ ሪዝቅ በሷ መሞት ምክንያት አላህ አቋርጦት እንደሆነ ስላወቅኩ ነው።"ብሎ መለሰለት።

@write_event
@write_event
@write_event
ለፈገግታ..!

አንዱ ነው አሉ ሚስቱ አልታዘዝም ብላ አስቸገረችው። ከዛ ገርፎ ሊያስተካክላት አስቦ ጩኀቷ ከቤት ውጪ እንዳይሰማ ብሎ የቤቱን በር ቆለፈባት አሉ።

ከዛ ሊመታት እጁን ሲሰነዝርባት እጁን ያዝ አድርጋ አንስታ ጣለችው። ከዛ ከላይ ቁጭ ብላበት ቀጠቀጠችው ሰውዬው " ተጋደልን" እያለ መጮህ ጀመረ። በጣም ስትበረታበት "ገደለችኝ" ብሎ መጮህ ጀመረ።

ከዛ ሰዎች ሊገላግሉ መጡ በሩን እንደምንም ሰብረው ልክ ሲገቡ፣ ሚስትየው ፈጠን ብላ ገልበጥ አድርጋ ባሏን ከላዩዋ ላይ አስቀምጣ ከስሩ ገባች። ከዛ እሱም እሷን መምታት ጀመረ።

የገቡት ሰዎች አረ ገደልካት ብለው ሊዙት ሲሉ "ተውኝ አዲስ ተገልባጭ ነኝ " አለቸው ይባላል ።

ለፈገግታ..!

አንዱ ነው አሉ ሚስቱ አልታዘዝም ብላ አስቸገረችው። ከዛ ገርፎ ሊያስተካክላት አስቦ ጩኀቷ ከቤት ውጪ እንዳይሰማ ብሎ የቤቱን በር ቆለፈባት አሉ።

ከዛ ሊመታት እጁን ሲሰነዝርባት እጁን ያዝ አድርጋ አንስታ ጣለችው። ከዛ ከላይ ቁጭ ብላበት ቀጠቀጠችው ሰውዬው " ተጋደልን" እያለ መጮህ ጀመረ። በጣም ስትበረታበት "ገደለችኝ" ብሎ መጮህ ጀመረ።

ከዛ ሰዎች ሊገላግሉ መጡ በሩን እንደምንም ሰብረው ልክ ሲገቡ፣ ሚስትየው ፈጠን ብላ ገልበጥ አድርጋ ባሏን ከላዩዋ ላይ አስቀምጣ ከስሩ ገባች። ከዛ እሱም እሷን መምታት ጀመረ።

የገቡት ሰዎች አረ ገደልካት ብለው ሊዙት ሲሉ "ተውኝ አዲስ ተገልባጭ ነኝ " አለቸው ይባላል ።

Fouad Oumer |
@write_event
@write_event
@write_event
ሰሞንኛ
(በእውቀቱ ስዩም)

የሆነ ጊዜ ላይ የተወሰኑ ጓደኞቼን የምወዳት ልጅ ወላጆች ቤት ሽምግልና ላክሁዋቸው::
የፍቅረኛየ አባት “ልጁ ምናለው?” ብለው ጠየቁ ::
ከሽማግሌዎች አንዱ ትንሽ ሲያቅማማ ከቆየ በሁዋላ፥

“ ከሁለት መቶ ሺህ ያላነሰ ተከታይ አለው፤ ፌስቡክ ላይ “ ብሎ ተከዘ::
ቁሞ የመቅረት ታሪኬም በዛች ቀን ጀመረ፤

በቀደም ለታ፥ ፌስቡክ ፥ ከሁለት መቶ ሺህ በላይ ተከታዮቼ መካከል፥ ዘጠኝ ሺውን ብቻ አስቀርቶል ሌላውን አፈሰብኝ፤ የገንዘቡ ሳያንስ የተከታይ ግሽበት መታገስ የምችልበት ጫንቃ አልነበረኝም::

ከተከታዮቼ መሀል ፥ ጽፌ የምለጥፈውን አንብበው መውደዳቸውን የሚያሳዩኝ አስተያየቱን የሚለግሱኝ ከአስር ሺህ አይበልጡም፤ ከተከታዮቼ መሀል” ክንዴ ቢዝል፥ ምላሴን ቢያዳልጠው፥ ግጥሜ ልቦና ባይረታ፥ ቀልዴ ጥርስ ባይመታ፥ ልክ ልኬን ሊነግሩኝ መከትከቻውን እየሳሉ እሚጠብቁኝ እንዳሉ አውቃለሁ፤ዝም ብለው ደጃፍ ላይ ተቀምጠው ሳልፍ ሳገድም እሚያዩኝም ሞልተዋል::

ቢሆንም “
“ባይነዳ ባይረዳ ባይኖረውም ሀብት “
ከደጃፍ ሲቀመጥ ደስ ይላል አባት “ ይላል እማ ሸንበቆ ጠላ ቤት ግድግዳ ላይ የተለጠፈ ጥቅስ!
እኔም እለላሁ፤
“ባይለይክ፤ ባይኮምንት ፤ አሻራው ባይታይ”
ከደጃፍ ሲቀመጥ ደስ ይላል ተከታይ”

የፌስቡክ አለቃ ፥ በሁሉን አወቅነቱ፥ ይህንን ስሜቴን ተረድቶ ፥ በነበሩት ተከታዮቼ ላይ አንድ የቀበሌ አዳራሽ የሚሞሉ ተከታዮች ከራሱ ጨምሮ መለሰልኝ::

በባለፈው ዝግጅት ላይ ለታደሙ ወዳጆቼ የምስጋና ቃል ልጽፍ ሰንዳ ሰንዳ ስል መብራት እልም አለ:: እኛ ሰፈር ያለው ትራንስፎርመር በሚፈነዳበት መጠን የልደት ፊኛ አይፈነዳም ፤ አሁን አሁንማ፥ መብራት ሲጠፋ እንደ ድሮው መናደድ አቁሚያለሁ፤ በጨለማ ውስጥም ቢሆን ስራ እንዳልፈታ ምቾት እንዳላጣ አድርጌ ራሴን አላማምደዋለሁ፤ ሆመር ፥ ሀሰን አማኑ፥ እማሆይ ገላነሽ፥ ወዘተ፤ ውበት ፥ ሀሳብ እና ለዛ ለማፍለቅ የግድ ውጫዊ ብርሀን አስፈላጊ እንዳልሆነ ምስክር ናቸው፤ እንዲህ እያልሁ ዘና ብየ ጥቂት እንደቆየሁ አምፖሉ እንደ ነሀሴ ሰማይ ብልጭ ብሎ ድርግም ይላል፤ ጉዋደኛየ ምኡዝ አንድ የሚወዳት ልጅ ነበረች፤ የሆነ ቀን ሲጽፍላት አትመልስም፤ ሲደውልላት አታነሳም፤ ጭራሽ ለተወሰኑ ወራት መገኛዋን ሁሉ ትደመስሳለች፤ እሱም ያለ እሷ ለመኖር ራሱን ለማለማመድ ይፍጨረጨራል፤ ከዛ እፎይ ብሎ እየኖረ እያለ You miss me? 😘🥰😊 '' የሚል ቴክስት ትልክለታለች፤ አምፖሌ ብልጭ ብሎ የተለማመድሁትን የጨለማ ደስታ ሲያደፈርስብኝ ትዝ የሚለኝ ይሄ ነው፤

ጥለት ሚድያ ባሰናዳው የሰኞ ዝግጅት ላይ የታደማችሁ ምስጋናየን ይድረሳችሁ፤ ገና ሁለተኛ ዝግጅታችን እንደመሆኑ መጠን ጉድለታችንን ለማሻሻል አጥብቀን እንሰራለን፤ ሐረር ባንድ ጀንበር አልተገነባችም፤ (በጊዜው በጉልህ የታየው የድምጽ ችግር ከመብራት መጥፋት ጋራ በተያያዘ በጄኔረተር ምክንያት የመጣ ነው፤ ለዚህ ይቅርታ እንጠይቃለን) ሌላ እንዲስተካከል እምትፈልጉትን ሳታስባንኑ ፥ በአካል አግኝታችሁ፥ ምሳ እየጋበዛችሁ፤ ትከሻየን እየቸበቸባችሁ ንገሩኝ፤ በማቱሳላ አቆጣጠር ገና ልጅ ነኝ፤ እታረማለሁ::

የዝግጅቱ ቀን ከጉዋደኛየ ጋራ ስደርስ ጥቂት አርፍጄ ነበር፤ ከብሄራዊ ትያትር ወዲህ ማዶ፥ ኢትዮጵያ ሆቴልን አለፍ ብሎ ሰው በረጅሙ ተሰልፎ ሳይ ራሴን መቆጣጠር ተሳነኝ፤ ልቤ ተነካ፤” ወንድ ልጅ ብቻውን ነው እሚያለቅሰው “ ይላል ባለቅኔ ጸጋየ ገብረመድህን:: እኔ ግን ወንድ ልጅ በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ባያላቅስ ደስ ይለኛል፤ የዛን ቀን ግን አልቻልኩም፤ የደስታ እምባየ “ናፕኪን” ከደረት ኪሴ እስካወጣ እንኳን አልታገሰኝም

“ አሁን እኔ ይሄን የሚያህል ሰልፍ deserve አደርጋለሁ?”
አልሁት ጓደኛየን፥

“ ተረጋጋ! እነዚህ ወደ ሜክስኮ የሚሄደውን ምኒባስ ለመሳፈር የተሰለፉ ናቸው “

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!

https://t.me/write_event
ነጠብጣብ ሐሳቦች
በ. ሥ)
ሰማይ ከሚመክን ፤ይጸንስ መከራ
ያርግፍ ! ያርግፍ! ያርግፍ ! መኣት እያፈራ
የ’ሣት ዛፍ ባለበት ፤ ሰደድ አያስፈራ
.............
ከሐምሌት ጋር ሞቷል፤ የማመንታት ዓለም
ከሆኑ በኋላ፤ አለመሆን የለም
ሸክም ጸጋ ሆኗል፤ ጸጋህን አትግፋ
በጠባብ ዓለም ውስጥ፤ ትከሻህን አስፋ!
............
አንድ ሕልም እንደ ጠጅ፤ እየደጋገሙ
ንግር ፤ትንቢት ሳይሆን፤ ታሪክ እያልለሙ
ተኝቶ መነሣት
አቤት ሲያቅለሸልሽ
ጌታ ሆይ አትንሣት
ነፍሴን እንቆቅልሽ
(ከስብስብ ግጥሞች)
share and join
@write_event
@write_event
@write_event
ዝግ ዓለም
(በ.ሥ)
ከትራሴ ግድም ፤በተደፋው ሰማይ
ኮከብ እያበራ ፤በመከዳየ ላይ
ምንም አላነበብኩ ፤ከህዋው ግድግዳ
እውነትና ንጋት፤ እያደር እንግዳ፡፡
(ከስብስብ ግጥሞች)
share and join
@write_event
@write_event
@write_event
እረፉ!
“ዘመመ!” ብላችሁ የሰው ቤት አትግፉ
እሾህ ለማሳመር አበባ አታርግፉ።
እረፍ!
“ቆሜያለሁ!” ለማለት አጥሬን አትደገፍ
ለአመዳም ወዘናህ ቆዳዬን አትግፈፍ።
እረፍ!
በመስመርህ ፍካ በድንበርህ ለምልም
በየአልጋህ እደር በየእንቅልፍህ አልም።
እረፊ!
በኩረጃ ንባብ ትርጉም አትግደፊ
በሰባራ መርፌሽ የሰው ልክ አትስፊ።.
...ማን አንደጠለፈኝ ማን እንደሰበረኝ
ጠያቂ አጣሁ እንጂ መልስማ ነበረኝ።
#Eyayu Fenges


share and join
@write_event
@write_event
@write_event